Connect with us

Opinions

ግለ-ትዝብት – ጠላን ማን ፈጠረው?

Published

on

Ethiopian Traditional Drink - Tella

ጠላን ማን ፈጠረው?
ከይርጋለም ብርሃኑ
Ethiopian Traditional Drink - Tella 2

ብዙውን ጊዜ በአለሁበት አካባቢ በኢትዮጵያውያን ድግስ ላይ ጠላ ከጓደኞቹ ከውስኪ እና ከቢራ ጋር ተሰልፎ ሳየት ይደንቀኛል:: ለመሆኑ “ጠላ” ማን ፈጠረው? የሚል ጥያቄ በአምሮዬ ይመላለሳል::

ድሮ! ድሮ! ዘመኑ በእርግጠኝነት መናገር ባይቻልም ጠላ በኢትዮጵያ ምድር የተፈጠረ ይመስለኛል። ቀማሚዎቹም ኢትዮጵያውያን ይመስሉኛል። ለዚሁ ማረጋገጫ ደግሞ በዚህ ዘመን ላይ የጠላን መጠጥ የሚጠቀሙት ኢትዮጵያውያን ብቻ ናቸውና:: ስለዚህ ጠላን የፈጠሩት ኢትዮጵያውያን ኬሚስ(chemist) ሴቶች መሆናቸው በእርግጠኝነት መናገር ይቻላል። እስከ ዛሬ ድረስም በኬሚስ እናቶቻችን ጠላ ለዚህ ዘመን ደርሶዋል:: ግን ለመጀመሪያ ጊዜ ጠላን ቀምማ ለመጠጥነት ያበቃች ሴት ማን ትሆን?? የፈጠራ ባለቤትነት መብት የማን ይሆን??መልሱን የምታውቁ ብታሳውቁኝ ደስ ይለኛል።

በሀገረ አሜሪካን በሰርግ፣ በክርስትና፣በሰንበቴ እና በአብይ በዓላት ጠላችን ከጓደኞቹ ከሌሎች መጠጦች ጋር እኩል ለተጠቃሚው ለምርጫ ይቀርባል። ነገር ግን ከእነዚህ ጓደኞቹ ጋር ሲሰለፍ መሸማቀቁ የማይቀር ነው። ምክንያቱም ውስኪ እና ሌሎችም ዘመነኛ ሆነው አሸብርቀው በሚያማምር ሁኔታ በውስጣቸው ያለው የአልኮል መጠን ተጽፎባቸው ለራሳቸው ብቻ በተሰራላቸው እቃ ለተጠቃሚው ይቀርባሉ። የጠላ አቀራረብ ግን ለራሱ በተሰራላት እንደ ሌሎቹ የአልኮል መጠን ተጽፎለት ሳይሆን ለሌሎች መጠጦች በተሰራ በተውሶ እቃ ለተጠቃሚው ይቀርባል። ታድያ የተውሶ ልብስ መልበስ አያሸማቅቅም ትላላቹ??

ጠላ ድሮ ሲፈጠር ፈጣሪዎቹ ለእሱ ብቻ የሚሆን በሸክላ በተሰራ ገንቦ ውስጥ ይጠምቁት ነበረ። ለእሱ ብቻ የተዘጋጀ ማቅረቢያ እና መጠጫ እቃ ነበረው። የሸክላ ገንቦ ሰሪዎች ኢትዮጵያውያን እንደሆኑም ብዙ ምርምር የሚያሻው አይመስለኝም። “ሸክላ ሰሪ” እየተባሉ በሙያቸው እየተንቋሸሹም ሸክለኞቹ ከእኛ ዘመን ላይ ደርሰዋል። ጠላ በእኛ ዘመን ግን በገንቦ የመጠመቅ እድል አላገኘም ምክንያቱም ገንቦ መጠቀም ኋላ ቀርነት ነውና። ያው መቼስ የውጪ አድናቂዎች አይደለን?? ይቅይታ እኔም የውጪ አድናቂ ነኝ። ጠላ ዘንድሮ ልክ እንደ ሀገራችን ኢትዮጵያ በልጽጋ እና አድጋ ፈረጆች በሰሩለት በብረት በርሜል ለመጠመቅ በቃ። እንኳን ደስ አለሽ ጠላ! አንቺም ፈረጆች በሰሩት በአቀራረብ ለማሸብረቅ ባትበቂም ለመጠመቅ ግን በቃሽ። ፈረጆቹ በርሜል የሰሩት ነዳጅ ለማመላስ ነበረ። እኛ ደግሞ አሻሽለን በርሜሏ ጠላ መጥመቂያ አደረግናት። እድገት ይሉታል እንዲህ ነው! የራስ እውቀት እና ፈጠራ ወደ ገደል ከቶ የሌላውን እውቀት እና ፈጠራ መጠቀም። ገንቦዋ በእኛው አሰራር እና ልማድ ማሳደግ እና ማሻሻል ግን አልቻልንም።

የጠላ ፈጣሪዎች ነፍሳቸውን ይማረውና እኛን ቢያዩ እንዴት ይታዘቡን ይሆን? ኧረ! እነሱማ በስንቱ ይታዘቡናል። ለሁሉም “ሆድ ይፍጀው”። ጠላ አለመታደል ሆኖ በኢትዮጵያ ምድር ተፈጠረችና እንደነ ውስኪ እና ቢራ ለሌሎች ዓለማት ለመተዋወቅም አልበቃችም። ያው እኛ ያለንን አድንቀን የራሳችንን ማሻሻል እንደ ኋላ ቀርነት ስለምንቆጥር እነ ውስኪ እና ቢራ በሀገራችን ኢትዮጵያ ዘመናዊ ፋብሪካ እየተሰራላቸው ነው። ለመሆኑ ጠላ በዘመናዊ የሸክላ ገንቦዎች ፋብሪካ ተሰርቶላት እንደ ቢራ እና ሌሎች ለዓለም ለመሰራጨት አትበቃም ነበረን??

 

Continue Reading
2 Comments

2 Comments

  1. Anonymous

    September 25, 2014 at 3:31 pm

    Trash!

  2. worwor

    September 25, 2014 at 6:03 am

    As anything was not taken shape out of the blue, Tella itself had been a chemistry that developed over generations. From this we can deduce that the credit is for the society not for a particular women or men. The issue of commercializing Tella is indeed a good point.

Leave a Reply

Your email address will not be published.

News

EthioTube ወቅታዊ – ኢትዮጵያ እና አሜሪካ ወዴት? | Ethiopia and United States Relations

Published

on

hqdefault
Continue Reading

Articles

የ40 /60 ፈተና – በአርኪቴክት ዮሐንስ መኮንን

Published

on

By

40-60 Buildings in Addis Ababa

40-60 Buildings in Addis Ababa

አዲስ አበባ ከተማን ሰንገው ከያዝዋት ችግሮች መካከል የመኖሪያ ቤት ችግርን የሚስተካከለው ያለ አይመስለኝም፡፡ ዜጎች ከግማሽ በላይ የሚሆነውን ገቢያቸውን ለቤት ኪራይ ስለሚያውሉ ቀጣይነት ያለው ሃብት መፍጠሪያ አቅም ነስቷቸዋል፡፡ የኽም ኑሮአችንን በመከራ የተሞላ አድርጎብናል፡፡ ይኽንን ችግር በዘላቂነት ለመፍታት መንግስት የቤቶች ግንባታ ፕሮገራም መንደፉ የሚያስመሰግነው ቢሆንም ወደ መሬት ያወረደበት መንገድ ግን አነጋጋሪ ሆኖ የሚቀጥል ይመስለኛል፡፡

ከነኚህ ፕሮግራሞች አንዱ የሆነው በተለምዶ 40/60 በመባል የሚታወቀው የቤቶች ግንባታ በመሠረታዊ የዲዛይን ስህተቶች የተሞላ እና ስህተቶቹን ለማረም የተኬደበት መንገድም ሌላ ተጨማሪ ስህተት የፈጠረ ይመስለኛል፡፡ ለመሆኑ ስህተቶቹ ምንድናቸው?

1) ፕሮግራሙ እና የተሠሩት ቤቶች አይተዋወቁም፡፡ ዜጎች ‹‹ታገኙታላችሁ›› በተባሉት አጠቃላይ የወለል ስፋት መሠረት በባንክ መቆጠብ መጀመራቸው ይታወቃል፡፡ ይሁን እንጂ በጥድፊያ እንዲገነቡ የተደረጉት አፓርታማዎች ግንባታቸው ከተጋመሰ በኋላ የወለል ስፋታቸው የተዛነፈ መሆኑ በመታወቁ እንደምንም ተብቃቅተው መንግስት ከዜጎች ጋር በተፈራረረመው ውል መሰረት እንዲስተካከሉ ለማድረግ ጥረት እየተደረገ ነው፡፡ (በአጭሩ ለማስረዳት ጃኬት ለማሰፋት ለተዋዋለ ደንበኛ ካፖርት ከሠፉ በኋላ ስህተቱን ለማረም ካፖርቱን በመቆራረጥ ሌሎች ጃኬቶች ለማውጣት እንደመሞከር ያለ ነው፡፡ከካፖርት ጃኬት ይወጣ ይሆናል፡፡ ግን የተጨማደደ እና የተጣበበ መሆኑን መቀበል ይኖርብናል፡፡ በ40/60 እየሆነ ያለውም ይኼው ነው፡፡)
2) የአደጋ ጊዜ ማለጫ የላቸውም፡፡ ግንባታቸው ከተጋመሰ በኋላ የታወቀውን የአደጋ ጊዜ ማመለጫ ደረጃ ቀድሞ ባልታሰበበት ሁኔታ ‹‹እንደምንም ብላችሁ አንድ ጥግ ፈልጉለት›› በማለት ለመፍታት መሞከር መፍትሔውን ሰንካላ ማድረጉ አይቀሬ ነው፡፡
3) የቆሻሻ ማስወገጃ ሊኖራቸው ይገባ ነበር፡፡ 12 ፎቅ ተገንብቶ ነዋሪዎች የሚያስወግዱትን ደረቅ ቆሻሻ በፌስታል ቋጥረው እንዲወርዱ ማሰብ ተገቢ አይደለም፡፡ በቀላሉ የቆሻሻ ማንሸራተቻ (Trash shooter) ማሰብ ይገባ ነበር፡፡ 
4) ለሁሉም በሽታ አንድ ክትባት! እንኳንስ ህንጻ ዛፍ እንኳን ሲተከል ከቦታ ቦታ የተለያየ እና ተስማሚ ዓይነት ይመረጣል፡፡ አሁን የሚሠሩት አፓርታማዎች ግን ለሁሉም የንፋስና የፀሐይ አቅጣጫዎች፣ ለአፈር እና ለድንጋይ ዓይነቶች እንዴት አንድ ዲዛይን ይሠራል? ይህን ያህል ጥድፊያስ ም ለማትረፍ ነው?
5) ንድፉ አያምርም፡፡ ይህን የመሰለ ከፍተኛ በጀት እና ጉልበት የሚፈስበት ብሔራዊ ዕቅድ በቂ የባለሙያዎች ክርክር እና ጥናት ሳይደረግበት በጥድፊያ በተሞላ ውሳኔ ወደ ተግባር መገባት አልነበረበትም፡፡ ሲሆን ሲሆን ከፍተኛ አማካሪዎች የተሳተፉበት የዲዛይን ውድድር ተደርጎ የተሻለው ሊመረጥ ይገባ ነበር !

የእነኚህ ሁሉ ችግሮች ምንጮች ሁለት ናቸው፡፡ ጥድፊያ እና አነስተኛ ግምት ! መፍትሔው ከዚሁ ይመነጫል፡፡ ሰከን ብሎ ማሰብ እና ተገቢው ትኩረት! ሀሳቡ የፓርቲ ሳይሆን የመላእክት እንኳን ቢሆን አፈጻጸሙ ከተበላሸ ፈተናውን ወደቀ ማለት ነው ፡፡

 

Source: አርኪቴክት ዮሐንስ መኮንን

Continue Reading

Keenya ስለእኛ

የወገኔ “Amarika”

Published

on

flag2

flag2

ያገሬ ሰዉ ፤ ከቀየዉ ቢሻለኝ ቀን ቢያወጣልኝ ብሎ ነፍሱን ሸጦ የፈለሰበትን ምድር ስም ተይብ ቢባል የሚያስፍራቸዉ ፊደላት ናቸዉ፤ Amarika….ብዬ ብጀምር ማጋነን ይሆንብኛል :: ወገኔ በ Amarika ድህነትን ሊያራግፍ ሀብት ሊሸምት ግዞትን አሽቀንጠሮ ነፃነትን ሊሸክፍ ተስፋን ሰንቆ ከተተ በAmarikaም ከተመ፡፡ ከወገን ኖሮ ከመራብ በሀገር ኖሮ ከመሰደብ በመሸበት አድሮ ከባየተዋር ምድር ጥጋብ እና ክብርን ሽቶ ሮጠ፤ ተሰደደ፡፡ ሆነለት፡፡ የቀን ሶስት ሩብ እየለፋ ከምን እንደተሰራ በማይታወቅ እንጀራ ሆዱን እየነፋ እነ እማማን እነ አባባን እነ ኩቺን እነጢሎን ዶላር ያስመረዝራል፤ ቀን ያወጣላቸዋል፤ ከጎረቤት በላይ ያደርጋቸዋል፡፡ እሱ የመኪና ተራ እያስጠበቀ እነ እማማን እነ ጢሎን ባለጋቢና ያደርጋቸዋል፡፡ ሳይማር አሜሪካ የላከዉን ህዝብ ሳይማር ወግ ያስተምረዋል፡፡ ለነ ኩቺም ያሜሪካ ወንድማቸዉ ከእግዜር በታች ከኦባማ ጎን ነግሶ የትንሽ ስራ መራቂያ ያሜሪካ መናፈቂያ የጎረቤት ማስፈራሪያ ሆኖ ይኖራል፡፡ ወገኔም ይህን ያዉቀዋል፤ ጎረቤታቸዉን እነ ቡለቲን አፍ ማስያዙ ያኮራዋል፡፡ ስራዉን ኑሮዉን ደብቆ የስራ ትንሽ እንደሌለ ቤተሰቡን ይመክራል፡፡ ስለወገኔ ኑሮ ዝርዝር ሁኔታ በስልክም ሆነ ባካል ከሱ ጋር መነጋገር አያስፈልግም የሴት ዕድሜ የሱ ስራ አይጠየቅማ፡፡ የቤቱ ትልቅነት የመኪናዉ ዘመናዊነት በአሜሪካዊዉ ወገኔ በዝርዝር ሊወሳ ይችላል፡፡ ይህ ማለት ግን የሱ ቤት የሱ መኪና ነዉ ማለት ላይሆን ይችላል፤ አይጠየቅም፡፡

ነገ ያቺ ሙሉ ቀን ስትመጣ ከስምንት ሻንጣ ጨርቅ እብድ ከሚያክል ስልክ እና የአሜሪካ ሰንደቅ ካለበት ካኒቴራ ጋር ቦሌ ይደርሳል እነኩቺም ካስራ አምስት ዘመድ አዝማድና ዳጎስ ካለ ብድር ጋር ይቀበሉታልእንኳን ላፈርህ አበቃህከዛማ የአንድ ወር ቆይታው በፌሽታና በአሜሪካ ኑሮ ትረካ የተሞላ ይሆናል፡፡ እንደዛ ሲሰራ ሲለፋ ለኖረው ወገኔ መዝናናት ሲያንስ ነው::

ችግር፤ ተስፋ ማጣት፤ ፖለቲካ፤ ጭቆና…ብዙ ብዙ ምክንያት ከምንወዳት ሀገራችን ያፈናቅሉናል፤፤ አሜሪካ እንዲሁም ሌሎች የሰለጠነዉ አለም የተሻለ አማራጭ ሆነዉ እናገኛቸዋለን፡፡ ለማንኛዉም ምክንያት ይሁን ሀገር ቀይሮ መኖር የግለሰብ ዉሳኔ ነዉ፡፡ ሊከበርም ይገባዋል፡፡ ይህ እንዳለ ሆኖ ግን የምንሄድበትን ቦታ፤ የምናልመዉን ኑሮ በሚገባ መረዳት ቅድሚያ ሊሰጠዉ የሚገባ ጉዳይ ይመስለኛል፡፡ የተሻለ ለዉጥን መፈለግ ድንቅ ነዉ፡፡ ለመለወጥ ግን ማወቅ ይቀድማል፡፡

አሜሪካን በእንግሊዝኛ ተይብ ቢባል አብዛኛዉ በትክክል እንደሚፅፍ ተስፋ አደርጋለሁ፡፡ ነገር ግን ምን ያህሉ ሊኖርባት የመረጣትን ሀገር ቋንቋ ለመግባቢያ እንኳን በሚጠቅም ደረጃ ያዉቃል ብትሉኝ በጣም ጥቂቱ ይሆናል መልሴ፡፡ የተወሰኑ ቃላትን በአሜሪካዊያን ዘይቤ ይጠራ ይሆናል፡፡ ነገር ግን አንድ ሙሉ አረፍተ ነገር በተሟላ መልኩ ቀምኖ አያቀርብም፡፡ በዚህ አይነት ሁኔታ ታዲያ ከታክሲ ሹፌርነት እና ከመኪና ጠባቂነት ያለፈ ህልም እንዴት ይኖረዋል፡፡ ቀን ሲሞላ ተመልሶ ወይንም በስልክ ስለአሜሪካ ሰማይ ጠቀስ ህንፃዎች እና ህዝብ ገድል ከማዉራት ያለፈ ህልም ልንሰንቅ እንችላለን? ሁሌ ከህንፃዉ ዙሪያ ያሉትን ጥቃቅን ስራዎቸን ሰንሰራ መኖርን ከማለም፤ ለወገናችን የተሳሳተ(ያልተሟላ) መረጃን ከመስጠት፤ ራሳችንን አለአግባብ ከመኮፈስ አልፈን ህንፃዉ ዉስጥ ካሉት ሰዎች ራሳችንን እንደአንዱ የማየት፤ ህንፃዉንም ሆነ ዉስጡ ያሉትን ንግዶች (አገልግሎቶች) የራስ የማድረግ ህልም ቢኖረን ይበዛብናል? አይመስለኝም ከአንድ ድሃ የአፍሪካ ሀገር የሄደ ስደተኛ ልጅን መሪዋ አድርጋ ለመሾም የፈቀደች ሀገር እኛ ከተጋን ትምህቱንም ሆነ ሀብቱን አትከለከንም። ለዚህ ደግሞ ማሳያ የሚሆኑ ወገኖቻችን በዙሪያችን ሞልተዉናል።

ነገር ግን መጀመሪያ መማር ማወቅ ለመለወጥ መዘጋጀት ይቀድማል። አሁን ምንሰበስበው ስምንትና ዘጠኝ ዶላር ለነገው ህልማችን ግብዐት እንጂ ራሳችንን ማታለያ የሀገር ቤት ወገናችንን ማደናበሪያ መሳሪያ መሆን የለበትም።

በነገራችን ላይ ይህ ጽሑፍ በትምህቱም ሆነ በንግዱ ለራሳቸው ስኬታማ ለወገን ኩራት የሆኑትን አይመለከትም። እነሱ በተቃራኒው ለነኩቺ ወንድም ወገኔ ምሳሌዎች ናቸው። በል እንግዲህ ወገኔ ወደ Amarika ስትመለስ መዝገበ ቃላት ስንቅህ ይሁን ከዛ ለሚጥለው ደረጃ ስትበቃ እንማከራለን:: ደህና ሰንብቱ።

Continue Reading

Trending