ከድሬደዋ አስተዳደር ፖሊስ ኮሚሽን የተሰጠ መግለጫ

ፖሊስ ሁኔታውን በመቆጣጠር አካባቢውን ወደ ቀድሞ ሰላም ለመመለስ ከፌደሬል ፖሊስ ከመከላኪያና ሌሎች የፀጥታ ሀይሎች ጋር በመሆን ግጭቱን የማስቆምና የማረጋጋት ስራ እየሰራ ሲሆን 51 ተጠርጣሪዎችንም ይህ መግለጫ እስከ ተሰጠበት ግዜ ድረስ በቁጥጥር ስር አውሏል::
በመሆኑም ከዚህ በሃላ ግጭትና ሁከቶችን በመፍጠርና አለመረጋጋት እንዲኖር በማድረግ የግል ፍላጎትና ጥቅማቸውን ማሳካት የሚፈልጉ ማናቸውም ግለሰቦችና ቡድኖችን ፖሊስም ሆነ መላው የፀጥታ ሀይል የማይታገስና አስፈላጊውን እርምጃ የሚወስድ መሆኑን በጥብቅ ፖሊስ እያሳሰበ ወላጆችና መላው ማህበረሰብ ይህንኑ በመረዳትና በመገንዘብ ልጆቹን እንዲመክርና በእንዲሂ ያለህ ተግባር እንዳይሳተፉ በማድረግ የድርሻውን እንዲወጣ ሲል ፖሊስ ጥሪውን ጨምሮ ያቀርባል::
መስከረም 22 ቀን 2011 አ.ም