Sports
ጌድዮን ዘላለም እና አሚን አስካር- —-ዶ/ር ቴድሮስ አድሀኖም ለዋልያዉ ተጫዋች እየመለመሉ ነዉ!!

አኝህ ሰዉ በብዙ ነገር ይለያሉ፤ጊታር ይዘዉ ሲዘፍኑ አይቼ ገርሞኛል፤ደቡብ አፍሪካ ላይ ቡድኑ በናይጄሪያ 2-0 ተሸንፎ ከዉድድሩ ሲወጣ ስልክ ደዉለዉ ከ40 ደቂቃ በላይ እኔና ተጫዋቾቹን ሲያናግሩ ከምርም ያገባኛል የሚሉ ሰዉ እንደሆኑ ተገንዝቤያለሁ፤ኒዉዮርክ ላይ ያደረጉትንም ንግግር ካያችሁ ሳይደንቃችሁ ያለፈ አይመስለኝም…አሁን ደሞ ወደ ዋልያዉ ፊታቸዉን አዙረዉ ተጫዋቾችን እያግባቡ ነዉ!!የሐገሬ ዉጭ ጉዳይ ሚኒስትር ለብሂራዊ ቡድኑ ተጫዋቾች ለማምጣት ሲነጋገሩ በርግጥም ኮርቻለሁ!!
ጌድዩን ዘላለም ስለዋልያ– በናይጄሪያ ጨዋታ ዙሪያ አስተያየቱን በቲዉተር ድረ-ገጹ አስነበበ፤
ከጨዋታዉ በሁዋላ ..አሁንም ኮርቻለሁ የሚል አስተያየት ነዉ የጻፈዉ፤የዉጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ዶ/ር ቴድሮስ አድሀኖም ለጌድዮን ፈጣን ምላሽ ሰጡ፤እንዲህም ብለዉ ከተቡለት፤
Hi Gedieon..Good to hear from u..We hope u will play for Ethiopia soon.
በዚህ ብቻ አላበቁም፤በኖርዌይ ከሚጫወተዉ አሚን አስካርንና ጌድዮንን ለማግኘት ጥረታቸዉን ቀጠሉ፤ከአሚን አስካር ፈጣን ምላሽ አገኙ፤ስልክ ቁጥሩን ላከላቸዉ እናም አዋሩት..ኢትዮጲያ መጥቶ እንዲጫት ጥሪ አቀረቡለት..በጣም ደስተኛ መሆኑን ገለጸላቸዉ፤በማቃት ስዊድንኛ…በቅርቢ ስትጫወት አያሀለሁ ብየ ተስፋ አደርጋለሁ አሉት!!አሰልጣኝ ሰዉነት ለጊዜዉም ቢሆን አሚንን እንማይፈልጉት መናገራቸዉ ይታወሳል፤
ለጌድዮን ዘላለም ያቀረቡት ጥሪም ቲዉተርን ከተቀላቀሉ ወዲህ በከፍተኛ ቁጥር የተነበበ መሆኑን ጠቅሰዋል፤ይህን ተከትሎም ሰዉየዉ የምን ደጋፊ እንደሆኑ ተጠይቀዋል፤እኔ የዋልያዉ ደጋፊ ብቻ ነኝ ብለዋል፤
አሁን የጌድዮን መልስ እየተጠበቀ ነዉ፤በዉጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ደረጃ ለዋልያዎቹ እንዲጫወት ጥሪ ቀርቦለታል፤ለጊዜዉ ጉዳት ላይ ነዉ፤ያም ቢሆን ግን በቅርቡ ይመለሳል፤እናም ለዋልያዉ እጫወታለሁ መልሱን በቅርቡ እንደሚያሰማቸዉ ዶክተር ቴድሮስ ተስፋቸዉን አስቀምጠዋል፤የዕሁዱን ጨዋታ በስታድየም ተገኝተዉ መከታተላቸዉን አትዘንጉ..ደሞ አዳነ ግርማን ከሚያደንቀዉ ልጃቸዉ ጋር ነበር የመጡት!!
እኔ ከሁሉም የገረመኝ ነገር ሚኒስትሩ የዋልያዉን ዋና ክፍተት የሆነዉ መሀል ሜዳ ላይ መፍትሄ መፈለጋቸዉ ነዉ!!አንድም የጌድዮን አይነት የአማካይነት ሚና የሚጫወት ፈጣሪ ተጫዋች በቡደኑ የለም፤ዶ/ር ከሰሙኝ እንዲህ ልበላቸዉ..””ሀገር ዉስጥ የሚጫወቱ ከጌድዮን የሚበልጡ አማካዮች በቡድኑ እንዲካተቱ እባክዋትን ጥሪ ለአሰልጣኙ ያቅርቡልን!!
Articles
በኦስሎ ዳይመንድ ሊግ የ5000ሜ ፉክክር ኢትዮጵያውያን አትሌቶች በሁለቱም ፆታዎች በአሸናፊነት አጠናቀዋል

ትላንት ምሽት በኖርዌይ ኦስሎ በተከናወነው የዳይመንድ ሊግ 5000 ሜ. ውድድር ኢትዮጵያውያን አትሌቶች በወንዶችም በሴቶችም ከአንደኛ እስከ ሶስተኛ ያሉትን ደረጃዎች በመቆጣጠር አሸንፈዋል፡፡ በዝናባማ የአየር ሁኔታ ውስጥ በተካሄደው የሴቶች 5000 ሜትር ፉክክር ዳዊት ስዩም በመጨረሻዎቹ መቶ ሜትሮች ውስጥ ፍጥነቷን በመጨመር ጉዳፍ እና ለተሰንበትን ቀድማ አንደኛ ወጥታለች፡፡ የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ለኦሪገን 2022 የአለም ሻምፒዮና ከመረጣቸው ዕጩ አትሌቶች ዝርዝር ውስጥ ያልተካተተችው ዳዊት በኦስሎ ያሸነፈችበት 14፡25.84 የሆነ ሰአት የራሷ ምርጥ ሲሆን እጅጋየሁ ታዬ (14.12.98) እና ለተሰንበት (14፡24.59) ባለፈው ወር በዩጂን ካስመዘገቧቸው በመቀጠልም የዘንድሮ የአለም ሶስተኛው ፈጣን ነው፡፡ በውድድሩ ላይ ከነበሩት ሌሎች ኢትዮጵያውያን መካከል በዘንድሮው የውድድር ዓመት በርቀቱ የመጀመሪያ ተሳትፎዋን ያደረገችው አልማዝ አያና በ14:32.17 ስድስተኛ ሆና አጠናቃለች፡፡ ሀዊ ፈይሳ በ14:33.66፣ ፅጌ ገብረሰላማ በ14:43.90፣ እና አበራሽ ምንሴዎ በ14:47.98 በቅደም ተከተል ሰባተኛ፣ አስረኛ እና አስራ አንደኛ ሆነው ሲያጠናቅቁ ሶስቱም ያስመዘገቡት ሰዓት የራሳቸውን ምርጥ ያሻሻሉበት ሆኗል፡፡ ጥሩነሽ ዲባባ እ.ኤ.አ. በጁን 2008 ዓ.ም. ያስመዘገበችውና 14:11.15 የሆነው የኦስሎ ዳይመንድ ሊግ የሴቶች 5000 ሜትር የውድድር ስፍራ ሪከርድ ይሰበራል ተብሎ ተጠብቆ የነበረ ቢሆንም ሳይሳካ ቀርቷል፡፡

ዳዊት ስዩም ውድድሩን በድል ካጠናቀቀች በኋላ ለውድድሩ አዘጋጆች በሰጠችው አስተያየት ‹‹ዛሬ ለእኔ ደስታን ስላመጣልኝ በውድድሩ ሰዓት የነበረውን ዝናብ ወድጄዋለሁ ማለት እችላለሁ፡፡ ጠንካራ ተፎካካሪዎች የነበሩበት ከባድ ውድድር ነበር እናም ሁሉንም ለማሸነፍ በቅቻለሁ። በርቀቱ የራሴን ምርጥ ሰዓት ማሻሻል መቻሌም አስፈላጊ ነበር፡፡ በስታድየሙ ውስጥ በከፍተኛ ስሜት ድጋፍ ይሰጡን የነበሩ ወገኖቻችን ነበሩ። ለሰጡን ድጋፍ እናመሰግናለን።›› ብላለች፡፡ በኦስሎ የወንዶች 5000 ሜትር የመጨረሻ ፉክክሩ በኢትዮጵያውያኑ ጥላሁን ሀይሌ እና ሳሙኤል ተፈራ መካከል የነበረ ሲሆን ጥላሁን የ1500 ሜትር ስፔሻሊስቱ ሳሙኤልን በአጨራረስ ፍጥነት ቀድሞ በ13:03.51 በአንደኛነት አጠናቋል፡፡ ሳሙኤል ተፈራ የራሱ ምርጥ በሆነ 13:04.35 ሁለተኛ ሲወጣ ጌትነት ዋለ የግሉ የዓመቱ ምርጥ በሆነ 13:04.48 ሶስተኛ ደረጃን ይዞ ጨርሷል። በውድድሩ ላይ የነበሩት ሌሎች ኢትዮጵያውያን ሚልኬሳ መንገሻ በ13:05.94 አምስተኛ እንዲሁም አሊ አብዱልመናን የራሱ ምርጥ በሆነ 13:16.97 አስረኛ ወጥተዋል፡፡

ጥላሁን ሀይሌ ውድድሩን በአሸናፊነት ካጠናቀቀ በኋላ ለውድድሩ አዘጋጆች በሰጠው አስተያየት ‹‹ሶስት ኢትዮጵያውያን የመጀመሪያዎቹን ሶስት ደረጃዎች ይዘን መጨረስ መቻላችን ጥሩ አፈጻጸም ነበር። እየጠነከርኩ እንደሆነ የተሰማኝ ሲሆን በውድድሩ እና ባስመዘገብኩት ሰዓትም ተደስቻለሁ። ለረጅም ጊዜ ጉዳት ላይ ስለነበኩ ወደ አሸናፊነቱ መመለስ መቻሌ በጣም ጥሩ ነው።›› ብሏል፡፡
በኦስሎ የሴቶች 800ሜ. ውድድር ላይ ተፎካካሪ የነበረችው ኢትዮጵያዊቷ ድሪቤ ወልቴጂ በ1፡58.69 አምስተኛ ሆና አጠናቃለች።
Articles
የዘንድሮው የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ብሄራዊ ሻምፒዮና በእኔ እይታ

ከመጋቢት19-24/2014 ዓ.ም በሐዋሳ አለም አቀፍ ስቴድዮም የተደረገው 51ኛዉ የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ሻምፒዮና ከሞላ ጎደል ስኬታማ በሚባል ሁኔታ ተጠናቋል፡፡ ከአምስት አመት በኋላ በድጋሚ በአካል በመገኘት ስለተከታተልኩት የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ሀገር አቀፍ ሻምፒዮና የግል ምልከታዬን እንደሚከተለው አጠናቅሬዋለሁ፡፡ የበለጠ ትኩረትን በሳቡት ውድድሮች ዙሪያ የተመዘገቡ ውጤቶችን በወፍ በረር በመዳሰስ ስጀምር ከፍተኛ ፉክክር በታየበት የመጨረሻ ቀን የወንዶች 5000ሜ. የአለም ከ20 አመት በታች ሻምፒዮና የ3000ሜ የብር ሜዳልያ አሸናፊው አሊ አብዱልመና 13፡45.0 በሆነ ሰዓት ከጥላሁን ሀይሌ፣ ጌትነት ዋለ እና ዮሚፍ ቀጄልቻ ቀድሞ አሸናፊ ሆኗል፡፡ የፉክክሩ አካል የነበረው እና የርቀቱ የወቅቱ የአለም ሻምፒዮን ሙክታር እድሪስ ስድስተኛ ወጥቷል። ከ20 ዓመት በታች የ3000ሜ የአለም ሻምፒዮኑ ታደሰ ወርቁ በ28፡12.0 የወንዶች 10,000ሜ. ሻምፒዮን ሲሆን በ1996 ዓ.ም. በአትሌት ስለሺ ስህን ተመዝግቦ የነበረውን 28፡16.23 የሆነ የሻምፒዮናው ሪኮርድ ለማሻሻልም በቅቷል፡፡ በ10 ሺህ ሜትር የሴቶች ፉክክር ግርማዊት ገብረእግዚአብሔር በቀዳሚነት የጨረሰችበት 31፡21.5 የሆነ ሰዓት አዲስ የሻምፒዮንሺፕ ሪኮርድ ሆኖ ተመዝግቧል፡፡ በርቀቱ የከዚህ ቀደሙ ሪኮርድ ለተሰንበት ግደይ ከሶስት ዓመት በፊት ያስመዘገበችው 32፡10.13 የሆነ ሰዓት ነበር፡፡ ሳሙኤል ፍሬው በዘንድሮ የወንዶች 3000ሜ. መሰናክል አፈፃፀም ከአለም ሁለተኛው ፈጣን በሆነ 8፡22.5 ሰዓት አሸናፊ ሲሆን ጌትነት ዋለ ከአራት ዓመት በፊት አስመዝግቦት የነበረውን 8፡28.98 የነበረ የሻምፒዮናው ሪኮርድም አሻሽሏል፡፡ በሴቶች 3000ሜ. መሰናክል ከ800ሜ ወደ ረጅም ርቀት የተሸጋገረችው ወርቅውሃ ጌታቸው በ9፡41.8 ሰዓት መቅደስ አበበን (9:43.8) በማስከትል በአሸናፊነት አጠናቃለች። አድሃና ካህሳይ (3:51.0) የወንዶች 1500ሜ ፉክክሩን በበላይት ሲያጠናቅቅ በሴቶች 1500 ሜ አያል ዳኛቸው (4:10.0) ተጠባቂዋ ዳዊት ስዩምን (4:11.1) በመቅደም በአንደኛነት አጠናቃለች። በ800ሜ. ወንዶች ቶሌሳ ቦደና (1:47.1) በሴቶች ወርቅነሽ መሰለ (2:02.1) አሸናፊ ሆነዋል። ዮብሰን ብሩ በ400ሜ/400ሜ መሰናክል (45.9/50.5) ድርብ ድል ሲቀዳጅ፣ በወንዶች ጦር ውርወራ ኡታጌ ኡባንግ ብሔራዊ ሪኮርድ በሆነ 73.28ሜ. አሸንፏል፡፡ የኋልዬ በለጠው እና ዮሃንስ አልጋው በእርምጃ ሩጫ የሻምፒዮንነት ክብርን ተቀዳጅተዋል። ጥቂት አስተያየቶች፡- የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ስፖርት አፍቃሪ እንደሆነ እና ለዕድገቱ እንደሚቆረቆር ሰው በብሔራዊ ሻምፒዮናው ላይ ስለተመለከትኳቸው አዎንታዊ እና አሉታዊ ጎኖች ጥቂት አስተያየቶቼን እንደሚከተለው አስቀምጣለሁ፡- አዎንታዊ ጎኖች • ባለው ነባራዊ ሁኔታ ውስጥ ሊገጥሙ የሚችሉትን ተግዳሮቶች በሙሉ በመቋቋም ፌዴሬሽኑ ውድድሩን ከአዲስ አበባ ውጭ አካሂዶ በሰላም ማጠናቀቅ መቻሉ አንደኛው ስኬቱ ነው፡፡ • በሻምፒዮናው ላይ ጥቂት የማይባሉ ታዋቂ አትሌቶች በሀገሪቱ ትልቁ የአትሌቲክስ ፉክክር ላይ ተሳታፊ ሆነው ሲወዳደሩ መመልከት የተቻለ ሲሆን በተለይም በወንዶች 5000 ሜትር ፍፃሜ ላይ የታየው የኮከብ አትሌቶች ፉክክር ልዩ ነበር፡፡ • በውድድሩ ወቅት ለአትሌቲክስ ዳኞች የብቃት ማሻሻያ ስልጠና መሰጠቱም የውድድሩን ጥራት ለማሳደግ የሚረዳ እንደመሆኑ እሰየው የሚባል ነው፡፡ • እንደ ኢትዮ ኤሌክትሪክ ያሉት ክለቦች ለአትሌቲክስ ስፖርት የበለጠ ትኩረት በመስጠትና ተጠናክሮ በመቅረብ ከዚህ ቀደም በጠንካራነታቸው ከሚታወቁት መከላከያ እና ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ጋር የቅርብ ተፎካካሪ ሆነው መታየት፤ የኦሮሚያ ክልል፣ ደቡብ ፖሊስ እና ሲዳማ ቡና ክለብ አትሌቶችም ጠንካራ ተሳትፎ ሳይዘነጋ የሻምፒዮናው ፉክክር ድምቀት ነበሩ፡፡ • የአንዳንዶቹ ተገቢነት አጠያያቂ ቢሆንም ብዛት ያላቸው የሻምፒዮናው ሪኮርዶች የተሻሻሉበት ውድድርም ነበር፡፡ አሉታዊ ጎኖች • የሀገሪቱ ትልቁ የአትሌቲክስ ውድድር ውጤት አሁንም በኤሌክትሮኒክስ የሰዓት መቆጣጠሪያ የማይደገፍ መሆኑ በተለይም በአጭር ርቀት እና በሜዳ ላይ ተግባራት ውድድሮች ላይ የሚሳተፉ አትሌቶች ልፋት ተገቢውን እውቅና እንዳያገኝ እያደረገ ይገኛል፡፡ የሻምፒዮናውን ውጤቶች በዘመናዊ እና ዓለም አቀፉን መለኪያ በሚያሟላ መልኩ አለመያዝ በአህጉራዊ እና አለም አቀፋዊ ውድድሮች ላይ ለተሳትፎ የሚያበቁ ውጤቶችን በማስመዝገቡ ረገድ የሚኖረው አሉታዊ ተፅዕኖ ከፍተኛ መሆኑ ከግምት ውስጥ ገብቶ አሁንም መፍትሄ ያልተበጀለት ጉዳይ ነው፡፡ • የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ወደ ሚዲያ/ለአጠቃላዩ ሕዝብ የሚያስተላልፈው የመጀመሪያዎቹን ሶስት ደረጃዎች ይዘው የሚያጠናቅቁ አትሌቶችን ውጤት ብቻ መሆኑ አወዳዳሪው አካል የሚያደርገውን የራሱን ውድድርም ሆነ አትሌቶቹ የለፉበትን ውጤት ከማስተዋወቅ አኳያ በቂ አይደለም፡፡ • በወንዶች የጦር ውርወራ እና የሴቶች ምርኩዝ ዝላይ ብሔራዊ ሪኮርዶች እንደተመዘገቡ ይታመናል፤ በሴቶች 100ሜ መሰናክል እና የወንዶች 400ሜ መሰናክል የተመዘገቡት ሰዓቶችም የምንግዜውም ፈጣን ሊሆኑ ይችላሉ፡፡ ነገር ግን ውድድሩ በኤሌክትሮኒክስ ታይሚንግ ያልተደገፈ እና የንፋስ ንባብ ያልነበረው መሆኑ ውጤቶቹ በዓለም አቀፍ ደረጃ ተቀባይነት እንዳይኖራቸው የሚያደርግ ነው። • በ20 ኪ.ሜ የእርምጃ ውድድር ላይ በሁለቱም ፆታዎች የተመዘገቡት ሰዓቶች ከሚጠበቀው በላይ እጅግ በጣም ፈጣን እና እውነታዊ አለመምሰላቸው በውድድሩ ላይ የተፈጠረ አንዳች ስህተት መኖሩን የሚያመላክቱ መሆኑ፡፡ እንዲህ አይነት ለማመን የሚከብዱ እና ጥርጣሬን የሚፈጥሩ አይነት ውጤቶች ሲመዘገቡም የተፈጠረ ስህተት መኖር አለመኖሩን ለማጣራት አለመሞከሩ፡፡ • የሴቶች 10 ኪሎ ሜትር ውድድር ላይ ለውድድር የማይፈቀድ የጎዳና ላይ መሮጫ ጫማን በመጠቀም የተመዘገበ ውጤት በሪኮርድነት ጭምር ተይዞ መፅደቁ። ብሔራዊ ፌዴሬሽኑ ከተከለከሉ ጫማዎች ጋር የተያያዙ ዓለም አቀፍ ሕገ ደንቦችን ማወቅና መተግበር ቢገባውም በሴቶች 10 ሺህ ሜትር ውድድር ላይ የተከሰተው ነገር የውድድር ሕገ ደንቦቹ መረጃ በፌዴሬሽኑ ውስጥ በትክክል የተሰራጩ እንዳልሆነ የሚያመላከት ነው፡፡ • በሴቶች 1500 ሜትር የግማሽ ፍፃሜ ውድድር ላይ አትሌት ዳዊት ስዩም የሻምፒዮናውን ሪኮርድ ያሻሻለችበት ውጤት እንደተመዘገበ በውድድሩ ወቅት በተደጋጋሚ ሲነገር ከተደመጠ በኋላ ግልፅ ባልተደረገ ምክንያት ውጤቱ በሐዋሳው ውድድር ላይ ተሻሻሉ ከተባሉት የሻምፒዮናው አዲስ ሪኮርዶች ዝርዝር ውስጥ ሳይካተት መቅረቱም የፌዴሬሽኑን ግልፀኝነት ጥያቄ ምልክት ውስጥ የሚከት ነው፡፡ ከላይ የተዘረዘሩት አዎንታዊ እና አሉታዊ ጎኖች ለረጅም ግዜ የኢትዮጵያን አትሌቲክስ ስፖርት እንቅስቃሴዎች በቅርበት ከመከታተሌ አንፃር በራሴ እይታ ያስቀመጥኳቸው እንደመሆናቸው አንዳንዶቹ ሀሳቦች አከራካሪ ሊሆኑ ይችላሉ፡፡ ሆኖም የውድድር ደንቦችን በአግባቡ ከማስፈፀም አኳያ በታዩት ክፍተቶች ዙሪያ ምንም የሚያከራክር ጉዳይ ስለሌለ በወቅታዊ የውድድር ደንቦች ዙሪያ የግንዛቤ እጥረት ላለባቸው የስፖርቱ ባለድርሻ አካላት በሙሉ አስፈላጊውን ገለፃ እና ትምህርት መስጠት የፌዴሬሽኑ ኃላፊነት ነው፡፡ ከውድድር ጋር የተያያዙ ደንቦችን ከመጣስ አኳያ በሀገር ውስጥ በሚደረጉ ውድድሮች እንደቀላል ነገር የሚታለፉ ጉዳዮች በዓለም አቀፍ ውድድሮች ላይም ተደግመው እንደግል አትሌቶችን እንደቡድን ሀገርን ትልቅ ዋጋ ሊያስከፍሉ ይችላሉና አስፈላጊው ጥንቃቄ ቢደረግ መልካም ነው፡፡ ባለፈው መስከረም ወር በቪየና ሲቲ ማራቶን ውድድሩን በአሸናፊነት ጨርሶ የነበረው ኢትዮጵያዊው ደራራ ሁሪሳ የገጠመውን አንዘንጋው! ሀገራችን ኢትዮጵያን በመልካም ጎኑ ስሟ እንዲነሳ በሚያደርገው እና በትልልቅ ዓለም አቀፍ የውድድር መድረኮች ላይ የኩራታችን ምንጭ በሆነው የአትሌቲክስ ስፖርት እንደጎረቤታችን ኬንያ ዓለም አቀፍ ውድድሮችን የማስተናገድ የብቃት ደረጃ ላይ ደርሰን ማየት የዘወትር ምኞቴ ነው፡፡ የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌደሬሽንም የውድድሮቹን ጥራት ለማሻሻል በትኩረት እንደሚሰራ ተስፋ አደርጋለሁ።
በመጨረሻም በሀዋሳ በተካሄደው 51ኛዉ የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ሻምፒዮና ከመሮጫ ጫማ ጋር የተያያዙ ደንቦችን በማስከበሩ ረገድ የተፈጠረውን ክፍተት እንደማስተማሪያ ብንጠቀምበት በሚል የሚከተለውን ለማለት ወደድኩ፡-
የመሮጫ ጫማ ደንቦች ለትራክ ውድድር
64 ደቂቃ ከ14 ሰከንድ በሆነ ሰዓት የዘንድሮ የራስ አል ካይማህ የግማሽ ማራቶን ውድድር አሸናፊ የሆነችው ግርማዊት ገብረእግዚአብሔር በሐዋሳ በተከናወነው 51ኛው የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ሻምፒዮና ላይ 31 ደቂቃ ከ21.5 ሰከንድ በመግባት የ10,000ሜ. አሸናፊ ሆናለች፡፡ የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽንም ዓለም አቀፉን ደንብ ከግምት ባላስገባ ሁኔታ ውጤቱን በአዲስ የሻምፒዮንሺፕ ሪኮርድነት ጭምር አፅድቆት አልፏል፡፡ ይሁን እንጂ መጋቢት 20/2014 በተደረገው የሴቶች የፍፃሜ ፉክክር ላይ በኢትዮጵያ ምድር የተመዘገበ የምንግዜውም ፈጣን የሴቶች 10 ሺህ ሜትር ሰዓት የሆነው ውጤት በአለም አትሌቲክስ ዘንድ እውቅና ሊሰጠው የማይችል ነው።
● ለምን?
አትሌቷ የሶል ውፍረቱ 40ሚሜ የሆነ ዙምኤክስ ቬፐርፍላይ (ZoomX Vaporfly) ጫማ አድርጋ በመወዳደሯ ምክንያት።
● ደንቡ ምን ይላል?
በትራክ ውድድሮች ላይ የሚፈቀደው ከፍተኛው የሶል ውፍረት ፡-
– 20ሚሜ ከ 800ሜ በታች ለሆኑ ውድድሮች እና ለሁሉም የሜዳ ላይ ተግባራት (ከስሉስ ዝላይ በስተቀር)
– 25ሚሜ ለ800ሜ እና ከዛ በላይ ለሆኑ ውድድሮች እንዲሁም ለስሉስ ዝላይ
– 40ሚሜ ለትራክ ላይ የእርምጃ ውድድሮች
እነዚህ ደንቦች እ.ኤ.አ. እስከ ኦክቶበር 31, 2024 ድረስ በሥራ ላይ ይውላሉ። ከኖቬምበር 1 ቀን 2024 ጀምሮ ለ800ሜ እና ከዚያ በላይ ለሆኑ ውድድሮች እንዲሁም ለስሉስ ዝላይ የሚፈቀደው ከፍተኛ የሶል ውፍረትም ወደ 20 ሚሜ ዝቅ የሚል ይሆናል።
● የትራክ ላይ መወዳደሪያ ስፓይክ ጫማ ከሌለኝስ?
ደንቡ የጎዳና ላይ የመሮጫ ጫማዎች በትራክ ላይ እንዳይደረጉ አይከለክልም ነገር ግን በ25 ሚሊ ሜትሩ ገደብ ምክንያት 30 ሚሜ ወይም 40 ሚሜ የሆኑ የጎዳና ላይ መሮጫ ጫማዎች በትራክ ውድድሮች ላይ እንዲደረጉ አይፈቅድም፡፡
● ለበለጠ መረጃ :-
https://www.worldathletics.org/news/press-releases/new-athletic-shoe-regulations-approved-2022
Articles
የቶኪዮ 2020 ኦሊምፒክ የኢትዮጵያ የአትሌቲክስ ተሳትፎ ድህረ ምልከታ

በቶኪዮ 2020 ኦሊምፒክ በወረቀት ደረጃ ከውድድሩ መጀመር በፊት ቡድኑ ባመዛኙ በጥሩ ብቃት ላይ የሚገኙ ወጣት አትሌቶችን ስላካተተ ቢያንስ የለመድናቸውን ሁለት ወይም ሶስት የወርቅ ሜዳልያ ድሎች እንደማያሳጣን ተስፋ አድርጌ ነበር፡፡ ሆኖም የሜዳ ላይ ውጤቱ እንደተጠበቀው ሳይሆን ቀርቷል፡፡ ኢትዮጵያ በውጤታማነቷ በምትታወቅበት የአትሌቲክስ ፉክክር በአንድ የወርቅ፣ አንድ የብር፣ እና ሁለት የነሐስ በድምሩ በአራት ሜዳልያዎች ከዓለም 14ኛ ከአፍሪካ 3ኛ ደረጃን ይዛ ጨርሳለች፡፡ ይህም ሁሌም ለአፍሪካ የበላይነት ከምንፎካከራት ኬንያ ጋር ያለን ልዩነት ይበልጥ እንዲሰፋ አድጎታል፡፡ ከቅርብ ግዜ ወዲህ ሌላኛዋ የምስራቅ አፍሪካ ተቀናቃኛችን እየሆነች ከመጣችው ኡጋንዳም አንሰን እንድንገኝ አድርጎናል፡፡ የቶኪዮ ኦሊምፒክ በአትሌቲክሱ ከ1992ቱ የባርሴሎና ኦሊምፒክ ወዲህ ኢትዮጵያ ዝቅተኛ የሜዳልያ ስኬት ያስመዘገበችበትም ሆኖ አልፏል፡፡
አሉታዊ ጎኖች
ቶኪዮ የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ውጤታማነት ፈር ቀዳጅ የሆነው ታላቁ አትሌት ሻምበል አበበ ቢቂላ በ1964 ዓ.ም. በተከታታይ ሁለተኛ የኦሊምፒክ ማራቶን ድሉን የተቀዳጀባት ከተማ ናት፡፡ እናም በቶኪዮ ከተማ በተከናወነው የኦሊምፒክ ውድድር የኢትዮጵያ ልዑካን ቡድን የሱን ክብር የሚያጎሉባቸውን ነገሮች ያደርጋሉ ብዬ ጠብቄ ነበር፡፡ የሆኑት ነገሮች ግን በተለይ በቡድኑ አስተዳዳሪዎች በኩል ፍፁም ኃላፊነት የጎደለውና ከጠበቅኩት በተቃራኒው ነበር፡፡ የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን እና የኢትዮጵያ ኦሊምፒክ ኮሚቴ ከአትሌቶች ምርጫ አንስቶ በቡድኑ የዝግጅት ወቅት በተካረረ ውዝግብ ውስጥ ነበር የከረሙት፡፡ የኦሊምፒክ ቡድኑን የማዘጋጀት እና የመምራት የጋራ ኃላፊነት የነበረባቸው ሁለቱ አካላት ይባስ ብለው ውዝግቡን ቶኪዮ ድረስ ይዘውት ሄደዋል፡፡ ይህ ሁሉ ሲሆን ሁለቱን አካላት በማቀራረብ በትልቁ ውድድር ላይ ያለንን ተሳትፎ እንከን አልባ ማድግ የሚጠበቅባቸውም ተመልካች ከመሆን የዘለለ ሚና አልነበራቸውም። የውዝግቡ አሉታዊ ትሩፋት በአትሌቶች ስነልቦና እና በአጠቃላይ የቡድኑ ውጤት ላይ የበኩሉን ተፅዕኖ ሳያሳርፍ እንዳላለፈ አያጠራጥርም፡፡
እንደ አለመታደል ሆኖ በቶኪዮ ኦሎምፒክ የኢትዮጵያን ልዑካን የመምራት ትልቁ ኃላፊነት የተሰጣቸው ሰዎች ኃላፊነት የጎደላቸው ነበሩ። የስፖርቱ አስተዳደሪዎች ትላልቅ ዓለም አቀፍ ውድድሮች በመጡ ቁጥር በአትሌቶች ምርጫ ዙሪያ የነበረውን ውዝግብ እንዲያቆሙልን እመኝ ነበር። ጭራሽ እራሳቸው ችግር ፈጣሪ ሆነው መገኘታቸው አስደንጋጭ እና አሳሳቢ ጉዳይ ነው፡፡ በመሮጫ መም ወይም በጎዳና ላይ በሚደረጉ ውድድሮች መሸነፍን በስፖርቱ ውስጥ ማሸነፍ እና መሸነፍ ያሉ የነበሩ እና ወደፊትም የሚኖሩ ነገሮች ስለሆኑ በፀጋ መቀበል ይቻላል፡፡ ተወዳዳሪዎቹ ውጤታማ እንዲሆኑ የስነልቦና ጥንካሬን ሊፈጥሩላቸው የሚገቡ ኃላፊዎች የእርስ በርስ ሽኩቻ ተቃራኒውን አሉታዊ ተፅዕኖ ሲያሳርፍ ማየት ግን ፍፁም ተቀባይነት የለውም፡፡ ለነገሩ ከስፖርቱ እድገት ይልቅ የፖለቲካ ግዴታቸው የሚያስጨንቃቸው የስፖርት አመራሮች በበዙባት ሀገር ስፖርቱ እንዲህ የማንም መጫወቻ ሲሆን ማየት አዲስ ነገር አይደለም፡፡
የስፖርት አመራሮች ከፖለቲካ ተፅዕኖ ነፃ ሆነው ትኩረታቸውን ስፖርቱን በማስፋፋቱ እና ማሳደጉ ላይ አድርገው የሚሰሩ ስለስፖርቱም በቂ እውቀት እና ፍቅሩ ያላቸው ቢሆኑ መልካም ነው፡፡ ለቦታው በሚመጥን እና ኃላፊነቱን በአግባቡ መወጣት በሚችል የስፖርት አመራር የሚመራ የስፖርት ተቋምን መገንባት በተመሳሳይ ሰዓት የሀገር ግንባታን የሚደግፉ ሶስት ነገሮችን ስኬታማ ያደርጋል፡፡ በስፖርት ጤናውን የሚጠብቅ ማሕበረሰብ በመፍጠር በጤናው ሴክተር ላይ የሚኖረውን ጫና ይቀንሳል፣ በሀገር ገፅታ ግንባታ እና በኢኮኖሚው ዕድገት ላይም የበኩሉን ከፍተኛ አስተዋፅኦ ያደርጋል፡፡ በቶኪዮ ላይ የተመለከትናቸው የሀገርን ክብር ዝቅ ያደረጉ ግዴለሽነቶች ተገቢው ትኩረት ተሰጥቷቸው ሊታዩና አጥፊዎቹ ሊጠየቁበት ይገባል፡፡ በመጪዎቹ ዓመታት በሚጠብቁን ዓለም አቀፍ ውድድሮች ላይም የቶኪዮ ኦሊምፒኩን አይነት ሀፍረት እንዳይገጥመን ከወዲሁ ለችግሮቹ መፍትሔ መፈለግ አለበት፡፡
ባለፉት ዓመታት ኦሊምፒክ በመጣ ቁጥር በልዑካን ቡድኑ ውስጥ እየተካተቱ በሕዝብ ገንዘብ የሚዝናኑት የኦሊምፒክ ቱሪስቶች ጉዳይ ዘንድሮም ያልተቀረፈ ችግር ሆኖ ተስተውሏል፡፡ ከሌላው ግዜ በተለየ መልኩ ተጠባባቂ አትሌቶችን ይዞ መጓዝ ይጠይቅ በነበረው ውድድር ላይ አትሌቶቹን ትቶ ምንም የማይሰሩ ሰዎችን ይዞ መሄድ ትልቅ ቀልድ ነው፡፡
ከሜዳ ውጭ የነበረው ውዝግብ ዋነኛ የትኩረት ማዕከል የነበረ መሆኑ በሜዳ ላይ የነበሩብንን ድክመቶች ሊያስረሳንም አይገባም፡፡ ስድስት የጎዳና ላይ ተወዳደሪዎቻችን እና አንድ የመም ተወዳዳሪ ውድድራቸውን ማቋረጣቸው በቶኪዮ ከታዩት ደካማ ጎኖቻችን መካከል የሚጠቀስ ነው፡፡ ችግሩ በዚህ ምክንያት ነው የተከሰተው ብሎ ለይቶ ለመናገር ባይቻልም ብዙ ግዜ ሲፈትነን ለሚስተዋለው የሞቃታማ ቦታ ውድድር የምናደርጋቸው ዝግጅቶችን መለስ ብሎ መመልከትን የሚጠይቅ ይመስለኛል፡፡ የተጎዳች አትሌትን ወደውድድር እንድትገባ ማድረግ እና በሁለት ደቂቃ ውስጥ ለማቋረጥ መገደዷም የአትሌቶች የጤና ክትትል ላይ ክፍተት እንዳለ የጠቆመን ክስተት ነው፡፡
የኢትዮጵያ ኦሊምፒክ ቡድን ወደውድድር ስፍራው ካቀናበት ግዜ ጀምሮ በቶኪዮ ምንም አይነት ቡድኑን የተመለከቱ ይፋዊ ጋዜጣዊ መግለጫዎች ወይም ፕሬስ ሪሊዞች አልነበሩም፡፡ ይህም እንደተለመደው የሕብረተሰቡን እና የመገናኛ ብዙሀንን ስለቡድኑ ቀጥተኛ መረጃ የማግኘት መብት የገደበ ነበር፡፡ ጋዜጠኞችም ሚዛናዊ ሆኖ ከመዘገብ ይልቅ ጎራ ለይተው ቃላት መወራወራቸው የህዝብን ትክክለኛ መረጃ የማግኘት መብት የነፈገ ነው፡፡
አዎንታዊ ጎኖች
ሰለሞን ባረጋ በወንዶች 10,000 ሜትር ወርቅ፣ ለሜቻ ግርማ በወንዶች 3000 ሜትር መሰናክል ብር፣ ጉዳፍ ፀጋዬ በሴቶች 5000 ሜትር ነሐስ፣ እና ለተሰንበት ግደይ በሴቶች 10,000 ሜትር ነሐስ ማስመዝገብ መቻላቸው የሚደነቅ ስኬት ነው፡፡
የመጪው ትውልድ አካል የሆኑት ተስፈኞቹ መቅደስ አበበ፣ ፍሬወይኒ ሀይሉ፣ በሪሁ አረጋዊ እና ጌትነት ዋለን ጨምሮ አምስት አትሌቶች ለሜዳሊያ የቀረበ የአራተኛነት ደረጃን ይዘው ማጠናቀቅ መቻላቸውም መልካም ነው፡፡ በተለይ ወጣቶቹ ያስመዘገቡት ውጤት በመጪዎቹ ዓመታት ተገቢውን ድጋፍ ካገኙ የምንጓጓለትን ድል ሊያስገኙልን እንደሚችሉ ያመላከተን ነው፡፡
የሀብታም አለሙ በኢትዮጵያ የኦሊምፒክ ተሳትፎ ታሪክ በሴቶች 800 ሜትር ለመጀመሪያ ግዜ ለፍፃሜ ተወዳዳሪነት መብቃት ምንም እንኳ በፍፃሜው የሜዳልያ ድል ባይቀናትም በአዎንታዊ ጎን ሊጠቀስ የሚችል ስኬት ነው፡፡
ከአንደኛ እስከ ስምንተኛ ደረጃን ይዘው ላጠናቀቁ አትሌቶች በሚሰጥ ነጥብ ድምር መሰረት በወጣው የነጥብ (ፕሌስመንት) ደረጃ ሰንጠረዥ ላይ በ64 ነጥብ ዘጠነኛ ሆነን ማጠናቀቃችንም እሰየው የሚያስብል ነው፡፡
በቶኪዮ ኦሊምፒክ ከአራተኛ እስከ ስምንተኛ ባሉት ደረጃዎች ውስጥ አጠናቀው ነጥብ ያስገኙ እና የዲፕሎማ ተሸላሚ የሆኑት አትሌቶች፡-
4ኛ – ፍሬወይኒ ሀይሉ – በሴቶች 1500 ሜትር
4ኛ – መቅደስ አበበ – በሴቶች 3000 ሜትር መሰናክል
4ኛ – ሮዛ ደረጀ – በሴቶች ማራቶን
4ኛ – በሪሁ አረጋዊ – በወንዶች 10,000 ሜትር
4ኛ – ጌትነት ዋለ – በወንዶች 3000 ሜትር መሰናክል
5ኛ – እጅጋየሁ ታዬ – በሴቶች 5000 ሜትር
6ኛ – ሀብታም አለሙ – በሴቶች 800 ሜትር
6ኛ – ሰንበሬ ተፈሪ – በሴቶች 5000 ሜትር
8ኛ – ዮሚፍ ቀጄልቻ – በወንዶች 10,000 ሜትር
8ኛ – ዘርፌ ወንድማገኝ – በሴቶች 3000 ሜትር መሰናክል

- የአትሌቲክስ የነጥብ ደረጃ ሰንጠረዥ ከአንደኛ እስከ ስምንተኛ ባሉት ደረጃዎች ውስጥ የሚያጠናቅቁ አትሌቶች በሚያስመዘግቡት ነጥብ ድምር መሰረት የሚወጣ ሲሆን የነጥብ አሰጣጡም ለአንደኛ ደረጃ 8 ነጥብ፣ ለሁለተኛ ደረጃ 7 ነጥብ፣ ለሶስተኛ ደረጃ 6 ነጥብ፣ ለአራተኛ ደረጃ 5 ነጥብ፣ ለአምስተኛ ደረጃ 4 ነጥብ፣ ለስድስተኛ ደረጃ 3 ነጥብ፣ ለሰባተኛ ደረጃ 2 ነጥብ፣ እና ለስምንተኛ ደረጃ 1 ነጥብ ነው።
ከፊታችን ምን እየጠበቀን ነው? ምንስ እናድርግ?
ባለፈው ዓመት በዓለም አቀፉ ወረርሺኝ ምክንያት ትልልቅ ዓለም አቀፍ ውድድሮች ለሌላ ግዜ እንዲተላለፉ መደረጉ ይታወቃል፡፡ ሌላ አስገዳጅ ሁኔታ ካልተፈጠረ በስተቀር ቀጣዮቹ አራት ዓመታት በተከታታይ በየዓመቱ ዓለም አቀፍ የአትሌቲክስ ውድድሮች የሚካሄዱባቸው ይሆናሉ፡፡ በ2022 የዓለም ሻምፒዮና፣ በ2023 የዓለም ሻምፒዮና፣ በ2024 የኦሊምፒክ ጨዋታዎች፣ እና በ2025 የዓለም ሻምፒዮና ውድድሮች ይኖራሉ፡፡ በቀጣዩ ዓመት በኢትዮጵያ የቀን አቆጣጠር ከሐምሌ 8 – 17/2014 በዩናይትድ ስቴትስ ኦሪጎን የሚካሄደው የዓለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና አዘጋጆች ሙሉ የውድድሩን ፕሮግራም፣ የማራቶን እና የእርምጃ ውድድሮች የሚካሄዱባቸውን ቦታዎች በትላንትናው ዕለት ይፋ አድርገዋል፡፡ የዓለም ሻምፒዮናውን ውድድር በኃላፊነት የሚመራው የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽንም ከወዲሁ ለዛ ውድድር ተሳትፎ የሚጠበቅበትን አቅዶ መንቀሳቀስ ይኖበርታል፡፡
ከምርጫ ጋር በተያያዘ የሚነሱ ጭቅጭቆችን ለማስቀረት ከወዲሁ ሁሉም አትሌቶች አውቀውት በውስጡ የሚያልፉበትን ገዢ የሆነ የመምረጫ መስፈርት ማዘጋጀት ቀዳሚው ተግባር መሆን አለበት፡፡ የመምረጫ መስፈርት ሁልግዜም በግላዊ ምልከታ እና ፍላጎቶች ላይ በሚመሰረት ምክንያት አነጋጋሪ መሆኑ የማይቀር ነው፡፡ ቢሆንም ባለድርሻ አካላቱን በሙሉ ባሳተፈ መልኩ ውይይት ተደርጎበት ቢወጣ ሁሉንም ገዢ እና ከጭቅጭቅ የፀዳ ሊሆን ይችላል፡፡ እዚህ ላይ በቶኪዮ ኦሊምፒክ ከተከሰቱት ሁኔታዎች አንፃር የሌሎች ሀገሮችንም ተሞክሮዎች በመዳሰስ ነገሩን ሰፋ አድርጎ መመልከት ቢቻል ጥሩ ነው፡፡ ትልልቅ ውድድሮች በመጡ ቁጥር በተደጋጋሚ እንደታዘብነው አንዳንድ አትሌቶች በቡድኑ ውስጥ ለመካተት የሚያደርጉትን ተገቢ ያልሆነ ሙከራም ማቆም አለባቸው፡፡ ከፋም ለማም ስፖርቱን እንዲመራ ኃላፊነት የተሰጠው ተቋም የሚያወጣቸውን መስፈርቶች ማክበርና በዛ ውስጥ ተመራጭ ለመሆን መሞከር ግድ እንደሚላቸውም መዘንጋት የለባቸውም፡፡ ማኔጀሮች እና አሰልጣኞች በተለይ በማራቶን የራሳቸውን አትሌት ለማስመረጥ የሚያደርጓቸው አላስፈላጊ ግፊቶችም ሊያቆሙ ይገባል፡፡
ለውድድሮች የምናደርጋቸውን ዝግጅቶች ጠንካራ እና ደካማ ጎኖች ከውድድሮች በኋላ መገምገም እና መታረም ያለባቸው ነገሮች ካሉ ማረም፡፡ ከፍተኛ ሙቀት በነበረባቸው በለንደን 2012 ኦሊምፒክ ሶስቱም የወንዶች ማራቶን ተወዳዳሪዎቻችን፣ በሞስኮ 2013 የዓለም ሻምፒዮና ሁለቱ የሴቶች ማራቶን ተወዳዳሪዎቻችን፣ በቶኪዮ ኦሊምፒክ ላይ አምስት የማራቶን (ሶስቱም ወንዶች እና ሁለት ሴቶች) ተወዳዳሪዎቻችን እንዲሁም የሴቶች እርምጃ ተወዳዳሪያችን ለማቋረጥ መገደዳቸውን አስተውለናል፡፡ ስለዚህ በጎዳና ላይ ውድድሮች ከባድ ሙቀት ለሚኖርባቸው ቦታዎች እንዴት መዘጋጀት አለብን የሚለው ጉዳይም በደንብ ሊታይ የሚገባው ይመስለኛል፡፡ አንዳንድ የመም (ትራክ) ተወዳዳሪ አትሌቶቻችን የውድድር ዓመቱ ሲጀምር ድንቅ ብቃታቸውን ያሳዩን እና ወደትልቅ ውድድር ሲቃረቡ አቋማቸው እየወረደ ይመጣል፡፡ አሰልጣኞቻቸው ለእነዚህ አይነቶቹ አትሌቶች ወደትልቅ ውድድር ሲቃረቡ ብቃታቸውን እያሳደጉ እንዲሄዱ የሚረዳቸውን የልምምድ ፕሮግራም ቢያዘጋጁላቸው መልካም ነው፡፡ በመካከለኛ ርቀት ውድድሮች ላይ በተለይ በወንዶች አሁንም በከፍተኛ ደረጃ የሚፎካከሩ አትሌቶችን ለማፍራት ጠንክረን መስራት ይጠበቅብናል፡፡
-
EBS Mogachoch8 years ago
[New] EBS Drama Series – Mogachoch : ሞጋቾች | Episode 7
-
Articles9 years ago
Ethiopia’s renewable energy revolution shouldn’t fail to empower its poor
-
News2 years ago
መንግሥት ከሕወሓት ይልቅ ለአገሪቱ ሥጋት የሆኑ ሌሎች ችግሮች አሉብኝ አለ
-
Opinions1 year ago
On the TPLF’s Love Affair With ‘Genocide’
-
Music4 years ago
2019 ESFNA Atlanta: Ethiopian Day – Ethiopia Hagerachin : ኢትዮጵያ ሀገራችን
-
Music4 years ago
2019 #ESFNA Atlanta: Ethiopian Day | Neway Debebe – Hageren Alresam : ሀገሬን አልረሳም
-
Articles8 years ago
ሰበር ዜና፦ ተዋናይት ሰብለ ተፈራ (ትርፌ) በመኪና አደጋ ህይወቷ አለፈ
-
Bahilawi Zefenoch10 years ago
Bahilawi Zefenoch – ባህላዊ ዘፈኖች
Anonymous
February 7, 2014 at 9:40 am
As known D/r is doing many things which makes Ethiopia to be known in world, from all his works what made me unbelieving is that, his speaking on EGAD meeting about sud arbia cases.He said “we or our former Governors made positive things for SAUDI immigrants, but they…..
Zinabu
October 17, 2013 at 2:02 pm
Bravo Doc
betelhem mengiste
October 17, 2013 at 1:21 pm
I am proud of u. I just wish all ministers just like u (be free to express their feeling)
Anonymous
October 17, 2013 at 9:52 am
endh aynet be ethiopia tayto aytawokem yketlubet
zenayeneh Girma
October 17, 2013 at 8:11 am
I am confident enough to say Dr Tewodros is very committed, dedicated, visionary and inspiring leader. I know him very well since my childhood while he was working with my Dad in the Ministry of Health. Really he is optimistic positive mind and enthusiastic. I mate him at Makush Restaurant for the first time in 2008 which is his favorite place to enjoy with people and dealing a lot of business with donors. I also get the chance to have a meal sitting nearby him conversing lots of development issues regarding about his country with international people on international meeting at Sheraton Hotel couple of times.
Personally I hope and believe he will do a lot for our country.
God bless you and wish you to be safe and sound including your family.
paul
October 17, 2013 at 6:31 am
bastard guy….i think you dont have know how on foot ball.
Bex
October 17, 2013 at 2:39 am
Aye Said, Ye buna degafi nesh malet new.
Ekram mol
October 17, 2013 at 12:55 am
Betam. Des. Ylal. Bwnet. Ethiopa. lzlam. Tnur. Bkber
Anonymous
October 17, 2013 at 12:50 am
Betam. Des. Ylal. Bwnet. Ethiopa. lzlam. Tnur. Bkber
sebsibe
October 16, 2013 at 7:10 pm
#Still proud#
tarekegn
October 16, 2013 at 4:06 pm
I actually agree on the idea of DR. Tewodros,but Is Mr. Sewunet agree on the idea? It may be difficult
Amanuel
October 16, 2013 at 3:16 pm
ከዘመኑ የኢትዩጵያ መሪዎች ሁሉ አብልጨ ለምዎድዎ ዶ/ር በየቀኑ የሚሰሩትና የሚያደርጉት ነገር በጣም ያስደስተኛል… ለቀጣይ ኢሀዴግ ኢትዩጵያን እንዲመራ ፈጽሞ አልፈልግም! ነገር ግን እርስዎ ጠቅላይ ሚኒስትራችን ሆነው በነጻነት የራስዎን ፍላጎትና እውቀት መጠቀም የሚችሉ ቢሆን ለቀጣዩቹ 30 ዓመታትም ቢሆን ኢህዴግ ኢትዩጵያን ቢገዛ አልቃዎምም…! መማር ጥሩ ነው እውቀትም ሀብት ነው ይህ ደግሞ ለሃገር እድገትና ልማት ስናውለው ለመንፈስ እርካታ ለወገንም አለኝታ ነው፡፡ እርስዎ በእኔ እምነት ጥሩ መሪ መሆን ይችላሉ በጥላቻ ሳይሆን በፍቅር አሸንፈውናል፡፡ ጸባይዎን ፈጣሪ አይቀይረው ጤናዎን፣ መልካሙን አዕምሮና እረጅም እድሜ ይስጥዎ!
Amanuel
October 16, 2013 at 3:13 pm
yea Gadi , we hope u play for Ethiopia
tank you Dr. Tewodros
Anonymous
October 16, 2013 at 3:07 pm
Aste Tewodros bilihis!!!!!!
halefom
October 16, 2013 at 3:02 pm
good idea docter
Ephrem Mekonen
October 16, 2013 at 2:45 pm
we proud on you!!!
Temesgen Sisay
October 16, 2013 at 1:53 pm
why you are doing this silly thing….why dont you do your part rather than blaming others with out ….i will not say this…….
Temesgen Sisay
October 16, 2013 at 1:49 pm
I know Dr. Tewodros,he is really smart Guy….he will do a lot for the country the above you mentioned are very minor things. We will expect a lot…he is not like those Politician, he is a real man….Love you Teddy!!!!!
ABEBE BELAY
October 16, 2013 at 1:40 pm
We’re lucky
Elda
October 16, 2013 at 1:30 pm
yea Gadi , we hope u play for Ethiopia
tank you Dr. Tewodros
Yohannes Damtew
October 16, 2013 at 1:24 pm
we are lucky to have a leader like you who gives time(of his busy schedule) to fix football which is the passion of the Ethiopian people. We have great hope to have a better stadium as we deserve in the near future so that coaches like Stephen won’t poke jokes at us as well as our team will have a better pitch to practice on. We definately need Ethiopian footballers in the Diaspora to be part of this awakening giant soon and your contacting these players at a highr office as you hold will go a long way to help. Please also put your weight in producing the next generation of footballers in a systematic way in order that our happiness derived from football will continue for many years to come. Thank you once again!
dejene
October 16, 2013 at 12:47 pm
this is an idea.what our country and also our world need.i agree with your idea.
Anonymous
October 16, 2013 at 12:43 pm
አምባ ገነኑን አሰልጣኝ ምትቋቋመው አይመስለኝም ቢመጡ እንኳን ከተቀያሪ ወንበር ሳይነሱ ይመለሷታል
Anonymous
October 16, 2013 at 12:11 pm
ክብር ለደ/ር ቴድሮስ በጣም ሊመስገኑ የሚገባዎት ነው ከትልቅ የሰራ ሃላፊነት በተጨማሪነት ወደ ስፖርቶ ፊቶትን በማዞሩት ሊመሰገኑ ይገባዎታል፤፤እኔ ግን ለል የፈለኮት ባሎት ከፍተኛ የስልጣን ሃላፊነት ለዚህ ምስኪን ህዝብ አንድ የሚጸናናበት ስታድዪም ባሰሩለት
ለርሶም ክብር ነው፤፤አመስግናለው ዶ/ር
Anonymous
October 16, 2013 at 11:55 am
i want you be prime minster.
Anonymous
October 16, 2013 at 10:23 am
Dr tewdrus adhanom thanks for everything.
ግርማ
October 16, 2013 at 10:17 am
ዶ/ር ቴድሮስ የጀመርከው ስራ በጣም መልካም ነው ስለሆነ ተስፋ ሳትቆርጥ ቀጥልበት እግዚአብሔር ካንተ ጋር ሆኖ ምታስበውን ያሳካልህ ዘንድ ልባዊ ምኞቴ ነው…. አበቃሁ
Anonymous
October 16, 2013 at 9:53 am
በርግጥ ዶክተር ቴዎድሮስን በጣም አደንቃለሁ እያደረጉ ስላለው መልካም ስራ… በተጨማሪም ዶክተር ቴዎድሮስ በነፃነት ለሃገር ጉዳይ እንዲሰሩ ነፃነቱን ለሰጧቸው ጠቅላይ ሚንስትር ኃይለማሪያም ደሳለኝንም ማድነቄ አይቀርም… ከአሁን በፊት እንደዚህ አይነት በእግር ኳሱ በኩል ከመንግስት በኩል ትልቅ ማበረታታትና ማነቃቃት አይቼ አላውቅም….. እንደ ፓርቲ ሳይሆን እንደ ግለሰብ ሁለቱንም ሰዎች አደንቃቸዋለሁ፡፡
Anonymous
October 16, 2013 at 9:29 am
thank u Dr
tesfu D
October 16, 2013 at 8:53 am
I proud of Dr. tewodros Adhanom u really finding more walyas strength..so keep it up leader
Koka
October 16, 2013 at 8:51 am
ዶ/ር ቴዎድሮስ በጣም ብልህና አርቆ አሳቢ የዘረኝነት አባዜ ያልተጠናወተዉ ባለስልጣን መሆኑን እኔምበቅርብ አዉቀዋለሁ:: ስለዚህ ልንኮራበት ይገባል:: ሰይድ ኪያር እና መሰሎቹ ግን የኢት/ን እግር ኳስ ማጥፋት እንጂ የተሻለ ስራ ስትሰሩ አትታዩም:: ከስንት ዉጣዉረድ በኋላ ለዚህ ያበቃንን አቶ ሰዉነትን ቢሻዉን እንደዚህ ስትንቅ ግን ትንሽ እንኳን አይሰማህም? ቡልሽት!!!
Anonymous
October 16, 2013 at 8:46 am
GOD BLESS U,D/R TEWODRS
Anonymous
October 16, 2013 at 8:00 am
O my GOD Dr Tewodros ‘
Anonymous
October 16, 2013 at 7:33 am
wow wow wow!!!!!!!!!!!!!!!!!!!!!!!!!!!!!!
Dr.Tewodros smart leader God bless u!!!!!!!!!!!!!!!!!!!!!!!!!!!!!!!!!!!!!!!!!!!!!!!!!!!!!!!!!!!!……………………………………..
Anonymous
October 16, 2013 at 7:25 am
ሁሌም አድናቂዎት ነኝ ረጅም እድሜና ጤና!!
Anonymous
October 16, 2013 at 7:18 am
you r one of wonderful lieder i my opinion u r so optimistic from the dead one life less party but we got u pls come to minister because it is ur place, pls keep it up your commitment, wish u long life love uuuuuuuuuuuuuu
Anonymous
October 16, 2013 at 7:11 am
ማህበራዊ….
HABTAMU
October 16, 2013 at 7:04 am
I am happy in this idea. Good luck 4 walya!!!!!!!!!!!!!!!
lukas
October 16, 2013 at 6:42 am
ከዘመኑ የኢትዩጵያ መሪዎች ሁሉ አብልጨ ለምዎድዎ ዶ/ር በየቀኑ የሚሰሩትና የሚያደርጉት ነገር በጣም ያስደስተኛል… ለቀጣይ ኢሀዴግ ኢትዩጵያን እንዲመራ ፈጽሞ አልፈልግም! ነገር ግን እርስዎ ጠቅላይ ሚኒስትራችን ሆነው በነጻነት የራስዎን ፍላጎትና እውቀት መጠቀም የሚችሉ ቢሆን ለቀጣዩቹ 30 ዓመታትም ቢሆን ኢህዴግ ኢትዩጵያን ቢገዛ አልቃዎምም…! መማር ጥሩ ነው እውቀትም ሀብት ነው ይህ ደግሞ ለሃገር እድገትና ልማት ስናውለው ለመንፈስ እርካታ ለወገንም አለኝታ ነው፡፡ እርስዎ በእኔ እምነት ጥሩ መሪ መሆን ይችላሉ በጥላቻ ሳይሆን በፍቅር አሸንፈውናል፡፡ ጸባይዎን ፈጣሪ አይቀይረው ጤናዎን፣ መልካሙን አዕምሮና እረጅም እድሜ ይስጥዎ!
jappy worku
October 16, 2013 at 6:31 am
I am proud of waliya team and foreign minister Dr Tewdrus adhanos
milliyo
October 16, 2013 at 6:23 am
am not impressed on Dr. Tewodros Adhanos commitment, because he has done common every citizens should have done. rather we all look at to our National team and gave constructive idea. while we feel normality as of our foreign affair minster.
Sammy
October 16, 2013 at 6:20 am
I like his motivation,Tewodros is trying his best. But I have a question on Sewinet Bishaw, he doesn’t like to change his tactics and squad. he has told so many times to include skill full midfielders but he resist.He doesn’t accept the current players performance.The only good thing of him is that, he is psychologically strong but that by itself is not worth enough.We need to say goodbye to more than 5 players from the current squad including 3 goal keepers.What about these sleepy silly goal keepers,they shouldn’t be there at all….find some new active keeper like Robert of St.george.
Zebenay workneh
October 16, 2013 at 6:20 am
Oh this is what an inspirational comment from Dr Tedross, Gedion is an out standing player so we should enquire him to be part of our national team.
Anonymous
October 16, 2013 at 6:17 am
Thanks Dr Tewodros go on it is nice Idea!!
Anonymous
October 16, 2013 at 6:01 am
hulegeb
Anonymous
October 16, 2013 at 5:57 am
Nice idea
ayele endshawu
October 16, 2013 at 5:52 am
ሊመሰገን ይገባዋል ዳ/ር
Anonymous
October 16, 2013 at 5:34 am
በጣም እናመሰግናለን ዶ/ር ቲዎድሮስ እንደዚህ አይነት ምክርህን ለ ስ/ፌደሬሽኑም ብትለግስ ለጀርመን ከ 20 ዓመት በላይ ሳይጫወት ለማምጣት ቢጥሩ…gedion
Anonymous
October 16, 2013 at 1:31 am
Amen!!!!!!!!!!!!!!!!!!!!!!
Temesgen shomoro
October 15, 2013 at 10:26 pm
I proud on Dr.Tewdros as one Walya team member.
Anonymous
October 15, 2013 at 10:02 pm
Thank you!,Dr.Tewdros for your being part of our football reviva.
zola
October 15, 2013 at 8:15 pm
wow Dr.Tewodros smart leader God bless u
Henok Efrata Efrata
October 15, 2013 at 8:12 pm
ሊመሰገን ይገባዋል ዳ/ር
a
October 15, 2013 at 5:47 pm
Nice idia
Yohans barak
October 15, 2013 at 5:47 pm
Always walya! Walya has the strong ability that it brings the aprciation of world audiances and football lovers. Ethiopia or walya 100% wins Nigeria before the cameroons pig discrimnate wit his continues yelew cards and lie the truth of our goals!
bereket hailgeorgis
October 15, 2013 at 4:50 pm
nice……………
assistant sergent dawit
October 15, 2013 at 4:32 pm
i know he is the real diplomat doctor tewodros. really i apprecait what u r doing. im proud of u doctor.
Anonymous
October 15, 2013 at 3:02 pm
be doc tegbar koraw serachewen behulu zerf eyeseru endale yameleketal bravo doc
Anonymous
October 15, 2013 at 1:19 pm
But i wish Dr. Tewodros , do what he supposed to do , pushing the Government to build a new stadium, its a shame to have a poor stadium , which was built 50 yrs before !, … though I appreciate his follow up of Waliays !
Dave
October 15, 2013 at 1:18 pm
But i wish Dr. Tewodros , do what he supposed to do , pushing the Government to build a new stadium, its a shame to have a poor stadium , which was built 50 yrs before !, … though I appreciate his follow up of Waliays !
አይኔ
October 15, 2013 at 12:23 pm
በመጀመሪያ ዶ/ ር ቴዎድሮስ ከበፊት ጀምሮ በጎሰኝነት ያልጎደፈ እውነተኛ ሀገሩን የሚወድ ተላቅ ሰው መሆኑን በአንድ አጋጣሚ በቅርበት አይቼው ተገንዝቤያለሁ እናም ሰዉየዉ ላገሩና ለህዝብ ወገናዊ በመሆኑ የበለጠ ነገር እንጠብቃለን ።እድሜ ይስጥህ ።
yoftahe fekadu
October 15, 2013 at 12:10 pm
good to hear from u gedion
Anonymous
October 15, 2013 at 11:58 am
good adia
Anonymous
October 15, 2013 at 11:13 am
10q D.tedros adhanom lesport yalehn amelekaketna lehzbh yaleh fckr hulyem enadenckhalen!!!
Gelchuu debeso
October 15, 2013 at 10:58 am
Llemin mahalu meda bado hone
Cool Head
October 15, 2013 at 10:17 am
Seido, I and so many soccer fans in Ethiopia used to love & respect you. But these days, you’re becoming completely non-sense. Leave Coach Sewunet alone. It’s people like you who have been like a CANCER to Ethiopian football for several years. Sewunet has changed that; he has completely shunned destructive people like you. We know that you recently had an altercation and physical fight with your own colleague Yonas at ETV because of your erratic behavior and stand. Get a life… we detest you from now onwards. You’re stinky. አሁንስ ገማህ፣ ሰነፈጥክ::
AMEHA ZEWUDIE
October 15, 2013 at 10:17 am
I am proud of waliya team and foreign minister Dr Tewdrus adhanos .we hope that both gedion and amin will play soon for their countries. the couch sewunet bishew should give thier ear to the large peoples of ethiopia. they should not reject thed decision of others like emperers.
Cool Head
October 15, 2013 at 10:11 am
Saido, I and so many soccer fans in Ethiopia used to love & respect you. But these days, you’re becoming completely non-sense. Leave Coach Sewunet alone. It’s people like you who have been like a CANCER to Ethiopian football for several years. Sewunet has changed that; he has completely shunned destructive people like you. We know that you recently had an altercation and physical fight with your own colleague Yonas at ETV because of your erratic behavior and stand. Get a life… we detest you from now onwards. You’re stinky. አሁንስ ገማህ፣ ሰነፈጥክ::
yacob
October 15, 2013 at 10:01 am
Seid bizu gize yemititsifachew negeroch yimechugnal. Gin ke Africa wancha jemro budnu yemehal meda fetari techawach chigir alebet tilaleh,,eshi enismama besu, eski ante limeretu yigebal yemitilachewun techawachoch tikes, kene miknyatuna statisticsu,,alebelzia zim bilo endezih ashmur eyetenegageru menoru fayda yelewum.
tesfalem
October 15, 2013 at 9:40 am
hi Dr. thanks for everything , God help you ……….
Lijalem Mulusew
October 15, 2013 at 9:37 am
We should be proud of not only to have such brothers in abroad, but also to the value that Dr. Theodros gives to the Ethiopian foot ball. I hope our beloved brothers Gedeon and Amin Ascar, to be to be proud of being Ethiopian and contribute with all what they can and have!!
Long Live to Ethiopia, the figure of all Africa!!!
Anonymous
October 15, 2013 at 9:25 am
Dr. I thank you. God Bless you, your family and your COUNTRY.AMEN!!!
Anonymous
October 15, 2013 at 8:56 am
our couch Mr.Sewunet Bishawu has did mistake. Why he change Adane? he is playing like RONI. he has power as much as possible. when he off have u try to see his face he was not happy. I seen Omar activities but it is some how. that referee also kill as
Fitsum
October 15, 2013 at 8:38 am
Thank you for D/r Tewodros for concerning as such.& please give the chance for sewnet b/c he knows what he did.
Anonymous
October 15, 2013 at 8:32 am
Dr Tedros is nice person with good caliber. He can change things as he has done on the health sector. Sewnet is the best coach we has seen so far in Ethiopia. No one can deny that. Saied Kiar you are losing the respect of the people. You will soon lose your followers and outcasted…. don’t forget this …. PESSIMIST
miki
October 15, 2013 at 7:37 am
betam des yilal endezih lehager liyu simet yalachewn balesiltanatn egizabher yabzalin
ewnet
October 15, 2013 at 7:31 am
ato saied…tinish alabezahwm ? tiba tibo techawto kemeshenef, gegmo mashenef yishalal. That’s what we all learned on sunday. Yetekatelnewm eko leza new. You have an agenda…make your own team and let’s see how far you can go.You are instead trying to destroy what the coach has built.
Elias Ashine
October 15, 2013 at 6:58 am
we all consider the man as our icon coz he contributed a lot to health coverage in the country while he was health minister. he is so special in every aspects. i personally admire the man in areas of politics social affairs and the like.
Bayu
October 15, 2013 at 6:57 am
God bless Ethiopia,i proud of Waliyas and i would have appreciate this man.
bethelhem
October 15, 2013 at 6:26 am
wow proud of Tehodrose adhonem i wish along time GOD Bless Ethiopia
Anonymous
October 15, 2013 at 6:08 am
I’ve a special place for Waliyas. I hope Gedian will be someone in the world stage. May be like Macy. I do not know Amin but I’m glad to hear about him. However, the comment about the foreign minister is a bit exaggerated. Because, reaching out to citizens should be duty of people in power. He didn’t do something special. I would have appreciate this man should he react in such a way when Ethiopians in the gulf or Yemen would suffer. I don’t think so.
Abraham
October 15, 2013 at 5:40 am
seid please dont make me lough in the middle of the night…lol