Articles
የዛሚ ሬዲዮ ሚሚ ስብሃቱ በታሰሩት ጋዜጠኞች፣ በፕሬስ ነፃነትና ያለመረጃ በሚሰሩ ውንጀላዎች ላይ

03 May, 2014 | Written by አበባየሁ ገበያው እና አለማየሁ አንበሴ
የአለማቀፉ የፕሬስ ነፃነት ቀን በዛሬው እለት “Media freedom for abetter feauture` በሚል መሪ ቃል ይከበራል፡፡ ይህን ምክንያት በማድረግ በኢትዮጵያ የፕሬስ ካውንስል ለማቋቋም በሚደረገው ጥረት ተሣታፊ ከሆነችው ጋዜጠኛ ሚሚ ስብሃቱ ጋር ጋዜጠኛ አበባየሁ ገበያው እና አለማየሁ አንበሴ ስለሀገራችን የፕሬስ ተግዳሮች ስለ ካውንስል ምስረታው እና የተለያዩ ጉዳዮች ቃለ ምልልስ አድርገዋል፡፡
የአገራችን የፕሬስ ተግዳሮቶች ምንድን ናቸው ትያለሽ?
እንደ ኢንዱስትሪ ተግዳሮቶቹ ሁለት ናቸው፡፡ ውስጣዊም ውጫዊም ናቸው፡፡ የመገናኛ ብዙሃን ኢንዱስትሪው ራሱን በራሱ የሚቆጣጠርበትና ራሱን በራሱ የሚያሻሽልበት ስርዓት እስከ አሁን ድረስ መገንባት አለመቻሉ ከፍተኛ የማንነት ቀውስ ውስጥ መሆኑን ያሳያል፡፡ ብዙዎችን ለማስተናገድ፣ ብዙ የሰው ሃይል አቅፎ ለመንቀሳቀስ፤ እንደሀገሪቱ ግዙፍነት፣ እንደ ህዝባችን ብዛት የተደራሽነት አቅም እንዲኖር የማያስችል ሁኔታ ነው ያለው፡፡ ሀገሪቱ ጥርት ያለ የሚዲያ ፖሊሲ የላትም፡፡ በሌሎች አገሮች መገናኛ ብዙሃን እንዲያብቡ፣ እንዲጐለብቱ ብዙ ድጋፍ ይደረጋል፡፡ ማተሚያ ቤቶች እንዲያቋቁሙ ሃሳብ ከመስጠት ጀምሮ በፓርላማ አማካኝነት ከመንግስት ገንዘብ የሚመደብበት አሰራር አለ፡፡ ለምሳሌ በአገራችን የማተሚያ ቤት ችግር አለ፡፡ የእሁዱን ጋዜጣ ረቡዕ እያነበብን ነው፡፡ እነዚህ ሁኔታዎችን ነው እንደ ተግዳሮት የምናስባቸው፡፡
ከ10 ዓመት በፊት ከነበረው ጋር ሲነፃፀር አሁን ያለው የፕሬስ ደረጃ ምን ይመስላል፡፡ ያኔ በመቶዎች የሚቆጠሩ ጋዜጦች ይታተሙ ነበር፡፡ አሁን በጣት የሚቆጠሩ ናቸው ያሉት….
ከአስር ዓመት በፊት የነበረው የህትመት መገናኛ ብዙሃን ብዛት እንጂ ጥራት አልነበረውም፡፡ መፃፍ የቻለው ሁሉ የፈለገውን የሚጽፍበት ጊዜ ነበር፡፡ ከብሔር ብሔረሰቦች ጀምሮ ግለሰቦች የሚብጠለጠሉበት፤ አንድ ገፅ እንኳን ትክክለኛ ዜናና መረጃ ተፈልጐ የማይገኝበት የህትመት መገናኛ ብዙሃን ነበር፡፡ መገናኛ ብዙሃን ህዝብን መለወጥ አለባቸው፡፡ የህዝብን ህይወት ለማሻሻል ትልቅ አስተዋጽኦ ሊያደርጉ ይገባል፡፡ የሰው ልጅ የመገናኛ ብዙሀንን የፈጠረው ለሰዎች የተሻለ ህይወት ለማምጣት ነው፡፡
ከዚህ አንፃር ሲታይ ከ10 ዓመት በፊት የነበሩት ምንም ዓይነት ዓላማ ያልነበራቸው፣ እንደውም ህብረተሰቡን ብዥታ ውስጥ የሚከቱ፣ ምንም ዓይነት መረጃ የማይሰጡ፣ በአሉባልታና በወሬ የተሞሉ ነበሩ፡፡ ከአስር ዓመት ወዲህ ያሉት ቁጥራቸው ቢያንስም የጋዜጠኝነት ሙያን እየተገበሩ ነው እስከዛሬ የዘለቁት፡፡ በእርግጥ ከ10 ዓመት በፊት የነበረው ጊዜ የመገናኛ ብዙሃን እድገት አንድ ምዕራፍ ነው፡
ያንን አልፈን አሁን ሁለተኛው ምዕራፍ ላይ ነን፡፡ የመገናኛ ብዙሃን መርሆቻቸውንና ስነምግባሮቻቸውን አክብረው የሚንቀሳቀሱበት፤ መፃፍ የቻለ ሁሉ የፈለገውን የሚዘባርቅበት ሳይሆን ሙያተኞች ወደ ዘርፉ ገብተው የህዝብ ልሳንነታቸውንና አገልጋይነታቸውን በተግባር እያሳዩ ያሉበት ወቅት ነው፡፡ በአገራችን ያለውን የህትመት መገናኛ ብዙሃን ስንመለከት ምንም የለም ለማለት ያስደፍራል፡፡ የኤሌክትሮኒክስ የመገናኛ ብዙሃን በተወሰነ ደረጃ አድጓል፡፡ በህትመት የመገናኛ ብዙሃን ከብዛት ይልቅ ጥራቱ የሚታይበት ደረጃ ላይ ነው ያለው፡፡
የፕሬስ ካውንስል ለማቋቋም እንቅስቃሴ ስታደርጉ ነበር፡፡ ምን ላይ ደረሰ?
ጨርሰናል ማለት ይቻላል፡፡ በተቋሙና በሥነምግባር ደንቡ (በኮድ ኦፍ ኮንዳክቱ) ላይ የመጀመሪያ ዙር ውይይት አድርገናል፡፡ በቀጣይ ያለውን ሂደት ለመጀመር እየተዘጋጀን ነው፡፡ በቅርቡ አዲስ ነገር ይኖራል፡፡
የአለም የፕሬስ ነፃነት በሚከበርበት ዋዜማ 6 ጦማሪዎች (ብሎገሮች) እና 3 ጋዜጠኞች ታስረዋል፡፡ ዓለማቀፍ የጋዜጠኞች መብት ተሟጋቾች ኢትዮጵያ ጋዜጠኞችን በማሰር ከኤርትራ ቀጥሎ በሁለተኛ ደረጃ እንደምትገኝ ሪፖርት አውጥተዋል፡፡ በእዚህ ጉዳይ ላይ የአንቺ አስተያየት ምንድነው?
በመሠረቱ የጋዜጠኞች መብት ተሟጋች ነን ብለው የሚንቀሳቀሱ ዓለምአቀፍ ተቋማት ላይ እምነት የለኝም፡፡ ተዓማኒነታቸው የወደቀ ነው፡፡ የሚሠሯቸውን ስራዎች ስለማውቅ ነው፡፡ የሀገራችን ሁኔታም አልጋ በአልጋ አይደለም፡፡ ታሰሩ ስለተባሉት ሰዎች ጉዳይ ፖሊስን ጠይቀን አጣርተናል፡፡ “ከውጭ ሃይሎች ጋር እየተገናኙ በሀገሪቱ ሁከትና ብጥብጥ ለመቀስቀስ ሙከራ ሲያደርጉ ደርሸባቸዋለሁ” ነው ያለው ፖሊስ፡፡
በእርግጥ ጋዜጠኛ አይታሰርም፤ ነገር ግን ጋዜጠኛ አይታሰርም ሲባል ከህግ በላይ ነው ማለት አይደለም፡፡ ህግ መከበር አለበት፡፡ በተለይ ደግሞ አገርን አደጋ ላይ ሊጥሉ ከሚችሉ ነገሮች ከማንም በላይ ቀድሞ ዘብ መቆም ያለበት ጋዜጠኛው ነው፡፡ በዓለም የፕሬስ ነፃነት ቀን የተለመዱት ጩኸቶች ይኖራሉ፡፡ የዘንድሮው የሚከበረው በጣሊያን ነው፡፡ በዛ ቦታ ያ ሩጫ ሊኖር ይችላል፡፡ ግን መታወቅ ያለበት ማንም ቢሆን ጋዜጠኛም፣ ተራ ዜጋም፣ መንግስትም ቢሆን ከህግ በላይ አይደሉም፡፡ ነፃነት ከሃላፊነት ጋር ነው የሚመጣው፡፡
የሚፃፈው ነገር ምን ያስከትላል ተብሎ መታየት አለበት፡፡ ይሄ የሙያው መርህና ስነምግባር የሚያጐናፅፈው ክህሎት ነው፡፡ በእርግጥ ይህ ሁኔታ መፈጠሩ (ሰዎቹ መታሰራቸው) ደስ የማይልበት ሁኔታ አለ፡፡ በሌላ በኩል ደግሞ የማናውቀው ነገር አለ፡፡ ፖሊስ አለኝ የሚለውን ማስረጃና የፍርድ ቤትን ውሳኔ ማየት አለብን፡፡
በአገር ውስጥም ሆነ በውጭ የፀረ ሽብር ህጉ ጋዜጠኞች በነፃነት እንዳይሰሩ እንቅፋት እንደሆነና ሃሳብን በነፃነት የመግለጽ መብትን እየሸረሸረ ነው የሚል ወቀሳ እየተሰነዘረ ነው፡፡ በዚህ ላይስ ምን ትያለሽ?
ሽብር ኢትዮጵያ ብቻ ሳትሆን መላው ዓለም እየተጋፈጠው ያለ አደጋ ነው፡፡ ብዙ ሃገሮች የፀረ ሽብር ህግ አላቸው፡፡ የፀረ ሽብር ህጉ የተለየ ሆኖ ትኩረት የሚስበው የተወሰኑ ሲቪል መብቶችን ስለሚገድብ ነው፡፡ ይህ ደግሞ ለደህንነት የሚከፈል መስዋዕትነት ነው፡፡ በሰላም ወጥቶ ለመግባት፣ በሰላም ልጆችን ለማሳደግ ህዝቦች እንደዚህ አይነቱን ህግ የሚቀበሉበት ሁኔታ አለ፡፡ የመከላከል ህግ እኮ ነው! የጭቃ ሹም አስተሳሰብ ያለው ሹመኛ ያለአግባብ ሊጠቀምበት ይችላል፤ በተገቢው መንገድ ተግባራዊ ከተደረገ ግን አሸባሪዎች ፍንዳታ ከማድረሳቸው በፊት ይያዛሉ፡፡ አወዛጋቢ የሆነው የፀረ ሽብር ህግ፣ በተለያዩ ሀገሮችም አለ፡፡ በተወሰነ ደረጃ በህገመንግስቱ ውስጥ አይነኬ የሆኑት ሁሉ ይነካሉ፡፡ ይሄ ደግሞ ለመዳን ስንል የምናደርገው፤ የምንወስደው እርምጃ ነው፡፡ እኛም እንደባለሙያ መሳሪያ እንዳንሆን መጠንቀቅ አለብን፡፡ የምናገኛቸውን መረጃዎች ደግመን ደጋግመን ማረጋገጥ አለብን፡፡ መረጃ ስለተገኘ ብቻ አይደለም የምንጠቀመው፡፡ የፀረ ሽብር ህጉ ሃሳብን በነፃነት የመግለጽ መብት ላይ ጫና ይፈጥራል ብዬ አላምንም፡፡ ሃሳባችንን መግለጽ፣ ጉዳያችንን ማስተጋባት እንችላለን፡፡ እንፅፋለን እናነባለን፡፡ ከህጉ ጋር የምንጋጨው፣ ነፃ አውጭነት ወይም ፋኖነት ሲሰማን ነው፡፡ የእኛ ብዕር ዓላማ ደግሞ ፋኖነት አይደለም፡፡ ተነስ፣ ውጣ ታገል፣ ታሰር… ማለት የእኛ ስራ አይደለም፡፡ ይሄንን ሚዛናዊ አድርጐ የመሄድ ጥያቄ ነው፡፡ የፀረ ሽብር ህጉ የት ላይ ነው ቀጫጭን መስመሮች ያሉት የሚለውን እኛ ማወቅ አለብን፡፡
የመንግስት የመረጃ ስስት የፕሬሱን ዕድገት አቀጭጮታል የሚሉ ሃሳቦች ይሰነዘራሉ፡፡ በዚህ ሃሳብ ትስማሚያለሽ?
መረጃ የማግኘት መብትን በተመለከተ በህግ ተቀምጧል፡፡ ብዙ አገሮች እንደውም የላቸውም፡፡ ኢትዮጵያ የመረጃ ነፃነት ህግ አላት፡፡ ማህበረሰባችን የመጣበት ሁኔታ በራሱ መረጃ መስጠትን አያበረታታም፡፡ መረጃ መስጠት ግዴታቸው፣ ሃላፊነታቸው መሆኑን የማያውቁ የመንግስት ባለሥልጣናት አሉ፡፡ እንደማህበረሰብ ግልጽ አይደለንም፤ በጣም ዝግ ማህበረሰብ ነው፡፡ ያንን ዝግ ማህበረሰብ ነው ለመክፈትና መረጃ ለማግኘት የምንሞክረው፡፡ የኢትዮጵያ ጋዜጠኞች መደበኛ ስራቸው የምርመራ ጋዜጠኝነት (Investigative Journalism) የምንለው ነው፡፡ ምክንያቱም መረጃ ለማግኘት ብዙ ርቀት መሄድ ያስፈልጋል፡፡
የመገናኛ ብዙሃኑ አበቃቀልና አስተዳደግ ታሪክም ለዚህ የሚያመች አይደለም ይፈራል፡፡ መረጃ ሰጪው አካልና ጋዜጠኛው እንደ አጋር ነው መተያየት ያለባቸው፡፡ የምንሰራበት ማዕቀፍ ግን መረጃ መጠየቅና መስጠትን እንደ አይጥና ድመት የሚታይበት ነው፡፡ የህግ ማዕቀፉ ግን ተቀምጧል፡፡ ማንም የመንግስት ባለስልጣን መረጃ የመስጠት ግዴታ አለበት፡፡
በመገናኛ ብዙሃን አሰራር የዳበረ ባህልና ልምድ ባላቸው አገሮች፣ ምንም ቢፃፍ ማንም ዞር ብሎ አያያቸውም፡፡ ህብረተሰቡ የፀሐፊው እብደት ነው ብሎ ነው የሚያስበው፡፡ የመገናኛ ብዙሃንን እንደ ተፅዕኖ ፈጣሪ (ኦቶሪቲ) የሚወስድ እንደኛ ያለ ማህበረሰብ ውስጥ ሲኮን ነው ፍጥጫው የሚመጣው፡፡ “ተነስ…የማይነሳ ህዝብ ፈሪ ነው፣ ዘላለም በፍርሃት የተጨማደደ” ተብሎ የሚፃፍበትን ጋዜጣ ግን ጋዜጣ ነው ብዬ ለመቀበልም፣ ለመናገርም ይቸግረኛል፤ ሙያውን ስለማውቅ፡፡
የእዚህ ዓይነት መገናኛ ብዙሃን ዓላማ ህዝቡ በመንግስትና በተቋማት ላይ እምነት እንዲያጣ ማድረግ ነው፡፡ ተቋማትም ሆነ መንግስት የሚሻሻለው ግን ሚዲያው የጉዳዩ ባለቤት ሲያደርገው ነው፤ “እንዲህ አስተካክል” ሲለው እንጂ አሁን በሚታየው መንገድ አይደለም፡፡ በመንግስት ወገን የሚደረገውም ትክክል ነው እያልኩ አይደለም፡፡ እኔ መንግስትን ብሆን ጋዜጦቹን አልነካቸውም ነበር፡፡ በሌላ በኩል ግንበውጭ አገር ያሉ የጋዜጠኞች መብት ተሟጋች ነን ባዮች አይዋጡልኝም፡፡ ትክክለኛውን የጋዜጠኝነት ሙያ ተከትሎ የሚሠራ ሚዲያን አይፈልጉም፡፡ በሀገሪቱ ውስጥ ሁከት የሚያመጣን ነው የሚደግፉት፡፡
በዛሚ ኤፍ ኤም ሬዲዮ ጣቢያ “የጋዜጠኞችየክብ ጠረጴዛ” ፕሮግራም ላይ ጋዜጦችና የጋዜጠኞች ማህበር ከውጪ ተቋማትና ከፖለቲካ ፓርቲዎች ገንዘብና ድጋፍ ያገኛሉ የሚሉ ውንጀላዎች ይሰነዘራሉ፡፡ በዚህም ዛሚ ወንጃይ ሆኗል በሚል የሚተቹ ወገኖች አሉ፡፡
ይሄ ውንጀላ አይደለም፡፡ ዛሚም እኮ የሚዲያ ተቋም ነው፡፡ ዛሚም እኮ ሁኔታውን ያያል፣ የማይደራድርባቸው መርሆዎች አሉት፡፡ በዚህም ምክንያት ገንዘብና ድጋፍ አይደረግለትም፡፡ ከዚህ ቀደምም የተጠየቅንበት ሁኔታ ነበር፡፡ ገንዘቡ እንዳለ፣ ገንዘቡ እንደሚመጣ አውቃለሁ፡፡ የጋዜጠኞች የክብ ጠረጴዛ አላማም ሙያችን፣ ኢንዱስትሪው በጠንካራ እና ትክክለኛ መሠረት ላይ እንዲገነባ ብቻ ሳይሆን እንደዚህ ዓይነት ነገሮችን ህብረተሰቡ እንዲያውቅ ማድረግም ነው፡፡
በቀደም ዕለት በክብ ጠረጴዛ ፕሮግራም ላይ ከፖሊስ ያገኘሁትን መረጃ አውርቻቸዋለሁ፡፡ ከኬንያ የመጣው የ“አርቲክል 19” ሰውዬ… ኬንያዊ ያደረጉት እኮ… “አርቲክል 19” ነጭ አጥተው አይደለም፡፡ ነጩ ከመጣ መንግስት ሊያየውናአይኑን ሊጥልበት ይችላል ብለው ነው፡፡ ይሄኛው ግን ቪዛም አያስፈልገውም በሚል ነው መርጠው የላኩት፡፡ ይሄ ሰውዬ አምስት ጊዜ ወደ ኢትዮጵያ ተመላልሷል፡፡ የተወሰኑ ጋዜጠኞችን ብቻ ነው የሚያሰለጥነው፡፡ ውጭ አገር የሚወስዱት፣ ትልልቅ ሆቴሎች ውስጥ ስብሰባ የሚያደርጉት ከተወሰኑ ጋዜጠኞች ጋር ብቻ ነው፡፡ ይሄ ደግሞ ለኢትዮጵያ ጋዜጠኞች እድገት አይጠቅምም፡፡
የፕሬስ አዋጁ ሲረቀቅ ሸራተን በተደረገው ስብሰባ “አርቲክል 19” የገንዘብ ድጋፍ ማድረጉ ይነገራል፡፡ ይሄ እውነት ከሆነ የአሁኑ ስልጠና ለምን እንደ ወንጀል ተወሰደ?
“አርቲክል 19” ቶቢ ሜንደ የተባለ ባለሙያ በመላክ በኤክስፐርት ደረጃ እገዛ አድርጓል፡፡ ገንዘብ ግን አልሰጠም፡፡ ተቋሙ አዲስ አበባ ጋዜጠኞች አሰለጥናለሁ ብሎ ለምንድን ነው የተመረጡት ጋዜጠኞችን ብቻ የሚወስደው? ለምንድን ነው ስልጠናውን በድብቅ የሚያካሂደው? ለሁሉም አዲስ አበባ ላሉ ጋዜጠኞች (ለየተቋማቱ) ደብዳቤ ልኮ ሥልጠናውን መስጠት ይችል ነበር፡፡ እነማን ናቸው የተመረጡት? ምንድን ናቸው? በመንግስት ቦታ ብትሆኑ እኮ አስተያየታችሁ ሌላ ይሆናል፡፡ ሰውየው እኮ ገንዘብ እያመጣ ይሰጣል፡፡ ይሄ ምን ሊባል ይችላል? “የጋዜጠኞች የክብ ጠረጴዛን” አነሳችሁ እንጂ… ግብፅና ኤርትራ በግልጽ እኮ ነው የተናገሩት፡፡ ምንም አይነት መንገድ ተጠቅመን ኢትዮጵያ ውስጥ ያለመረጋጋትን እንፈጥራለን ብለዋል፡፡ ከዚህ በፊትም ለኢሳት ገንዘብ መስጠታቸውን እናውቃለን፤ በተጨባጭ የተረጋገጠ ነው፡፡ ሁላችሁም ተጠንቀቁ ነው የምንለው፡፡ በዳያስፖራው ውስጥ ከፍተኛ ገንዘብ በማንቀሳቀስ ለመበጥበጥ የተዘጋጁ አሉ፡፡ በዚህች አገር ውስጥ ህገወጥ እንቅስቃሴ ለማድረግ ፈቃደኛ ለሆኑ ሰዎች ገንዘብ ተዘጋጅቶ ተቀምጧል፡፡ ስለዚህ በሉዓላዊነታችሁ ላይ አትደራደሩ፡፡ ማንም ሚዲያ የአገሩን ጥቅም አሳልፎ እንዳይሰጥ…እንላለን፡፡
በተለያዩ የህትመት ውጤቶች ላይ “የጋዜጠኞች ክብ ጠረጴዛን” ተቃውመው ሲጽፉ አያለሁ፤ መንግስትን የሚደግፍ በሚል፡፡ መንግስትን ደገፉ የሚባለው “ልማትህን ጠብቅ፣ ከድህነት የምትወጣው በልማት ላይ ስትተጋ ነው” ስለምንል ነው፡፡ ይሄን ለማለት የመንግስት ደጋፊ መሆን አይጠይቅም፡፡ ወደ አገሬ የመጣሁት ይሄን ልሠራ ነው፡፡ አሜሪካንን ትቼ የመጣሁት ጠንካራና የበለፀገ “ቫይብራንት” የሆነ የሚዲያ ኢንዱስትሪ ለመገንባት ነው፡፡ መንግስትን መቆጣጠር የሚችል፣ የመንግስት ጠላት ሳይሆን እንደ አንድ ተቋም የህዝብን ደህንነት በጋራ የሚጠብቅ ሚዲያ ለመፍጠር ነው፤
ጋዜጠኝነት፤ ልማታዊ የሚባል ቅፅል አያስፈልገውም፡፡ ጋዜጠኝነት በራሱ ልማታዊ ነው፡፡ እኔ “የፖለቲካ” ወይም “የታይብሎይድ” ጋዜጠኝነት በሚል በሚሰጠው ቅፅል ተስማምቼ አላውቅም፡፡ ጋዜጠኝነት “ኢንስትሩመንት ፎር ሂዩማን ቢንግ” (ለሰው ልጅ የሚያገለግል እንደማለት) ብዬ ነው የምከራከረው፡፡
ከኤርትራና ከግብፅ ገንዘብ ወስደዋል ብላችሁ ተናግራችኋል፤ ገንዘቡ መቼ ተሰጠ? ለማን ተሰጠ? እንዴት ተሰጠ?
እኛ እኮ ያንን የተናገርነው ከፖሊስ መረጃ ነው፡፡ የፖሊስ መረጃ ከተለያዩ አካባቢዎች ፈንድ በተለይ ከውጪ እንደሚደረግ ነው የጠቀሰው፡፡ የሆነ ሆኖ ግን ሃገሪቱን ለማተራመስ ቅርጫት አስቀምጠው የሚለምኑ ወገኖች እንዳሉ እናውቃለን፡፡
እነማን ናቸው ይሄን የሚያደርጉት በስም እንወቃቸው
እንዴ! ብርሃኑ ነጋ ከግብፅ ተቀብሎ በኢሳት ሲታይ አልነበረም እንዴ?
ብርሃኑ ነጋ መቀበሉ እነዚህን የሃገር ውስጥ ሚዲያዎች እና አክቲቪስቶች ለመወንጀል እንዴት ያስችለናል?
አይደለም! እኛ እኮ ሃሳብ የሰጠነው ሲቀባበሉ በዓይናችን አይተናል ብለን አይደለም፡፡ ከአርቲክል 19 ጋር በስውር ሲንቀሳቀሱ ከፖሊስ መረጃ ማግኘታችንን ነው የተናገርነው፡፡
በአጠቃላይ በዚህች ሃገር ውስጥ የጎዳና ላይ ነውጥ እንዲካሄድ ግፊት የሚያደርጉና ገንዘብ የሚያሰባስቡ ሃይሎች እንዳሉ የታወቀ ነው አልን እንጂ እነሱ ተቀብለዋል የሚል ውንጀላ አላቀረብንም፡፡ ልንልም አንችልም፡፡ የጎዳና ላይ ነውጥ የሚናፍቁ ወገኖች ገንዘብ እንዴት እንደሚያገኙ ነው የተናገርነው፡፡ ይሄ ደግሞ በአለማቀፍ ደረጃ የሚታወቅ መረጃ ነው፡፡ እኛ ገንዘብ ሲቀበሉ አይተናል የሚል ቃል አልወጣንም፡፡
ከዚህ ቀደም ሪፖርተርስ ዊዝ አውት ቦርደር የአንቺን ፕሮግራም ስፖንሰር ያደርግ ነበር ዛሬ ላይ ከእነዚህ ተቋማት ገንዘብ ተቀብሎ መስራቱን እንዴት ትኮንያለሽ?
በድብቅ ሲሆን ነዋ! እኛ እኮ በግልፅ እየተናገርን ሪፖርተርስ ዊዝ አውር ቦርደርስ ገንዘብ ሰጥቶናል ብለን ተናግረን ነው የተጠቀምነው፡፡ አሁን ግን በድብቅ ጋዜጠኞችን በየሆቴሉ ሰብስቦ ሰጠ የሚል ነው ከፖሊስ ያገኘነው መረጃ፡፡
በሰብአዊ መብትና በሚዲያ ጉዳይ ላይ የሚሰሩ አለማቀፍ ተቋማት ሁሉም መንግስትን ይተቻሉ፡፡ ይሄ መንግስት ጋር ድክመት መኖሩን አያሳይም?
አንድ አይነት ትችት የሚያቀርቡት ምንጫቸው አንድ አይነት ስለሆነ ነው፡፡ ፍልስፍናቸው፣ ተልእኮአቸው፣ የገንዘብ ምንጫቸው አንድ አይነት ነው፡፡ ስለዚህ አንድ አይነት ነው ሊያወሩ የሚችሉት፡፡
ለኢህአዴግ ትወግናለች ኢህአዴግም ነች ትባያለሽ አንቺ ደግሞ ማስረጃ የሌለው ውንጀላ ነው ትያለሽ፡፡ እናንተስ ፕሬሶችንና ጋዜጠኞችን የውጭ ሃይሎች ተላላኪ ናቸው ስትሉ ያለ ማስረጃ መወንጀል አይሆንም?
እኔ ላይ ማስረጃ ማንም ሊያቀርብ አይችልም፡፡ እኔ ሚዲያ ነኝ፡፡ ሚዲያ ደግሞ ትልቁ መርሁ ገለልተኛነት ነው፡፡ እኔ ፖለቲከኛ ሆኜም አላውቅም፡፡ ልሆንም አልችልም፡፡ እኔ ላይ የሚቀርበውን ውንጀላ ያመጣው ሻዕቢያ ነው፡፡ በኢትዮ-ኤርትራ ጦርነት ጊዜ ዜናውን መጀመሪያ ይፋ ያደረኩት እኔ ነኝ፡፡ ወረራ የተፈፀመው ኤርትራ ጦር እንደሆነ በመናገሬ፣ በወቅቱ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሯ ሱዛን ራይትስ የኤርትራ ጉዞዋን ልትሰርዝ ችላለች፡፡ ስለዚህ የእኔን ተአማኒነት ለመሸርሸር ነው ሻዕቢያ ይሄን ዘመቻ የጀመረው፡፡ ነገር ግን እኔ በራሴ ስለምተማመን ስራዬንም ህዝብ የሚያየው ስለሆነ የሚያስጨንቀኝ ነገር አይደለም፡፡
አንቺስ ያለማስረጃ ወንጃይ አልሆንሽም ወይ ለተባለው እኛ በመጀመሪያ ደረጃ እገሌ እንዲህ አድርጓል ብለን አይደለም የምንናገረው፡፡ ፖሊስ የሰጠንን መረጃ ነው የተናገርነው፡፡
በተደጋጋሚ በክብ ጠረጴዛ ፕሮግራሞች ላይ ፕሬሶቹ ገለልተኛ እንዳይሆኑ ያደረጋቸው ገንዘብ ከፓርቲ ስለሚቀበሉ ነው የሚሉ ትችቶችንና ውንጀላዎችን ታቀርቢያለሽ፡፡ ለዚህ ማስረጃ አለሽ?
መልስ ነው የሃገራችን ፕሬሶች የሙያውን መርህና ስነ ምግባር ተከትለውመንቀሳቀስ አለባቸው ነው የምንለው
ከገንዘብ ጋር የተያያዘ ነገር ይነሳል፣ ከፓርቲ ፈንድ ይደረግላቸዋል ትላላችሁ ለዚህ ማስረጃ አላችሁ ወይ ነው ጥያቄያችን?
እኛ እንደዚያ ብለን አልፈረጅንም፡፡ ነገር ግን እንደዚህ አይነት ነገሮች በሌላው አለም እንዴት ነው የሚስተናገዱት የሚለውን በልምድም እናውቀዋለን ነው ያልነው እንጂ ተቀብለዋል የሚል መደምደሚያ ያለው ነገር አልተናገርንም፡፡ ያለውንና የምናውቀውን ሁኔታ እየተናገርን ጥንቃቄ እንደሚያስፈልግ ነው መልእክት የምናስተላልፈው፡፡ ጋዜጦች የፖለቲካ ፅንፍ መያዝ ይችላሉ ብለናል ነገር ግን በሙያው ስም መጠቀም የለባቸውም ነው መከራከሪያችን፡፡ የተቃዋሚ ድርጅት ልሳን ነኝ ብሎ ራሱን ይፋ ማድረግ እንጂ በመገናኛ ብዙሃን ስም ማጭበርበር አይቻልም፡፡ አክቲቪዝም እና ጋዜጠኝነት መለያየት አለባቸው ነው የኛ አቋም፡፡ ትችት ለምን ታቀርቢያለሽ ከሆነ እነሱም እኮ በኛ ላይ ብዙ ነገር ይፅፋሉ ይተቻሉ፡፡ እኔ እንደውም አሉባልታቸው ሲበዛ ነው ከሙያው ስነምግባር ጋር እያጣቀስኩ መተቸት የጀመርኩት፡፡
ምንጭ፦ አዲስ አድማስ
Articles
በኦስሎ ዳይመንድ ሊግ የ5000ሜ ፉክክር ኢትዮጵያውያን አትሌቶች በሁለቱም ፆታዎች በአሸናፊነት አጠናቀዋል

ትላንት ምሽት በኖርዌይ ኦስሎ በተከናወነው የዳይመንድ ሊግ 5000 ሜ. ውድድር ኢትዮጵያውያን አትሌቶች በወንዶችም በሴቶችም ከአንደኛ እስከ ሶስተኛ ያሉትን ደረጃዎች በመቆጣጠር አሸንፈዋል፡፡ በዝናባማ የአየር ሁኔታ ውስጥ በተካሄደው የሴቶች 5000 ሜትር ፉክክር ዳዊት ስዩም በመጨረሻዎቹ መቶ ሜትሮች ውስጥ ፍጥነቷን በመጨመር ጉዳፍ እና ለተሰንበትን ቀድማ አንደኛ ወጥታለች፡፡ የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ለኦሪገን 2022 የአለም ሻምፒዮና ከመረጣቸው ዕጩ አትሌቶች ዝርዝር ውስጥ ያልተካተተችው ዳዊት በኦስሎ ያሸነፈችበት 14፡25.84 የሆነ ሰአት የራሷ ምርጥ ሲሆን እጅጋየሁ ታዬ (14.12.98) እና ለተሰንበት (14፡24.59) ባለፈው ወር በዩጂን ካስመዘገቧቸው በመቀጠልም የዘንድሮ የአለም ሶስተኛው ፈጣን ነው፡፡ በውድድሩ ላይ ከነበሩት ሌሎች ኢትዮጵያውያን መካከል በዘንድሮው የውድድር ዓመት በርቀቱ የመጀመሪያ ተሳትፎዋን ያደረገችው አልማዝ አያና በ14:32.17 ስድስተኛ ሆና አጠናቃለች፡፡ ሀዊ ፈይሳ በ14:33.66፣ ፅጌ ገብረሰላማ በ14:43.90፣ እና አበራሽ ምንሴዎ በ14:47.98 በቅደም ተከተል ሰባተኛ፣ አስረኛ እና አስራ አንደኛ ሆነው ሲያጠናቅቁ ሶስቱም ያስመዘገቡት ሰዓት የራሳቸውን ምርጥ ያሻሻሉበት ሆኗል፡፡ ጥሩነሽ ዲባባ እ.ኤ.አ. በጁን 2008 ዓ.ም. ያስመዘገበችውና 14:11.15 የሆነው የኦስሎ ዳይመንድ ሊግ የሴቶች 5000 ሜትር የውድድር ስፍራ ሪከርድ ይሰበራል ተብሎ ተጠብቆ የነበረ ቢሆንም ሳይሳካ ቀርቷል፡፡

ዳዊት ስዩም ውድድሩን በድል ካጠናቀቀች በኋላ ለውድድሩ አዘጋጆች በሰጠችው አስተያየት ‹‹ዛሬ ለእኔ ደስታን ስላመጣልኝ በውድድሩ ሰዓት የነበረውን ዝናብ ወድጄዋለሁ ማለት እችላለሁ፡፡ ጠንካራ ተፎካካሪዎች የነበሩበት ከባድ ውድድር ነበር እናም ሁሉንም ለማሸነፍ በቅቻለሁ። በርቀቱ የራሴን ምርጥ ሰዓት ማሻሻል መቻሌም አስፈላጊ ነበር፡፡ በስታድየሙ ውስጥ በከፍተኛ ስሜት ድጋፍ ይሰጡን የነበሩ ወገኖቻችን ነበሩ። ለሰጡን ድጋፍ እናመሰግናለን።›› ብላለች፡፡ በኦስሎ የወንዶች 5000 ሜትር የመጨረሻ ፉክክሩ በኢትዮጵያውያኑ ጥላሁን ሀይሌ እና ሳሙኤል ተፈራ መካከል የነበረ ሲሆን ጥላሁን የ1500 ሜትር ስፔሻሊስቱ ሳሙኤልን በአጨራረስ ፍጥነት ቀድሞ በ13:03.51 በአንደኛነት አጠናቋል፡፡ ሳሙኤል ተፈራ የራሱ ምርጥ በሆነ 13:04.35 ሁለተኛ ሲወጣ ጌትነት ዋለ የግሉ የዓመቱ ምርጥ በሆነ 13:04.48 ሶስተኛ ደረጃን ይዞ ጨርሷል። በውድድሩ ላይ የነበሩት ሌሎች ኢትዮጵያውያን ሚልኬሳ መንገሻ በ13:05.94 አምስተኛ እንዲሁም አሊ አብዱልመናን የራሱ ምርጥ በሆነ 13:16.97 አስረኛ ወጥተዋል፡፡

ጥላሁን ሀይሌ ውድድሩን በአሸናፊነት ካጠናቀቀ በኋላ ለውድድሩ አዘጋጆች በሰጠው አስተያየት ‹‹ሶስት ኢትዮጵያውያን የመጀመሪያዎቹን ሶስት ደረጃዎች ይዘን መጨረስ መቻላችን ጥሩ አፈጻጸም ነበር። እየጠነከርኩ እንደሆነ የተሰማኝ ሲሆን በውድድሩ እና ባስመዘገብኩት ሰዓትም ተደስቻለሁ። ለረጅም ጊዜ ጉዳት ላይ ስለነበኩ ወደ አሸናፊነቱ መመለስ መቻሌ በጣም ጥሩ ነው።›› ብሏል፡፡
በኦስሎ የሴቶች 800ሜ. ውድድር ላይ ተፎካካሪ የነበረችው ኢትዮጵያዊቷ ድሪቤ ወልቴጂ በ1፡58.69 አምስተኛ ሆና አጠናቃለች።
Articles
የዘንድሮው የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ብሄራዊ ሻምፒዮና በእኔ እይታ

ከመጋቢት19-24/2014 ዓ.ም በሐዋሳ አለም አቀፍ ስቴድዮም የተደረገው 51ኛዉ የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ሻምፒዮና ከሞላ ጎደል ስኬታማ በሚባል ሁኔታ ተጠናቋል፡፡ ከአምስት አመት በኋላ በድጋሚ በአካል በመገኘት ስለተከታተልኩት የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ሀገር አቀፍ ሻምፒዮና የግል ምልከታዬን እንደሚከተለው አጠናቅሬዋለሁ፡፡ የበለጠ ትኩረትን በሳቡት ውድድሮች ዙሪያ የተመዘገቡ ውጤቶችን በወፍ በረር በመዳሰስ ስጀምር ከፍተኛ ፉክክር በታየበት የመጨረሻ ቀን የወንዶች 5000ሜ. የአለም ከ20 አመት በታች ሻምፒዮና የ3000ሜ የብር ሜዳልያ አሸናፊው አሊ አብዱልመና 13፡45.0 በሆነ ሰዓት ከጥላሁን ሀይሌ፣ ጌትነት ዋለ እና ዮሚፍ ቀጄልቻ ቀድሞ አሸናፊ ሆኗል፡፡ የፉክክሩ አካል የነበረው እና የርቀቱ የወቅቱ የአለም ሻምፒዮን ሙክታር እድሪስ ስድስተኛ ወጥቷል። ከ20 ዓመት በታች የ3000ሜ የአለም ሻምፒዮኑ ታደሰ ወርቁ በ28፡12.0 የወንዶች 10,000ሜ. ሻምፒዮን ሲሆን በ1996 ዓ.ም. በአትሌት ስለሺ ስህን ተመዝግቦ የነበረውን 28፡16.23 የሆነ የሻምፒዮናው ሪኮርድ ለማሻሻልም በቅቷል፡፡ በ10 ሺህ ሜትር የሴቶች ፉክክር ግርማዊት ገብረእግዚአብሔር በቀዳሚነት የጨረሰችበት 31፡21.5 የሆነ ሰዓት አዲስ የሻምፒዮንሺፕ ሪኮርድ ሆኖ ተመዝግቧል፡፡ በርቀቱ የከዚህ ቀደሙ ሪኮርድ ለተሰንበት ግደይ ከሶስት ዓመት በፊት ያስመዘገበችው 32፡10.13 የሆነ ሰዓት ነበር፡፡ ሳሙኤል ፍሬው በዘንድሮ የወንዶች 3000ሜ. መሰናክል አፈፃፀም ከአለም ሁለተኛው ፈጣን በሆነ 8፡22.5 ሰዓት አሸናፊ ሲሆን ጌትነት ዋለ ከአራት ዓመት በፊት አስመዝግቦት የነበረውን 8፡28.98 የነበረ የሻምፒዮናው ሪኮርድም አሻሽሏል፡፡ በሴቶች 3000ሜ. መሰናክል ከ800ሜ ወደ ረጅም ርቀት የተሸጋገረችው ወርቅውሃ ጌታቸው በ9፡41.8 ሰዓት መቅደስ አበበን (9:43.8) በማስከትል በአሸናፊነት አጠናቃለች። አድሃና ካህሳይ (3:51.0) የወንዶች 1500ሜ ፉክክሩን በበላይት ሲያጠናቅቅ በሴቶች 1500 ሜ አያል ዳኛቸው (4:10.0) ተጠባቂዋ ዳዊት ስዩምን (4:11.1) በመቅደም በአንደኛነት አጠናቃለች። በ800ሜ. ወንዶች ቶሌሳ ቦደና (1:47.1) በሴቶች ወርቅነሽ መሰለ (2:02.1) አሸናፊ ሆነዋል። ዮብሰን ብሩ በ400ሜ/400ሜ መሰናክል (45.9/50.5) ድርብ ድል ሲቀዳጅ፣ በወንዶች ጦር ውርወራ ኡታጌ ኡባንግ ብሔራዊ ሪኮርድ በሆነ 73.28ሜ. አሸንፏል፡፡ የኋልዬ በለጠው እና ዮሃንስ አልጋው በእርምጃ ሩጫ የሻምፒዮንነት ክብርን ተቀዳጅተዋል። ጥቂት አስተያየቶች፡- የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ስፖርት አፍቃሪ እንደሆነ እና ለዕድገቱ እንደሚቆረቆር ሰው በብሔራዊ ሻምፒዮናው ላይ ስለተመለከትኳቸው አዎንታዊ እና አሉታዊ ጎኖች ጥቂት አስተያየቶቼን እንደሚከተለው አስቀምጣለሁ፡- አዎንታዊ ጎኖች • ባለው ነባራዊ ሁኔታ ውስጥ ሊገጥሙ የሚችሉትን ተግዳሮቶች በሙሉ በመቋቋም ፌዴሬሽኑ ውድድሩን ከአዲስ አበባ ውጭ አካሂዶ በሰላም ማጠናቀቅ መቻሉ አንደኛው ስኬቱ ነው፡፡ • በሻምፒዮናው ላይ ጥቂት የማይባሉ ታዋቂ አትሌቶች በሀገሪቱ ትልቁ የአትሌቲክስ ፉክክር ላይ ተሳታፊ ሆነው ሲወዳደሩ መመልከት የተቻለ ሲሆን በተለይም በወንዶች 5000 ሜትር ፍፃሜ ላይ የታየው የኮከብ አትሌቶች ፉክክር ልዩ ነበር፡፡ • በውድድሩ ወቅት ለአትሌቲክስ ዳኞች የብቃት ማሻሻያ ስልጠና መሰጠቱም የውድድሩን ጥራት ለማሳደግ የሚረዳ እንደመሆኑ እሰየው የሚባል ነው፡፡ • እንደ ኢትዮ ኤሌክትሪክ ያሉት ክለቦች ለአትሌቲክስ ስፖርት የበለጠ ትኩረት በመስጠትና ተጠናክሮ በመቅረብ ከዚህ ቀደም በጠንካራነታቸው ከሚታወቁት መከላከያ እና ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ጋር የቅርብ ተፎካካሪ ሆነው መታየት፤ የኦሮሚያ ክልል፣ ደቡብ ፖሊስ እና ሲዳማ ቡና ክለብ አትሌቶችም ጠንካራ ተሳትፎ ሳይዘነጋ የሻምፒዮናው ፉክክር ድምቀት ነበሩ፡፡ • የአንዳንዶቹ ተገቢነት አጠያያቂ ቢሆንም ብዛት ያላቸው የሻምፒዮናው ሪኮርዶች የተሻሻሉበት ውድድርም ነበር፡፡ አሉታዊ ጎኖች • የሀገሪቱ ትልቁ የአትሌቲክስ ውድድር ውጤት አሁንም በኤሌክትሮኒክስ የሰዓት መቆጣጠሪያ የማይደገፍ መሆኑ በተለይም በአጭር ርቀት እና በሜዳ ላይ ተግባራት ውድድሮች ላይ የሚሳተፉ አትሌቶች ልፋት ተገቢውን እውቅና እንዳያገኝ እያደረገ ይገኛል፡፡ የሻምፒዮናውን ውጤቶች በዘመናዊ እና ዓለም አቀፉን መለኪያ በሚያሟላ መልኩ አለመያዝ በአህጉራዊ እና አለም አቀፋዊ ውድድሮች ላይ ለተሳትፎ የሚያበቁ ውጤቶችን በማስመዝገቡ ረገድ የሚኖረው አሉታዊ ተፅዕኖ ከፍተኛ መሆኑ ከግምት ውስጥ ገብቶ አሁንም መፍትሄ ያልተበጀለት ጉዳይ ነው፡፡ • የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ወደ ሚዲያ/ለአጠቃላዩ ሕዝብ የሚያስተላልፈው የመጀመሪያዎቹን ሶስት ደረጃዎች ይዘው የሚያጠናቅቁ አትሌቶችን ውጤት ብቻ መሆኑ አወዳዳሪው አካል የሚያደርገውን የራሱን ውድድርም ሆነ አትሌቶቹ የለፉበትን ውጤት ከማስተዋወቅ አኳያ በቂ አይደለም፡፡ • በወንዶች የጦር ውርወራ እና የሴቶች ምርኩዝ ዝላይ ብሔራዊ ሪኮርዶች እንደተመዘገቡ ይታመናል፤ በሴቶች 100ሜ መሰናክል እና የወንዶች 400ሜ መሰናክል የተመዘገቡት ሰዓቶችም የምንግዜውም ፈጣን ሊሆኑ ይችላሉ፡፡ ነገር ግን ውድድሩ በኤሌክትሮኒክስ ታይሚንግ ያልተደገፈ እና የንፋስ ንባብ ያልነበረው መሆኑ ውጤቶቹ በዓለም አቀፍ ደረጃ ተቀባይነት እንዳይኖራቸው የሚያደርግ ነው። • በ20 ኪ.ሜ የእርምጃ ውድድር ላይ በሁለቱም ፆታዎች የተመዘገቡት ሰዓቶች ከሚጠበቀው በላይ እጅግ በጣም ፈጣን እና እውነታዊ አለመምሰላቸው በውድድሩ ላይ የተፈጠረ አንዳች ስህተት መኖሩን የሚያመላክቱ መሆኑ፡፡ እንዲህ አይነት ለማመን የሚከብዱ እና ጥርጣሬን የሚፈጥሩ አይነት ውጤቶች ሲመዘገቡም የተፈጠረ ስህተት መኖር አለመኖሩን ለማጣራት አለመሞከሩ፡፡ • የሴቶች 10 ኪሎ ሜትር ውድድር ላይ ለውድድር የማይፈቀድ የጎዳና ላይ መሮጫ ጫማን በመጠቀም የተመዘገበ ውጤት በሪኮርድነት ጭምር ተይዞ መፅደቁ። ብሔራዊ ፌዴሬሽኑ ከተከለከሉ ጫማዎች ጋር የተያያዙ ዓለም አቀፍ ሕገ ደንቦችን ማወቅና መተግበር ቢገባውም በሴቶች 10 ሺህ ሜትር ውድድር ላይ የተከሰተው ነገር የውድድር ሕገ ደንቦቹ መረጃ በፌዴሬሽኑ ውስጥ በትክክል የተሰራጩ እንዳልሆነ የሚያመላከት ነው፡፡ • በሴቶች 1500 ሜትር የግማሽ ፍፃሜ ውድድር ላይ አትሌት ዳዊት ስዩም የሻምፒዮናውን ሪኮርድ ያሻሻለችበት ውጤት እንደተመዘገበ በውድድሩ ወቅት በተደጋጋሚ ሲነገር ከተደመጠ በኋላ ግልፅ ባልተደረገ ምክንያት ውጤቱ በሐዋሳው ውድድር ላይ ተሻሻሉ ከተባሉት የሻምፒዮናው አዲስ ሪኮርዶች ዝርዝር ውስጥ ሳይካተት መቅረቱም የፌዴሬሽኑን ግልፀኝነት ጥያቄ ምልክት ውስጥ የሚከት ነው፡፡ ከላይ የተዘረዘሩት አዎንታዊ እና አሉታዊ ጎኖች ለረጅም ግዜ የኢትዮጵያን አትሌቲክስ ስፖርት እንቅስቃሴዎች በቅርበት ከመከታተሌ አንፃር በራሴ እይታ ያስቀመጥኳቸው እንደመሆናቸው አንዳንዶቹ ሀሳቦች አከራካሪ ሊሆኑ ይችላሉ፡፡ ሆኖም የውድድር ደንቦችን በአግባቡ ከማስፈፀም አኳያ በታዩት ክፍተቶች ዙሪያ ምንም የሚያከራክር ጉዳይ ስለሌለ በወቅታዊ የውድድር ደንቦች ዙሪያ የግንዛቤ እጥረት ላለባቸው የስፖርቱ ባለድርሻ አካላት በሙሉ አስፈላጊውን ገለፃ እና ትምህርት መስጠት የፌዴሬሽኑ ኃላፊነት ነው፡፡ ከውድድር ጋር የተያያዙ ደንቦችን ከመጣስ አኳያ በሀገር ውስጥ በሚደረጉ ውድድሮች እንደቀላል ነገር የሚታለፉ ጉዳዮች በዓለም አቀፍ ውድድሮች ላይም ተደግመው እንደግል አትሌቶችን እንደቡድን ሀገርን ትልቅ ዋጋ ሊያስከፍሉ ይችላሉና አስፈላጊው ጥንቃቄ ቢደረግ መልካም ነው፡፡ ባለፈው መስከረም ወር በቪየና ሲቲ ማራቶን ውድድሩን በአሸናፊነት ጨርሶ የነበረው ኢትዮጵያዊው ደራራ ሁሪሳ የገጠመውን አንዘንጋው! ሀገራችን ኢትዮጵያን በመልካም ጎኑ ስሟ እንዲነሳ በሚያደርገው እና በትልልቅ ዓለም አቀፍ የውድድር መድረኮች ላይ የኩራታችን ምንጭ በሆነው የአትሌቲክስ ስፖርት እንደጎረቤታችን ኬንያ ዓለም አቀፍ ውድድሮችን የማስተናገድ የብቃት ደረጃ ላይ ደርሰን ማየት የዘወትር ምኞቴ ነው፡፡ የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌደሬሽንም የውድድሮቹን ጥራት ለማሻሻል በትኩረት እንደሚሰራ ተስፋ አደርጋለሁ።
በመጨረሻም በሀዋሳ በተካሄደው 51ኛዉ የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ሻምፒዮና ከመሮጫ ጫማ ጋር የተያያዙ ደንቦችን በማስከበሩ ረገድ የተፈጠረውን ክፍተት እንደማስተማሪያ ብንጠቀምበት በሚል የሚከተለውን ለማለት ወደድኩ፡-
የመሮጫ ጫማ ደንቦች ለትራክ ውድድር
64 ደቂቃ ከ14 ሰከንድ በሆነ ሰዓት የዘንድሮ የራስ አል ካይማህ የግማሽ ማራቶን ውድድር አሸናፊ የሆነችው ግርማዊት ገብረእግዚአብሔር በሐዋሳ በተከናወነው 51ኛው የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ሻምፒዮና ላይ 31 ደቂቃ ከ21.5 ሰከንድ በመግባት የ10,000ሜ. አሸናፊ ሆናለች፡፡ የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽንም ዓለም አቀፉን ደንብ ከግምት ባላስገባ ሁኔታ ውጤቱን በአዲስ የሻምፒዮንሺፕ ሪኮርድነት ጭምር አፅድቆት አልፏል፡፡ ይሁን እንጂ መጋቢት 20/2014 በተደረገው የሴቶች የፍፃሜ ፉክክር ላይ በኢትዮጵያ ምድር የተመዘገበ የምንግዜውም ፈጣን የሴቶች 10 ሺህ ሜትር ሰዓት የሆነው ውጤት በአለም አትሌቲክስ ዘንድ እውቅና ሊሰጠው የማይችል ነው።
● ለምን?
አትሌቷ የሶል ውፍረቱ 40ሚሜ የሆነ ዙምኤክስ ቬፐርፍላይ (ZoomX Vaporfly) ጫማ አድርጋ በመወዳደሯ ምክንያት።
● ደንቡ ምን ይላል?
በትራክ ውድድሮች ላይ የሚፈቀደው ከፍተኛው የሶል ውፍረት ፡-
– 20ሚሜ ከ 800ሜ በታች ለሆኑ ውድድሮች እና ለሁሉም የሜዳ ላይ ተግባራት (ከስሉስ ዝላይ በስተቀር)
– 25ሚሜ ለ800ሜ እና ከዛ በላይ ለሆኑ ውድድሮች እንዲሁም ለስሉስ ዝላይ
– 40ሚሜ ለትራክ ላይ የእርምጃ ውድድሮች
እነዚህ ደንቦች እ.ኤ.አ. እስከ ኦክቶበር 31, 2024 ድረስ በሥራ ላይ ይውላሉ። ከኖቬምበር 1 ቀን 2024 ጀምሮ ለ800ሜ እና ከዚያ በላይ ለሆኑ ውድድሮች እንዲሁም ለስሉስ ዝላይ የሚፈቀደው ከፍተኛ የሶል ውፍረትም ወደ 20 ሚሜ ዝቅ የሚል ይሆናል።
● የትራክ ላይ መወዳደሪያ ስፓይክ ጫማ ከሌለኝስ?
ደንቡ የጎዳና ላይ የመሮጫ ጫማዎች በትራክ ላይ እንዳይደረጉ አይከለክልም ነገር ግን በ25 ሚሊ ሜትሩ ገደብ ምክንያት 30 ሚሜ ወይም 40 ሚሜ የሆኑ የጎዳና ላይ መሮጫ ጫማዎች በትራክ ውድድሮች ላይ እንዲደረጉ አይፈቅድም፡፡
● ለበለጠ መረጃ :-
https://www.worldathletics.org/news/press-releases/new-athletic-shoe-regulations-approved-2022
Opinions
On the TPLF’s Love Affair With ‘Genocide’

Today, the joint investigation report by the Ethiopian Human Rights Council and the UNHR
on human rights violations committed in Tigray concluded that there is no evidence that genocide has taken place so far. While this is a bit of a setback for the TPLF, which has wanted the world to believe—since the 1990s, even as the TPLF was dominating power in Addis—that a genocide has been perpetrated against the people of Tigray, unfortunately the group still appears to be determined to make genocide a reality. This is confusing for people who don’t understand why the TPLF is obsessed with genocide, why its internet cadres began using #TigrayGenocide in April 2020, months before the war began. So many weapons have been deployed in this war, and among them: confusion and obfuscation.
In the past several months and more so in the past few weeks, we have been getting
testimony after testimony from allied Amhara forces fighting the TPLF that Tigrayan residents of cities in Wollo have been collaborating with the TPLF by a) attacking ENDF and allied forces from behind; b) forcing ENDF and allied forces to withdraw from towns and cities afraid of committing large scale massacres by firing back at the civilians (Tigrayans) firing at them; c) helping the TPLF locate and execute young Amharas believed to be a threat; and d) in at least one horrifying account by an IDP who managed to escape occupied territories, handing TPLF soldiers a list of women to rape. Another shocking development in the past several months has been the widespread use of child soldiers by the TPLF, which, according to experts who have studied the practice, is an “alarm bell” calling attention to possible plans to commit mass atrocities. The use of child soldiers by the TPLF and its attendant implications, along with the widespread deployment of civilian sleeper agents in Amhara cities the TPLF has taken over, serves to create an overall perception of every Tigrayan as a potential enemy, sowing fear and mistrust.
Many Ethiopians are looking at this and wondering: why are Tigrayan elites on the internet
either celebrating the TPLF’s advance via these toxic methods or silent about all this? How can they not see how dangerous this is for everyone, especially for Tigrayans who live outside Tigray? How can they not see that there is no “winning” after stoking all this lasting animosity? Do Tigrayan elites not understand that there can be no justice for Tigray—whether Tigray secedes or not—unless there is justice for her neighbors, for Tigray does not exist in a vacuum? The questions are being asked but nobody is answering them. Our academic class has largely failed to offer viable analyses of the ideas driving this war, as they failed over the past fifty years in regards to coming up with a fitting paradigm for understanding Ethiopia’s unique situation.
Here is my humble attempt to explain what I think is happening with the TPLF’s obsession
with—and with its active attempt to inspire—genocide:
The most successful psychopaths in any field understand that, in order to win anything, one
must risk everything, including the very thing one is supposedly fighting for. In the case of the
TPLF (and associated Tigrayan political elites), whose motto appears to be “give me supremacy or give me death,” that “everything” they are risking is the lives of ordinary Tigrayans in whose names they are fighting. We have seen over the past several months the extent to which the TPLF is willing to go to sacrifice ordinary Tigrayans in order to get what it wants: wave after wave after wave of young poorly armed and inexperienced Tigrayans were unleashed upon ENDF and Amhara and Afar forces in order to force the latter to waste ammunition and energy before the more experienced soldiers are sent.
So, for a political group who sends tens of thousands, if not hundreds of thousands, of
young Tigrayans towards open fire, violence against hundreds of thousands of Tigrayans is nothing if it means the TPLF will in the end win the “prize” it has been obsessed with for decades: genocide. You see, merely attaining power in Addis Ababa is not enough for the TPLF, whose core driving ideology is Tigrayan supremacy. Power is temporary; anybody can take it away from you, and the 2018 uprisings demonstrated that. Genocide is forever. Nobody can take away from you the story of genocide committed against your people.
The TPLF looked at countries like Israel and Rwanda and realized what a potent instrument
genocide is for establishing perpetual minority rule. We have some indications suggesting that the TPLF views Israel as a model. When the war between Ethiopia and the TPLF began in November 2020, Sekoutoure Getachew, a TPLF official, went on TV to tell us that the TPLF’s decision to launch a preemptive attack on the Northern Command was inspired by how the young state of Israel, feeling threatened by her neighbors, launched preemptive attacks against them in the “six-day war” of 1967. Another indication is the manner in which the TPLF, during its 27 years in power, invested heavily in creating a wealthy and strongly networked Tigrayan diaspora which has been used to lobby and influence western governments and organizations much in the same way as the Jewish diaspora aids the state of Israel. The TPLF has figured out that truth does not matter in politics, especially in international politics. If you have the wealth and the personnel to peddle your preferred narrative, if you have the military power to subdue the people you want to subdue, if you are willing to make concessions to external forces (US, Egypt, etc), you can do unspeakable things to others (much like the state of Israel does to Palestinians) and still manage to portray yourself as the victim.
This calculation is so far working for the TPLF, but nothing would seal the deal like the actual
commission of genocide—or something that looks like it—against Tigrayans. As we have seen over the past twelve months, western governments and organizations have shown their willingness to adopt TPLF’s narratives without scrutiny and can easily reward the TPLF with its much pursued prize, genocide, even if actual genocide doesn’t take place.
But why does the TPLF need genocide to establish minority rule? Because, as we saw in their
first tenure in power, you can only rule with an iron fist for a limited period of time. Leaders of the TPLF are adherents of Tigrayan supremacy: the idea that Tigrayans, as the “only” heirs of the Axumite empire, are the natural rulers of the Ethiopian state, and cannot be ruled by “barbarians” south of them. The only acceptable power arrangement for the TPLF is one in which Tigrayans are either directly dominating political power or are the perpetual kingmakers pulling all the major strings. Anything outside that, any system that forces Tigrayans to live on equal footing with everyone else, is unacceptable. And this kind of domination by a minority cannot coexist with a democratic system that the majority of Ethiopians clearly prefer. So, the TPLF needs something more potent than pure political/economic/military power to justify bypassing democracy to establish itself as the permanent ruler/kingmaker of Ethiopia. It needs a new and powerful raison d’être to justify its domination not just to Tigrayans and the rest of Ethiopians but, and most importantly, to the rest of the world. If a genocide were to be committed against Tigrayans (or if the U.S. decides to reward the TPLF with the genocide label even in the absence of it), then the TPLF can license itself to impose all manner of drastic measures aimed at “protecting Tigray and
Tigrayans.” This could be anything from redrawing internal borders (and taking debilitating
measures against the peoples whose lands are being robbed—most likely Amharas and Afaris—so that they will never be in a position to assert themselves) to ethnic cleansing and genocide against populations considered to be a threat. And when you oppose it, the TPLF will say “you committed a genocide against Tigrayans” over and over and over, and its western backers will repeat the same chorus. If they have been this loud over a non-existent genocide over the past twelve months, just imagine what it would be like if the U.S. or UN rewards them with that label.
And this is where the Ethiopian government’s major dilemma comes from: if ENDF and
Amhara forces fight to regain their cities and towns, they risk committing large scale massacres. The TPLF networks reported to be operating within these cities wear civilian clothing and fire at the armies from inside civilian establishments, in an apparent attempt to set up pro-Ethiopia forces. Pro-Ethiopia forces are essentially being dared to commit large scale massacres in order to win back their own cities. So far, they are choosing to withdraw from these towns and cities. But that is another problem: not only is the TPLF committing unspeakable violence against civilians and destroying infrastructure in those cities, the takeovers are emboldening it to continue pressing, giving young people back in Tigray false hope that they are winning and—this is very important—the false idea that they are being “welcomed” by locals in those cities. Then more and more and more young Tigrayans are sent to their deaths.
So the Ethiopian government is stuck between a rock and a hard place. One option is
allowing its forces to do whatever it takes to take back territory, thereby offering protection to its citizens in Wollo and elsewhere, but also risking the “genocide” label by western governments who have been eagerly waiting for such an opportunity so that they can blackmail the government into submitting itself to their wishes on GERD and other issues. Option two is avoiding large scale violence and allowing the TPLF to take power in Addis Ababa and do to Ethiopia what it wishes. One of the things it might do to Ethiopia, according to its leaked strategy document, is force a confederation that will no doubt privilege some states, i.e. Tigray, more than others, and that will no doubt be designed to subdue some populations—mainly Amharas and Afaris—who are considered obstacles to Tigray’s aspirations of domination and expansion (in the TPLF’s original manifesto, Afar is claimed as Tigray land).
And there is absolutely no doubt that the TPLF will make big concessions on the GERD in
order to compensate its western and Egyptian backers, if not redraw borders to make Benishangul Gumuz Tigrayan territory. If you think this is wild, read about the history of the state of Israel, the TPLF’s model state. The redrawing of borders that the TPLF undertook in 1991 was also wild at the time; people don’t think of it as outrageous anymore because the fact that they held onto the territory for 30 years has normalized the event in our minds. And that’s all the TPLF needs: another thirty years to normalize all the outrageous things they will do next.
One may argue that this is a false dichotomy, that there is a third or even maybe fourth option: winning these cities back without mass violence much in the same way the ENDF managed to do during its first campaign in Tigray. We all should pray for such a miracle, of course. However, one can also say that in the early days of the war, the TPLF was mostly withdrawing from Tigrayan cities to avoid urban warfare. And even when they engaged in urban warfare, it was not at the same scale and intensity as has been the case over the past four and half months or so. Starting in mid June, the TPLF’s use of civilians as human shields and fighters stopped being just another weapon in its arsenal and became a center of its operations. The near collapse of the ENDF inside Tigray right before its withdrawal was precipitated by the TPLF’s intensified use of “civilians” to trap the ENDF. Many ENDF soldiers chose to surrender rather than fire at those “civilians.” It is still possible to avoid large scale violence in the attempt to retake towns in Wollo, but the risk for it is very high, and is possibly behind the federal government’s reluctance to take decisive actions.
The point is: barring miracles, the Ethiopian government is positioned to lose something
one way or another. All that is left is choosing its preferred poison. Perhaps one thing to consider for the federal government is: the rights of Amharas and Afaris to defend themselves against the existential threats posed against them by the TPLF is much bigger than the national government’s concerns about its place and relationships with the rest of the world. If the federal government decides to risk the disintegration of Ethiopia, like it has done so far either due to incompetence or severe fear of committing large scale violence, that is fine for the federal government. But when you allow that disintegration to happen, please don’t leave the people of Amhara and Afar in a vulnerable position, unable to defend themselves and their lands. If we must return to the State of Nature, at least give these two peoples, who have so far shed more blood than anyone else in defense of their country, a chance to preserve their lives and their lands. Give them the resources they need to defend themselves before it is too late for them even if you feel it is too late for Ethiopia. Anything less is just a continuation of the gross criminal negligence that the federal government has been guilty of so far.
-
EBS Mogachoch9 years ago
[New] EBS Drama Series – Mogachoch : ሞጋቾች | Episode 7
-
Articles9 years ago
Ethiopia’s renewable energy revolution shouldn’t fail to empower its poor
-
News2 years ago
መንግሥት ከሕወሓት ይልቅ ለአገሪቱ ሥጋት የሆኑ ሌሎች ችግሮች አሉብኝ አለ
-
Opinions2 years ago
On the TPLF’s Love Affair With ‘Genocide’
-
Music4 years ago
2019 ESFNA Atlanta: Ethiopian Day – Ethiopia Hagerachin : ኢትዮጵያ ሀገራችን
-
Music4 years ago
2019 #ESFNA Atlanta: Ethiopian Day | Neway Debebe – Hageren Alresam : ሀገሬን አልረሳም
-
Articles8 years ago
ሰበር ዜና፦ ተዋናይት ሰብለ ተፈራ (ትርፌ) በመኪና አደጋ ህይወቷ አለፈ
-
Bahilawi Zefenoch10 years ago
Bahilawi Zefenoch – ባህላዊ ዘፈኖች
Anonymous
May 15, 2014 at 5:37 pm
ever Right!!!
Anonymous
May 15, 2014 at 5:36 pm
Mimi Don’t give up you are the one who scarifies for reality.
Anonymous
May 15, 2014 at 5:34 pm
You are the Great Daughter of Ethiopia! Long Live!
Anonymous
May 15, 2014 at 5:32 pm
Bravo Mimi the fighter for truth!
Anonymous
May 15, 2014 at 5:31 pm
WOYANE, WOYANE, WOYANE …………………yes the sign of EVER Peace and Strength!
Anonymous
May 10, 2014 at 3:12 pm
Azo whodam ayzoshi and ken skay wedanchi ymetal jib jib jib jib neshi weyane
Tesfa
May 9, 2014 at 9:28 pm
die bitch!
Mekonen
May 9, 2014 at 6:28 pm
I just don’t get it why most comments are emotional, if we can;t express ourselves better to keep quiet than insulting each other!!!
Sara
May 9, 2014 at 6:24 pm
Well said !
Sara
May 9, 2014 at 6:24 pm
Well said
Anonymous
May 9, 2014 at 4:35 pm
do have personal behavior for yourself
Genet
May 9, 2014 at 12:04 pm
Bravo MIMI.
Anonymous
May 9, 2014 at 11:34 am
Mimi u r the best
Anonymous
May 9, 2014 at 9:08 am
asfdsdsfsdff
Anonymous
May 9, 2014 at 8:40 am
horror yehonech set, wechuam westuam
Anonymous
May 9, 2014 at 8:13 am
mejemrya anchi gazetagn hugni ena sil muyaw taworyalesh
Anonymous
May 9, 2014 at 7:23 am
I like her confidence and maturity!
youuuu
May 9, 2014 at 7:15 am
ወደር የሌለሽ ጨ ካ ኝ
IIT
May 9, 2014 at 6:17 am
i like her justification