Uncategorized
የህዳሴው ገደል እምን ላይ ደረሰ?

አውሮፕላን መጣ እየገሰገሰ
በዘፈን አንደኛ ሙሉቀን መለሰ
(እስከመቸ ድረስ ጥላሁን ገሰሰ)
የህዳሴው ገደል እምን ላይ ደረሰ? Lol
የህዳሴውን ግድብ ወደ “ህዳሴው ገደል” ያሸጋገረውን ስምምነት የፈረመው ሰውየ“ እጁን ለቁርጥማት፤ ደረቱን ለውጋት“ እንዲዳርገው በመመረቅ ወደ ሰላምታየ እገባለሁ፡፡ እንዴት ናችሁ፤ ያልታደላችሁ? እኔ በህይወቴ በተለያየ ጊዜ ተስፋ ቆርጫለሁ፡፡ እንደ ዘንድሮ ተስፋን፤ ከሻኛውና ከፍሪምባው አፈራርቄ የቆረጥሁበት ጊዜ አልገጠመኝም፡፡
መንግሥትም ሃያ አመት ሙሉ አጥሮ፤ ሃያ ዓመት ሙሉ ቆፍሮ የተሳካለት ኣይመስልም ፡፡ “በየቦታው እንምሳለን፡፡ ለመጭው ትውልድ ነዳጅ ሳይሆን ጉዱጓድ እናወርሳለን” የሚል ነው የሚመስለው፡፡ የዛሬ አስራ አምስት አመት ገደማ ውሃ ማቆር የተባለ ፕሮጀክት ነድፎ ነበር፡፡ እናም ኅብረተሰቡ በየጓሮው ሮቶ ሮቶ የሚያክል ጉድጓድ እየቆፈረ የዝናብ ውሃ እንዲያቁር ትዛዝ ተላልፎለት ነበር፡፡ ከዚያ በኋላ ውጤቱ ምንድን ነበር? የየሰፈሩ ሰካራም በየጉድጓዱ እየገባ አለቀ ፡፡ ይሁን እንጂ መንግሥት፤ ስንት ሰካራም አጥንቱን የከሰከሰበትን ፤ ደሙን ያፈሰሰበትን ፕሮጄክት ድንገት ሰረዘ፡፡ በጊዜው የተወሰኑ ሰዎች ለዶማና ላካፋ መግዣ በሚል ወፍራም በጀት አስለቅቀው ከድህነት ተላቀቁ ፡፡ አገሪቱ ግን የግዜር ገበጣ መጫወቻ መስላ ቀጠለች፡፡ የውሃ ማቆር ፕሮጀክሩ ቢቀጥል ኖሮ ዛሬ የህዳሴውን ገደል ለመሙላት ግብጽን አንለማመጥም ነበር፡፡
መንግስት ደከመኝ ሰለቸኝ ሳይል የማይፈጽመውን እያቀደ፤ አዲስአበቤም ደከመኝ ሰለቸኝ ሳይል በችግሩ እየቀለደ፤ ሃያ አምስት አመት ተገባደደ፡ ፡በውቄም ስኮላርሺፕ በሚል ሰበብ፤ ማንነታቸው ያልታወቀ ፌዴራል ፖሊሶች የሚወረውሩት ቦምብ ወደማይደርስበት ቦታ ተሰደደ፡፡ በግንቦት ወር ወደ አገሩ ሲመለስ ችግር ይገጠመው ይሆን?ወይስ በእጃችን እንይጠፋብን ብለው ይተውት ይሆን? ቀጣዩን ክፍል በመጭው ግንቦት ይጠብቁ፡፡ግን መንግስትን መተቸት ህገመንግሥታዊ መብቴ መሆኑ ይሰመርበት ፡፡ በርግጥ ህገመንግስቱ እንደ ኣዲስ ኣበባ ምግብ ቤቶች Menu ነው፡፡ የተጻፈውን በተግባር ስትፈልገው አታገኘውም፡፡
በነገራችን ላይ ጠቅላይ ምኒስትር ኃይለማርያም ደሳለኝ የሆነ መጽሄት ላይ “ያመቱ ሰው” ተብለው መሸለማቸውን ሰምቼ ተደስቻለሁ፤ ሲያንሳቸው ነው፡፡ ይሄን ያክል እየተተረበ፤ ይሄን ያክል እየተሰደበ፤ ይሄን ያክል ከታችም ከላይም ንቀት እየተከናነበ ቆሞ መሄድ የቻለ ሰው፤ ሽልማት አነሰው?
እኔም እንሆ፤ ሰሜን አሜሪካ ጫፍ አርፌ
በጀርባየ የካናዳን የጉም ግድግዳ ተደግፌ
ከጢሜ ላይ የኮካኮላ ጤዛ ፤ከኪቦርዴ ላይ በረዶየን አራግፌ
“የኢትዮጵያ ህዝብ ሆይ ተባብረህ ተነስተህ ላንዴና ለመጨረሻ ግዜ አምባገነኑን ሥርአት ገርስስ” እያልሁ ነጋሪት ስደልቅ ፤አዲስ አበቤም “ወይ ኦን ላይን ያለ ሰው!” እያለ በኔ ላይ ሲስቅ፤ ጀምበር ”ሎግ አውት” አድርጋ ጥልቅ፡፡
ባለፈው 53 የፖለቲካና የሃይማኖት ድርጅቶች መግለጫ አውጡ ሲባል ስቄ ልሞት፡፡ ያሁላ ፓርቲ ቢሮ አለው? ወይስ ህልሙን ባሮጌ ሳምሶናዊት ሸክፎ የሚዞረው ሁሉ ተቆጥሮ ነው?ግሩም ነው መቸም፡፡ ኢትዮጵያ በቀንድ ከብት አንደኛ ሆና ወተት ይርባታል ፤ አምሳ ሦስት የፖለቲካ ፓርቲ ኖሯት ፖለቲካው ቸግራታል፤ እንዲያው ምን ይሻላታል?
ድሮ የኔ ቢጤ ባይተዋር ሰው ሲጨንቀው ሰላም ፍለጋ ወደ ቸርች ነበር የሚሄደው፡፡ አሁን በየቤተክስያኑ ድብድብ ነው፡፡ እዚያ ዲሲ ቤተክስያን ልትስሚ ከሄድሽ በነጠላሽ ላይ የጥይት መከላከያ መደረብ አለብሽ ፡፡ እነ አባባ ቆባቸው በሮ እስኪሄድ ሲከታከቱ ታዝበሽ፤ ከተወረወረ መቋሚያ በመትረፍሽ ኣንድየን አመስግነሽ፤ ወደ ቤትሽ ትመለሻለሽ፡፡ ባገር ቤት፤ ቤተክርስትያን ውስጥ አንድ ቄስ በዲያቆናት ሲታጀብ፤ የዲሲ አበሻ ቄሶች ግን በፖሊስ ታጅበው ነው የሚቀድሱ፡፡ እንዲያውም የፈረንጅ ፖሊሶች ለግልግል እየተጠሩ ቤተክስያኑን ከማዘውተራቸው የተነሣ ቅዳሴውን ለምደው ተሰጥኦ ሁሉ መቀበል ጀምረዋል፡፡
በነገራችን ላይ ላገራችን የገጠር ቄስ ክብር አለኝ፡፡ “ዳዋ ጥሶ፤ ጤዛ ልሶ፤ ድንጋይ ተንተርሶ፤ ግርማ ሌሊትን፤ ጸብአ አጋንንትን ታግሶ ፤የሚኖር ነው፡፡ የዲሲ ቄስ በበኩሉ ሙዳየ ምጽዋት አፍሶ፤ አይስክሬሙን ልሶ ፤የንስሃ ልጁን ጡት ተንተርሶ ፤ በቴስታ ተከሳክሶ ይኖራል የሚል ሀሜት አለ፡፡
የዛሬውን የህትመት ዳሰሳየን የምቋጨው በመሬት “ ትንታኔ“ ነው፡፡ ያዲስ አበባ የመሬት ችግር የመነጨው ከዘጠና ሰባት በኋላ ይመስለኛል፡፡ ጌቶች በነዋሪው ተስፋ ስለቆረጡ፤ በስልጣናቸውም ዋስትና ስላጡ፤ “ኪስህ ነው የቅርብ ወዳጅህ” የሚለውን ዘፈን ማንጎራጎር መረጡ፡፡ ይህንን ዝንባሌ እኔና ቢጤዎቼ የቀኝ አዝማች ሰውነቴ “ ሲንድረም ”ብለን እንጠራዋለን፡፡
ቀኛማች ሰውነቴ ከደብረማርቆስ ባላባቶች አንዱ ነበሩ፡፡ እና በስድሳ ስድስቱ አብዮት ዋዜማ የጭሰኞቻቸውን መሬት ጆሮ ጆሮውን ብለው ካቲካላ ጠጡበት ፡፡ባላባት ጓደኞቻቸው ለምን እንዲያ እንደሚያረጉ ሲጠይቋቸው“ መሬት ሳትበላኝ ልብላት ብየ ነው” አሉ ይባላል፡፡
ትንታኔውም ይቀጥላል፡፡
Articles
24ኛው የዓለም ግማሽ ማራቶን ሻምፒዮና በፖላንድ ግድኒያ ይካሄዳል

ኢትዮጵያውያን አትሌቶች ከምስራቅ አፍሪካ አቻዎቻቸው ጋር ለአሸናፊነት ይፎካከራሉ
በባልቲክ ባሕር ዳርቻ የምትገኘው ትንሿ የፖላንድ ወደብ ከተማ ግድኒያ በሀገራት መካከል የሚካሄድ የዓመቱ ብቸኛ ዓለም አቀፍ የአትሌቲክስ ውድድር የሆነውን እና ከሰዓታት በኋላ የሚጀመረውን የዓለም ግማሽ ማራቶን ሻምፒዮና ለማስተናገድ ዝግጅቷን አጠናቃለች፡፡ ስመ ጥር አትሌቶች የተካተቱበትና ከ250 በላይ ተሳታፊዎች የሚፎካከሩበት ይህ ሻምፒዮና የዓለም አትሌቲክስ ስፖርት አፍቃሪያን አይኖች ዳግም በምስራቅ አፍሪካውያኑ ኮከቦች ላይ እንዲያተኩሩ እንደሚያስገድድ ይጠበቃል፡፡ በሴቶቹ ውድድር ሴቶች ብቻ የተሳተፉበት ሩጫ የዓለም ሪኮርድ ባለቤቷ ኬንያዊት ፐሬስ ጄፕቺርቺር እና በወንዶች አሯሯጭነት የተመዘገበ የዓለም ሪኮርድ ባለቤት የሆነችው ኢትዮጵያዊቷ አባበል የሻነህ፤ በወንዶች በቅርቡ የ5000 ሜትር እና 10000 ሜትር የዓለም ሪከርዶችን የሰባበረው ኡጋንዳዊው ጆሹዋ ቼፕቴጊ እንዲሁም ኢትዮጵያዊው ጉዬ አዶላ ከሌሎች ተፎካካሪዎቻቸው በመላቅ በፖላንዷ የባህር ዳርቻ ከተማ ላይ የወርቃማ ድል አሻራቸውን ለማሳረፍ ተስፋ ከሚያደርጉት ከዋክብት መካከል የሚጠቀሱ ናቸው፡፡

ከ2010 ዓ.ም. ወዲህ አዲስ አሸናፊ አትሌት የሚጠበቅበት የወንዶቹ ፉክክር
ከ2006 ዓ.ም. ወዲህ ከተካሄዱት ዘጠኝ የዓለም ግማሽ ማራቶን ሻምፒዮና የወንዶች ውድድሮች ከአንዱ በስተቀር ሁሉም ድሎች በኤርትራዊው ዘርሰናይ ታደሰ (5) ወይም በጆፍሬይ ካምዎሮር ስም የተመዘገቡ ናቸው፡፡ ዘርሰናይ እና ካምዎሮር በግዲኒያ የማይገኙ በመሆኑም ውድድሩ ከ2010 ዓ.ም. ወዲህ ለመጀመሪያ ጊዜ አዲስ የወርቅ ሜዳያ አሸናፊ ስም የሚመዘግብ ይሆናል፡፡ በግዲኒያ የወንዶቹ ፉክክር ማስጀመሪያ ሽጉጥ ሲተኮስ አይኖች ሁሉ ትኩረታቸው ከዚህ በፊት በ21.1 ኪ.ሜ ርቀት ላይ ተወዳድሮ በማያውቀው የወቅታዊ ምርጥ ብቃት ባለቤት ኡጋንዳዊ አትሌት ጆሹዋ ቼፕቴጊ ላይ ይሆናል፡፡ ኡጋንዳዊው ምንም እንኳን የግማሽ ማራቶን ውድድር ልምድ ባይኖረውም ባለፈው እና በዘንድሮ ዓመት በተለያዩ ውድድሮች ካሳየው ድንቅ ብቃት አንፃር እንደሚጠበቀው ሆኖ እንደሚገኝም ይገመታል፡፡ ከቅርብ ዓመታት ወዲህ በኡጋንዳ አትሌቶች ላይ እየታየ የመጣው የብቃት መሻሻል ከዚህ ቀደም ብብርቱ ተፎካካሪነት ከሚታወቁት ኢትዮጵያ እና ኬንያ አትሌቶች በተጨማሪ የዓለም የግማሽ ማራቶን ሻምፒዮና የወንዶቹን ፉክክር ይበልጥ እንደሚያደምቀው ይጠበቃል፡፡ የኡጋንዳ የወንዶች ቡድን በግማሽ ማራቶን ውድድር የመጀመሪያ ተሳትፎውን በሚያደርገው ጆሹዋ ቼፕቴጊ የሚመራ ሲሆን ሌላኛው ተጠባቂ አትሌት ጃኮብ ኪፕሊሞ፣ አቤል ቼቤት እና ሞሰስ ኪቤትንም አካቷል፡፡
በወንዶቹ ፉክክር ኢትዮጵያውያን አትሌቶችም የቼፕቴጊ ብርቱ ተፎካካሪዎች እንደሚሆኑ ተገምቷል፡፡ በኢትዮጵያ በኩል ሳይጠበቅ ድንቅ ውጤቶችን በማስመዝገቡ ረገድ መልካም ስም ያለው ጉዬ አዶላ ለወርቅ ሜዳያ ድሉ ከተገመቱት መካከል አንዱ ሆኗል፡፡ እ.ኤ.አ. በ2014 በዴንማርክ ኮፐንሀገን ከተካሄደው የዓለም ግማሽ ማራቶን ሻምፒዮና በፊት ብዙም እውቅና ያልነበረው ቢሆንም የራሱም ምርጥ ሰዓት ከሁለት ደቂቃ በላይ ባሻሻለበት 59፡21 የነሐስ ሜዳልያ አሸናፊ ለመሆን መብቃቱ ይታወሳል፡፡ በዚያው ዓመት መገባደጃ ላይም የወቅቱን የዓለም ግማሽ ማራቶን እና የዓለም አገር አቋራጭ ሻምፒዮን ጆፍሬይ ካምዎሮር በዴልሂ የግማሽ ማራቶን ፉክርር የራሱን ምርጥ ሰዓት 59.06 በማስመዝገብ ጭምር አሸንፎታል፡፡ ለመጀመሪያ ግዜ በሮጠበት የ2017 የበርሊን ማራቶን ውድድር ላይ ሁለተኛ ሆኖ ሲያጠናቅቅ በመጀመሪያ ተሳትፎ የተመዘገበ የምንግዜም ፈጣን የሆነ 2:03:46 ሰዓት ያለው ጉዬ አዶላ በፖላንዱ የግማሽ ማራቶን ላይ ለመሳተፍ ከተመዘገቡት አትሌቶች መካከል የርቀቱን ሶስተኛ ፈጣን ሰዓት የያዘም ነው፡፡
በጉዬ አዶላ በሚመራው የኢትዮጵያ ቡድን ውስጥ የግማሽ ማራቶን ፉክክርን ከ60 ደቂቃ በታች ለመጨረስ የበቁና ልምድ ያላቸው አንዳምላክ በልሁ (59:10)፣ ልዑል ገብረስላሴ (59:18) እና አምደወርቅ ዋለልኝ (59:22) እንዲሁም ለዚህ ውድድር መምረጫ በሀገር ውስጥ የተካሄደው የ15 ኪሎ ሜትር ውድድር አሸናፊው ሀይለማሪም ኪሮስ (1:01:08) ተካተዋል፡፡
የወንዶቹ ፉክክር ያለፉት ሶስት ሻምፒዮናዎች የተናጠል የወርቅ ሜዳልያ ድልን በጆፍሬይ ካምዎሮር አማካይነት አላስቀምስ ያለው የኬንያ የወንዶች ቡድን ዘንድሮም በጠንካራ አትሌቶች የተወከለ ሲሆን በግል የወርቅ ሜልያ ድል ተስፋውን የጣለውም የ2020 የፕራግ ግማሽ ማራቶን ሻምፒዮን በሆነው ኪቢዎት ካንዲዬ እና የ2017 የዓለም አገር አቋራጭ ሻምፒዮና የብር ሜዳልያ አሸናፊው ሊዮናርድ ባርሶቶን ላይ ነው፡፡ ማውሪስ ሙኔኔ፣ በርናርድ ኪፕኮሪር እና በርናርድ ኪሜሊም ሌሎቹ የኬንያ ተወዳዳሪዎች ናቸው፡፡
ሁለቱን የዓለም ሪኮርድ ባለቤቶች የሚያገናኘው የሴቶቹ ፉክክር
እ.ኤ.አ. ከ2011 ጀምሮ ዓለም አቀፉ የአትሌቲክስ አስተዳዳሪ አካል ቤሰቶች የጎዳና ላይ ፉከክሮች ሁለት አይነት የሪኮርድ አመዘጋገብን መከተል ከጀመረ ወዲህ የግድኒያው የዓለም ግማሽ ማራቶን ሻምፒዮና የሴቶች ውድድር በታሪክ ለመጀመሪያ ጊዜ ሁለቱን የርቀቱ የዓለም ሪኮርድ ባለቤቶች የሚያፎካክር ይሆናል፡፡ የሴቶቹ ውድድር ከዓለም ሪኮርድ ባለቤቶቹ ኬንያዊቷ ፐሬስ ጄፕቺርቺር (ሴቶች ብቻ የሮጡበት ሪኮርድ ባለቤት) እና ኢትዮጵያዊቷ አባበል የሻነህ (ሴቶች ከወንዶች ጋር የሮጡበት የዓለም ሪኮርድ ባለቤት) በተጨማሪ ያለፈው የዓለም ግማሽ ማራቶን ሻምፒዮን ኢትዮጵያዊቷ ነፃነት ጉደታም የአሸናፊነት ክብሯን ለማስጠበቅ የምትፎካከርበት ነው፡፡
በ2016 ካርዲፍ ላይ የተካሄደው የዓለም ግማሽ ማራቶን አሸናፊነት ገድልም ያላት የ27 ዓመቷ ኬንያዊት ፐሬስ ጄፕቺርቺር በ2017 እና 2018 በወሊድ ምክንያት ከውድድር ርቃ ከከረመች በኋላ በ2019 ባደረገቻቸው ውድድሮች ወደ ምርጥ አቋሟ መመለሷን አሳይታለች፡፡ ያም ሆኖ በ2016 በተፎካከሩበት የዴልሂ ግማሽ ማራቶን በጄፕቺርቺር ላይ የበላይነቱን የወሰደችው ኢትዮጵያዊቷ አባበል የሻነህ በግዲኒያም ብርቱ ተፎካካሪዋ እንደምትሆን አያጠራጥርም፡፡ በ2013 የሞስኮ ዓለም ሻምፒዮና እና በ2016ቱ የሪዮ ኦሊምፒክ የ10000 ሜትር እና 5000 ሜትር ተሳትፎዋ ብዙም አመርቂ የሚባል ውጤት ያላስመዘገበችው አባበል ከዛ በኋላ አብዛኛውን ግዜዋን ለጎዳና ላይ ሩጫዎች ሰጥታ ስትሰራ ቆይታለች፡፡ ከተሳተፈችባቸው አስራ ሁለት የግማሽ ማራቶን ውድድሮችም በአስሩ የመጀመሪያዎቹን ሁለት ደረጃዎች በመያዝ ማጠናቀቅ የቻለች ሲሆን ባለፈው ዓመት በተወዳደረችበት የቺካጎ ማራቶን ላይም የራሷ ምርጥ በሆነ 2፡20፡51 ሰዓት ሁለተኛ ሆና ጨርሳለች፡፡
የግድኒያው የሴቶች ግማሽ ማራቶን ዓለም ሻምፒዮና ሌላኛዎቹ የትኩረት ማዕከሎች ሁለቱ የከዚህ ቀደም ሪኮርድ ባለቤት እንዲሁም ከሁለት ዓመት በፊት በስፔን ቫሌንሲያ በተካሄደው የዓለም ግማሽ ማራቶን ሻምፒዮና የወርቅ እና የብር ሜዳልያ አሸናፊዎች ኢትዮጵያዊቷ ነፃነት ጉደታ እና ኬንያዊቷ ጆሴሊን ጄፕኮስጋይ ናቸው፡፡ ነፃነት ከሁለት ዓመት በፊት በቫሌንሲያ የቅድመ ውድድር ተጠባቂዋ ጄፕኮስጋይን በማስከተል ሻምፒዮን ስትሆን የገባችበት ሰዓት ሴቶች ብቻ የሮጡበት ሪኮርድ ባለቤት አድርጓት ነበር፡፡ ሆኖም ከዛ በኋላ ግን ላለፉት ሁለት ዓመታት አንድም የግማሽ ማራቶን ውድድር ማሸነፍ አልቻለችም፡፡ ጄፕኮስጋይ አሁንም ሙሉ በሙሉ ሪኮርዶችን ወደሰባበረችበት የ2017 ዓ.ም. ድንቅ አቋሟ መመለስ ባትችልም ባለፈው ዓመት በመጀመሪያ የማራቶን ውድድር ተሳትፎዋ የኒው ዮርክ ማራቶንን ለውድድር ስፍራው ሪኮርድ በቀረበ ሰዓት ለማሸነፍ ችላለች፡፡ ሁለቱ አትሌቶች ባለፉት ሁለት ዓመታት አቋማቸው እምብዛም አመርቂ የነበረ ባይሆንም የግድኒያውን ውድድር ዳግም ወደውጤት ከፍታ የሚወጡበት መድረክ ለማድረግ የሚችሉትን ሁሉ እንደሚያደርጉ ይጠበቃል፡፡
በኢትዮጵያ እና ኬንያውያን አትሌቶች መካከል ብርቱ ትንቅንቅ እንደሚደረግበት በሚጠበቀው የሴቶቹ ውድድር በኢትዮጵያ በኩል ከአባበል እና ነፃነት በተጨማሪ ያለምዘርፍ የኋላው፣ ዘይነባ ይመር እና መሰረት ጎላ የሀገራቸውን ሰንደቅ በዓለም አደባባይ ከፍ እንዲል ለማድረግ የሚፎካከሩ አትሌቶች ናቸው፡፡ በኬንያ በኩልም ሮዝመሪ ዋንጂሩ፣ ዶርካስ ኪሜሊ እና ብሪሊያን ኪፕኮኤች በጉጉት የሚጠበቀውን ድል ለማሳካት ከጄፕቺርቺር እና ጄፕኮስጋይ ጎን እንዲሰለፉ የተመረጡት አትሌቶች ናቸው፡፡
የኮሮና ቫይረስ በፍጥነት በዓለም ዙሪያ እየተስፋፋና አሳሳቢነቱ እያደገ በመምጣቱ ምክንያት በርካታ ዓለም አቀፍ የአትሌቲክስ ውድድሮች እንዲሰረዙ ተደርገዋል፡፡ በዓለም አቀፉ የአትሌቲክስ አስተዳዳሪ (ወርልድ አትሌቲክስ) የበላይ ተቆጣጣሪነት እ.አ.አ. በማርች 29/2020 ሊካሄድ ፕሮግራም ተይዞለት የነበረው የዓለም ግማሽ ማራቶን ሻምፒዮና ለመካሄድ የበቃውም በኮሮና ቫይረስ ወረርሺኝ ምክንያት ለኦክቶበር 17/2020 እንዲተላለፍ ተደርጎ ነው፡፡
በዘንድሮው ውድድር ላይ በ2014 ዓ.ም. ያስመዘገበችውን የወርቅ ሜዳልያ ድል ጨምሮ ባለፉት አስር የዓለም ግማሽ ማራቶን ሻምፒዮናዎች የቡድን የሜዳልያ ድል ተቋዳሽ የሆነችው ኤርትራ እንዲሁም ባለፉት 23 የዓለም ግማሽ ማራቶን ሻምፒዮናዎች ላይ ያለማቋጥ ተሳታፊ የነበሩት ጃፓን እና አሜሪካ ለመሳተፍ አትሌቶቻቸውን ሳያስመዘግቡ ቀርተዋል፡፡ ካናዳም ውድድሩ ሊካሄድ ጥቂት ቀናት ሲቀሩት ያስመዘገበቻቸውን አትሌቶች በኮሮና ቫይረስ ስጋት ምክንያት ወደ ፖላንድ እንደማትልክ አሳውቃለች፡፡
* የዓለም ግማሽ ማራቶን ሻምፒዮና አሜሪካ፣ ዩናይትድ ኪንግደም፣ ካናዳ እና ጣሊያንን ጨምሮ ከአስተላላፊዎች ጋር በተናጥል ስምምነት ከተደረሰባቸው 22 ሀገሮች በስተቀር በወርልድ አትሌቲክስ የዩቲዩብ ቻናል ለመላው ዓለም በቀጥታ ይተላለፋል፡፡
Uncategorized
የኢትዮጵያ ቀን በዋሽንግተን ዲሲ በ’ታላቁ የአፍሪካ ሩጫ’ ዝግጅት ሊከበር ነው – Interview with Dr. Gashaw Abeza
Uncategorized
#Ethiopia: EthioTube ከስፍራው – Town Hall in DC on Addis Politics – Opening Speech by Ermias Legesse
-
EBS Mogachoch8 years ago
[New] EBS Drama Series – Mogachoch : ሞጋቾች | Episode 7
-
Articles9 years ago
Ethiopia’s renewable energy revolution shouldn’t fail to empower its poor
-
News2 years ago
መንግሥት ከሕወሓት ይልቅ ለአገሪቱ ሥጋት የሆኑ ሌሎች ችግሮች አሉብኝ አለ
-
Opinions1 year ago
On the TPLF’s Love Affair With ‘Genocide’
-
Music4 years ago
2019 ESFNA Atlanta: Ethiopian Day – Ethiopia Hagerachin : ኢትዮጵያ ሀገራችን
-
Music4 years ago
2019 #ESFNA Atlanta: Ethiopian Day | Neway Debebe – Hageren Alresam : ሀገሬን አልረሳም
-
Articles8 years ago
ሰበር ዜና፦ ተዋናይት ሰብለ ተፈራ (ትርፌ) በመኪና አደጋ ህይወቷ አለፈ
-
Bahilawi Zefenoch10 years ago
Bahilawi Zefenoch – ባህላዊ ዘፈኖች
anania
January 5, 2016 at 10:52 am
I wish u use the power of your pen to correct minor shortcomings and reinforce the works which are in process of doing. compare Ethiopia with other African states just don’t compare with the land you are living which has a history of more than 400 years development. u r blind with hatred!!! i advice u just write jokes not politics u r not liable to write such staffs while u r living thousands away.
Anonymous
January 4, 2016 at 1:45 pm
YeBewuketu fes ayigebam yemil Comment anebebiku libel…
Anonymous
January 4, 2016 at 10:37 am
it is correct but upto when u write only problem why u r not put a sol/n for the problem
Anonymous
January 4, 2016 at 8:44 am
I actually appreciate the way you write and the ability of attract readers tension. but let me ask you one thing , you are a friend of temesgen desalegne ? and u used to write on fethe newspaper? i was one of good follower of this news paper and i know all writers mentality there. starting from the owner desalgne , the others reporters Hailemeskel shewayelahe and i think mulene , the supporter writes like prof. mesfin , Aboy from mekelle ,Dr bedelu wakijera, eferem seyom…so on. all this writers were dareful persons and heroes. because they always write gov dt problems like political,economical, social while facing all the gov, warning here at under nose of Ethiopian gov. for me this is how heroes and freedom lovers fight . you are instead never write when u are in Ethiopia like u are writing now. i don’t have a problem with ur idea and hence but you are fearful person. i don’t like those who are there in america and push us to fight against this gov. you scarify your toung while we scarify our blood.
Teddy
January 4, 2016 at 8:43 am
Dude!keep up the good work and keep us informed .
Anonymous
January 4, 2016 at 6:49 am
aleka gebrehanan astawosegn
Anonymous
January 4, 2016 at 5:56 am
Great !!
Anonymous
January 4, 2016 at 5:00 am
like
Ojulu Lero
January 4, 2016 at 12:54 am
Gud eko new keep up the good work and keep us infor.
hun
January 3, 2016 at 8:50 pm
welcome back bewke miss ya betam
Anonymous
January 3, 2016 at 6:38 pm
Wore bicha atawura iwunetunim iyetenagerkina iyegeletsik
Essay ase
January 3, 2016 at 3:04 pm
Hodam
Anonymous
January 3, 2016 at 3:01 pm
Hodam
Temesgen
January 3, 2016 at 1:06 pm
fesam ante neh DEnkoro!!!!
Anonymous
January 3, 2016 at 12:33 pm
zembeleh atelefelef fesam
Dagim Bekele
January 3, 2016 at 11:35 am
Ymechal
murazha
January 3, 2016 at 11:15 am
to be continue lol!!!!!
eskiyalef yalefal
Anonymous
January 3, 2016 at 11:14 am
yy
Anonymous
January 3, 2016 at 10:12 am
Yebwqetu tenshe temchetognal