Connect with us

Opinions

[የግል ምልከታ] የዘረኝነት ሀሳብ ጽዳት ዘመቻ ወቅታዊ ነዉ

Published

on

Addis Ababa Steet Cleaning - 3

ከአዲስ ካሳሁን

“ጡ- ጡ- ጡ- ጡ- ጡ – ጡ -ጡ -ጠ- የከተማ ፅዳት የአዲስ አበባ ጽዳት” አሉ ጋሸ አበራ ሞላና ወዳጆቹ በአንድ ወቀት አዲስ አባባን ከቆሻሻ ለመታደግ፡፡ በሌላ በኩል ደግሞ በአንድ ወቅት የሊቢያዉ ፕሬዘዳንት የነበሩት መሐምድ ጋዳፊ የአፍሪካ ህብረትን ወደ ሊቢያ ከተማ እንዲዛወር በጀመሩት እንቅስቃሴ “በዚች በቆሸሸች ከተማ እፍሪካ ህብረት እንዴት ይቀመጣል ስለዚህ ጽ/ቤቱ ሊቢያ ይሁን” ብለዉ ሃሳብ ሲያቀርቡ ኢተዮጵያን ለ 20 ዓመት ያህል የመሯት አቶ መለስ ዜናዊ “ከተማችንንስ እናፀዳታለን የማይፀዳዉ ግን ቆሻሻ ጭንቅላት ነዉ” ብለዉ ጥሩ መልስ ሰጥተዉልን ነበር፡፡ ሁለቱም ዛሬ በሂወት የሉም፡፡ ለዝች አጭር ህይወት መጥፎ ማሰብ ምን ይሰራል?

ታዲያ ዛሬ ልክ እንደ ጋሸ አበራ ሞላ የጽዳት ዘመቻ ሁሉ ጡ- ጡ- ጡ- ጡ- ጡ- ጡ- ጡ- ጡ የዘረኝነት ሀሳብ ጽዳት ዘመቻ ቢባል ወቅታዊና ትክክል ነዉ፡፡ ፌስቡክ መጠቀም ከ ጀመርኩ ዓመታት አልፈዋል፡፡ በነዚህ ጊዚያቶች ከፌስቡክ በዙ የሚባሉ ቁመነገሮችን አግኝቻለሁ፡፡ በዘመናዊ ቴክኖሎጅ ኢንፎረማሽን ማግኘት ነገሮችን ፈጣን ከማደረጉ በተጨማሪ እሩቅ ለሩቅ ያሉተን ሰዎች በአንድ መደረክ ላይ ያገናኛል፡፡ ግን በሌላ በኩል ፌስቡክና የተለያዩ ማህበራዊ ድህረ ገፆች በአንዳንድ ሰዎች በአሉታዊ መልኩ የሚጠቀሙባቸዉና እሾክ የሚዘሩባቸዉ ትላልቅ መሬቶች ሆነዋል ቢባል የተጋነነ አይደለም፡፡ ስልችት እሰከሚል ድረስ እና ማየትና ማንብብ እስከሚያሰጠላ ድረስ በነዚሀ አዉድማዎች ላይ ለትዉልድ የማይጠቅሙ የነገር አንክርዳዶች ይወቃሉ ይደቆሳሉ፡፡

በአብዛኛዉ እነዚህን ድህረ ገጾች የሚጠቀመዉ ህብረተሰብ “የተማረ“ የሚባል ነዉ፡ ግን ከተማረ የማይጠበቅ ለሃገር እና ለህዝብ አንድነት የማይጠቅም የዘረኝነት እና ጎጠኝነት ወሬ አናፋሹ እሱ እራሱ የተማረ ተብዬው ሲሆን ከመረበሽም በላይ ትልቅ የጭንቅላት ኪሳራና ዝገት መሆኑ ግልፅ ነዉ፡፡ ዛሬ በዘመነ ግሎባላይዜሽን ስለ ቀበሌ እና ጎጥ እያወሩና ጡሩንባ እየነፉ ሰላም የነበረዉን እና የሚፋቀረዉን ህዝብ ሆድና ጀርባ እንዲሆኑ ማደርግ ምናልባት ጠለቅ አድርጎ ቢታስብ ሰይጣናዊ ክፍ ሰራ ነዉ፡፡ ጭንቅላት ያለዉና ቆሞ የሚሄድ ሰዉ በዘር እና በቋንቋ አለያይቶ ምስኪኑን ህዝብ ምንም ወደ ማያዉቀዉ የዘረኝነት ጭለማ ዉስጥ ጎትቶ ማሰገባት ትልቅ የታሪክ ኪሳራም ነዉ፡፡

ብዙ የሌላ ሀገር ዜጎች ፌስቡክ ጋደኞች ይኖሩናል፡ ግን እነዚህ ሰዎች ይህንን ድህረ ገጽ የሚጠቀሙበት በአብዛኛዉ ለ አዎንታዊ ነገር ነዉ፡፡ ምናልባት ሀገራቸዉ ዉስጥ ጎሳና የተለያዩ ቋንቋ ተናገሪ ህዘብ ባለመኖራቸዉ አይመስለኝም ግን ይህ ነገር ለነሱ ከሀገር ተሻግሮ ትልቅ የመነጋገሪያ ነጥብ ሰላልሆነ ነዉ፡፡ በተቃራኒዉ ወደ እኛዉ ሀገር ተጠቃሚ ስንመጣ በዙ በጣም በዙ የዘረኝነት አካዉንት፤ፔጅ እና ግሩፖች ተከፍተዋል፡፡ አንድነትን የማይታያቸዉና ማባላት ስራቸዉ የሆነ የዘረኝነት መርዝ ተፊዎች በኛ ሀገር ነዉ ሽርጉድ የሚሉት፡፡

ግን አሁን ስንት የሚወራና የሚሰራ ነገር እያለ፡ ከሰዉነት ደረጃ ወረድ ብለን ከብሄራዊነት ይልቅ ሰለ ቅርነጫፎቹ ብሄር እያወሩ እኔ የእገሌ ጎራ ልጅ ነኝ ምናምን እያልን መቀባጠሩ ምን ይጠቅማል? ደግሞ በእንደዚህ አይነት እንቅስቃሴ የትኛዉ ሀገር ነዉ ያደገዉ? ገና በልተን ሳንጠግብ ስለ ጥቃቅን ነገሮች ስናወራ ሆዳችን ይሞላ ይሆን? ብዙ ለሀገርና ለወገን የሚጠቅም ነገር መስራት እየተቻለ በጥቃቅን ነገሮች ላይ ትኩረታችንን ሰጥተን በዚህ በ21ኛዉ ክፍለ ዘመን የዘቀጠ ሃሳብ ይዞ መራመድ ጨለምትኝነትአባ ጠባብነት ይመስለኛል፡፡

ስራቸዉ፤ ግባቸዉ ፤ እንዲሁም መተደዳሪያቸዉ ይህ ጭፍናዊ የማለያየት ፕሮፖጋንዳ የሆነ ግለሰቦች መኖራቸዉ የማይካድ ሃቅ ቢሆንም፡ የሚያሳዝነዉ ግን ጥራዝ ነጠቅ እና በ “አሉ፤ አሉ” መንፈስ የነሱን ፍልስፍና አናፋሹ መብዛቱ ነዉ፡፡ አንዳንዶቹ በ ፖለቲካው ዓለም ኪሳራ ሲያጋጥማቸዉ ህዝብን ከህዝብ አባልቶ ቤተ መንግሰት ለመግባት የሚያደርጉት የዘረኝነት የማያዋጣ የጭለማ ሩጫ ነዉ፡፡ እነሱ ለጥቅማቸዉ ነዉ። አራጋቢዉ ምን ለማግኘት ነዉ?

ዘረኝነት በምድር ሆነ በሰማይ የሚያስጠይቅ ዲያብሎሳዊ አስተሳሰብ ነዉ፡፡ አንድ ሰዉ እኔ ከ እነ እገሌ ብሄር ልወለድ ብሎ ፈጽሞ የተወለደ የለም፡፡ ሰዉ በሰዉንቱ እንጂ በሚናገረዉ ቋንቋ እና ከየት መጣ ተብሎ መገልል የለበትም፡፡ ስለዚህ የፌስቡክ ብሄረተኞች መጀመሪያ እሰኪ በቀን 3 ጊዜ ሰለመብላት እንማከር ቀጥሎ ሌሎች ጎደሎቻችንን እንሙላ፡፡ በሰዉ ሃገር ላይ ወንድም እና እህቶች ህይወታቸዉ በመንግደ ላይ ሲረግፍ እያየን እኛ እዚሀ የትርኪምርኪ እሳት እናነዳለን፡፡ እናስብብት አንድነት እንጅ መለያየት አይጠቅመንም!!!
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር!!!

News

EthioTube ወቅታዊ – ኢትዮጵያ እና አሜሪካ ወዴት? | Ethiopia and United States Relations

Published

on

hqdefault
Continue Reading

Articles

የ40 /60 ፈተና – በአርኪቴክት ዮሐንስ መኮንን

Published

on

By

40-60 Buildings in Addis Ababa

40-60 Buildings in Addis Ababa

አዲስ አበባ ከተማን ሰንገው ከያዝዋት ችግሮች መካከል የመኖሪያ ቤት ችግርን የሚስተካከለው ያለ አይመስለኝም፡፡ ዜጎች ከግማሽ በላይ የሚሆነውን ገቢያቸውን ለቤት ኪራይ ስለሚያውሉ ቀጣይነት ያለው ሃብት መፍጠሪያ አቅም ነስቷቸዋል፡፡ የኽም ኑሮአችንን በመከራ የተሞላ አድርጎብናል፡፡ ይኽንን ችግር በዘላቂነት ለመፍታት መንግስት የቤቶች ግንባታ ፕሮገራም መንደፉ የሚያስመሰግነው ቢሆንም ወደ መሬት ያወረደበት መንገድ ግን አነጋጋሪ ሆኖ የሚቀጥል ይመስለኛል፡፡

ከነኚህ ፕሮግራሞች አንዱ የሆነው በተለምዶ 40/60 በመባል የሚታወቀው የቤቶች ግንባታ በመሠረታዊ የዲዛይን ስህተቶች የተሞላ እና ስህተቶቹን ለማረም የተኬደበት መንገድም ሌላ ተጨማሪ ስህተት የፈጠረ ይመስለኛል፡፡ ለመሆኑ ስህተቶቹ ምንድናቸው?

1) ፕሮግራሙ እና የተሠሩት ቤቶች አይተዋወቁም፡፡ ዜጎች ‹‹ታገኙታላችሁ›› በተባሉት አጠቃላይ የወለል ስፋት መሠረት በባንክ መቆጠብ መጀመራቸው ይታወቃል፡፡ ይሁን እንጂ በጥድፊያ እንዲገነቡ የተደረጉት አፓርታማዎች ግንባታቸው ከተጋመሰ በኋላ የወለል ስፋታቸው የተዛነፈ መሆኑ በመታወቁ እንደምንም ተብቃቅተው መንግስት ከዜጎች ጋር በተፈራረረመው ውል መሰረት እንዲስተካከሉ ለማድረግ ጥረት እየተደረገ ነው፡፡ (በአጭሩ ለማስረዳት ጃኬት ለማሰፋት ለተዋዋለ ደንበኛ ካፖርት ከሠፉ በኋላ ስህተቱን ለማረም ካፖርቱን በመቆራረጥ ሌሎች ጃኬቶች ለማውጣት እንደመሞከር ያለ ነው፡፡ከካፖርት ጃኬት ይወጣ ይሆናል፡፡ ግን የተጨማደደ እና የተጣበበ መሆኑን መቀበል ይኖርብናል፡፡ በ40/60 እየሆነ ያለውም ይኼው ነው፡፡)
2) የአደጋ ጊዜ ማለጫ የላቸውም፡፡ ግንባታቸው ከተጋመሰ በኋላ የታወቀውን የአደጋ ጊዜ ማመለጫ ደረጃ ቀድሞ ባልታሰበበት ሁኔታ ‹‹እንደምንም ብላችሁ አንድ ጥግ ፈልጉለት›› በማለት ለመፍታት መሞከር መፍትሔውን ሰንካላ ማድረጉ አይቀሬ ነው፡፡
3) የቆሻሻ ማስወገጃ ሊኖራቸው ይገባ ነበር፡፡ 12 ፎቅ ተገንብቶ ነዋሪዎች የሚያስወግዱትን ደረቅ ቆሻሻ በፌስታል ቋጥረው እንዲወርዱ ማሰብ ተገቢ አይደለም፡፡ በቀላሉ የቆሻሻ ማንሸራተቻ (Trash shooter) ማሰብ ይገባ ነበር፡፡ 
4) ለሁሉም በሽታ አንድ ክትባት! እንኳንስ ህንጻ ዛፍ እንኳን ሲተከል ከቦታ ቦታ የተለያየ እና ተስማሚ ዓይነት ይመረጣል፡፡ አሁን የሚሠሩት አፓርታማዎች ግን ለሁሉም የንፋስና የፀሐይ አቅጣጫዎች፣ ለአፈር እና ለድንጋይ ዓይነቶች እንዴት አንድ ዲዛይን ይሠራል? ይህን ያህል ጥድፊያስ ም ለማትረፍ ነው?
5) ንድፉ አያምርም፡፡ ይህን የመሰለ ከፍተኛ በጀት እና ጉልበት የሚፈስበት ብሔራዊ ዕቅድ በቂ የባለሙያዎች ክርክር እና ጥናት ሳይደረግበት በጥድፊያ በተሞላ ውሳኔ ወደ ተግባር መገባት አልነበረበትም፡፡ ሲሆን ሲሆን ከፍተኛ አማካሪዎች የተሳተፉበት የዲዛይን ውድድር ተደርጎ የተሻለው ሊመረጥ ይገባ ነበር !

የእነኚህ ሁሉ ችግሮች ምንጮች ሁለት ናቸው፡፡ ጥድፊያ እና አነስተኛ ግምት ! መፍትሔው ከዚሁ ይመነጫል፡፡ ሰከን ብሎ ማሰብ እና ተገቢው ትኩረት! ሀሳቡ የፓርቲ ሳይሆን የመላእክት እንኳን ቢሆን አፈጻጸሙ ከተበላሸ ፈተናውን ወደቀ ማለት ነው ፡፡

 

Source: አርኪቴክት ዮሐንስ መኮንን

Continue Reading

Keenya ስለእኛ

የወገኔ “Amarika”

Published

on

flag2

flag2

ያገሬ ሰዉ ፤ ከቀየዉ ቢሻለኝ ቀን ቢያወጣልኝ ብሎ ነፍሱን ሸጦ የፈለሰበትን ምድር ስም ተይብ ቢባል የሚያስፍራቸዉ ፊደላት ናቸዉ፤ Amarika….ብዬ ብጀምር ማጋነን ይሆንብኛል :: ወገኔ በ Amarika ድህነትን ሊያራግፍ ሀብት ሊሸምት ግዞትን አሽቀንጠሮ ነፃነትን ሊሸክፍ ተስፋን ሰንቆ ከተተ በAmarikaም ከተመ፡፡ ከወገን ኖሮ ከመራብ በሀገር ኖሮ ከመሰደብ በመሸበት አድሮ ከባየተዋር ምድር ጥጋብ እና ክብርን ሽቶ ሮጠ፤ ተሰደደ፡፡ ሆነለት፡፡ የቀን ሶስት ሩብ እየለፋ ከምን እንደተሰራ በማይታወቅ እንጀራ ሆዱን እየነፋ እነ እማማን እነ አባባን እነ ኩቺን እነጢሎን ዶላር ያስመረዝራል፤ ቀን ያወጣላቸዋል፤ ከጎረቤት በላይ ያደርጋቸዋል፡፡ እሱ የመኪና ተራ እያስጠበቀ እነ እማማን እነ ጢሎን ባለጋቢና ያደርጋቸዋል፡፡ ሳይማር አሜሪካ የላከዉን ህዝብ ሳይማር ወግ ያስተምረዋል፡፡ ለነ ኩቺም ያሜሪካ ወንድማቸዉ ከእግዜር በታች ከኦባማ ጎን ነግሶ የትንሽ ስራ መራቂያ ያሜሪካ መናፈቂያ የጎረቤት ማስፈራሪያ ሆኖ ይኖራል፡፡ ወገኔም ይህን ያዉቀዋል፤ ጎረቤታቸዉን እነ ቡለቲን አፍ ማስያዙ ያኮራዋል፡፡ ስራዉን ኑሮዉን ደብቆ የስራ ትንሽ እንደሌለ ቤተሰቡን ይመክራል፡፡ ስለወገኔ ኑሮ ዝርዝር ሁኔታ በስልክም ሆነ ባካል ከሱ ጋር መነጋገር አያስፈልግም የሴት ዕድሜ የሱ ስራ አይጠየቅማ፡፡ የቤቱ ትልቅነት የመኪናዉ ዘመናዊነት በአሜሪካዊዉ ወገኔ በዝርዝር ሊወሳ ይችላል፡፡ ይህ ማለት ግን የሱ ቤት የሱ መኪና ነዉ ማለት ላይሆን ይችላል፤ አይጠየቅም፡፡

ነገ ያቺ ሙሉ ቀን ስትመጣ ከስምንት ሻንጣ ጨርቅ እብድ ከሚያክል ስልክ እና የአሜሪካ ሰንደቅ ካለበት ካኒቴራ ጋር ቦሌ ይደርሳል እነኩቺም ካስራ አምስት ዘመድ አዝማድና ዳጎስ ካለ ብድር ጋር ይቀበሉታልእንኳን ላፈርህ አበቃህከዛማ የአንድ ወር ቆይታው በፌሽታና በአሜሪካ ኑሮ ትረካ የተሞላ ይሆናል፡፡ እንደዛ ሲሰራ ሲለፋ ለኖረው ወገኔ መዝናናት ሲያንስ ነው::

ችግር፤ ተስፋ ማጣት፤ ፖለቲካ፤ ጭቆና…ብዙ ብዙ ምክንያት ከምንወዳት ሀገራችን ያፈናቅሉናል፤፤ አሜሪካ እንዲሁም ሌሎች የሰለጠነዉ አለም የተሻለ አማራጭ ሆነዉ እናገኛቸዋለን፡፡ ለማንኛዉም ምክንያት ይሁን ሀገር ቀይሮ መኖር የግለሰብ ዉሳኔ ነዉ፡፡ ሊከበርም ይገባዋል፡፡ ይህ እንዳለ ሆኖ ግን የምንሄድበትን ቦታ፤ የምናልመዉን ኑሮ በሚገባ መረዳት ቅድሚያ ሊሰጠዉ የሚገባ ጉዳይ ይመስለኛል፡፡ የተሻለ ለዉጥን መፈለግ ድንቅ ነዉ፡፡ ለመለወጥ ግን ማወቅ ይቀድማል፡፡

አሜሪካን በእንግሊዝኛ ተይብ ቢባል አብዛኛዉ በትክክል እንደሚፅፍ ተስፋ አደርጋለሁ፡፡ ነገር ግን ምን ያህሉ ሊኖርባት የመረጣትን ሀገር ቋንቋ ለመግባቢያ እንኳን በሚጠቅም ደረጃ ያዉቃል ብትሉኝ በጣም ጥቂቱ ይሆናል መልሴ፡፡ የተወሰኑ ቃላትን በአሜሪካዊያን ዘይቤ ይጠራ ይሆናል፡፡ ነገር ግን አንድ ሙሉ አረፍተ ነገር በተሟላ መልኩ ቀምኖ አያቀርብም፡፡ በዚህ አይነት ሁኔታ ታዲያ ከታክሲ ሹፌርነት እና ከመኪና ጠባቂነት ያለፈ ህልም እንዴት ይኖረዋል፡፡ ቀን ሲሞላ ተመልሶ ወይንም በስልክ ስለአሜሪካ ሰማይ ጠቀስ ህንፃዎች እና ህዝብ ገድል ከማዉራት ያለፈ ህልም ልንሰንቅ እንችላለን? ሁሌ ከህንፃዉ ዙሪያ ያሉትን ጥቃቅን ስራዎቸን ሰንሰራ መኖርን ከማለም፤ ለወገናችን የተሳሳተ(ያልተሟላ) መረጃን ከመስጠት፤ ራሳችንን አለአግባብ ከመኮፈስ አልፈን ህንፃዉ ዉስጥ ካሉት ሰዎች ራሳችንን እንደአንዱ የማየት፤ ህንፃዉንም ሆነ ዉስጡ ያሉትን ንግዶች (አገልግሎቶች) የራስ የማድረግ ህልም ቢኖረን ይበዛብናል? አይመስለኝም ከአንድ ድሃ የአፍሪካ ሀገር የሄደ ስደተኛ ልጅን መሪዋ አድርጋ ለመሾም የፈቀደች ሀገር እኛ ከተጋን ትምህቱንም ሆነ ሀብቱን አትከለከንም። ለዚህ ደግሞ ማሳያ የሚሆኑ ወገኖቻችን በዙሪያችን ሞልተዉናል።

ነገር ግን መጀመሪያ መማር ማወቅ ለመለወጥ መዘጋጀት ይቀድማል። አሁን ምንሰበስበው ስምንትና ዘጠኝ ዶላር ለነገው ህልማችን ግብዐት እንጂ ራሳችንን ማታለያ የሀገር ቤት ወገናችንን ማደናበሪያ መሳሪያ መሆን የለበትም።

በነገራችን ላይ ይህ ጽሑፍ በትምህቱም ሆነ በንግዱ ለራሳቸው ስኬታማ ለወገን ኩራት የሆኑትን አይመለከትም። እነሱ በተቃራኒው ለነኩቺ ወንድም ወገኔ ምሳሌዎች ናቸው። በል እንግዲህ ወገኔ ወደ Amarika ስትመለስ መዝገበ ቃላት ስንቅህ ይሁን ከዛ ለሚጥለው ደረጃ ስትበቃ እንማከራለን:: ደህና ሰንብቱ።

Continue Reading

Trending