Articles
ከሁሉም በላይ የሀገርንና የህዝብን ደህንነትና አንድነት ይቅደም!! – በዲያስፓራ የዓረና መድረክ ደጋፊዎች የተሰጠ የጋራ አቋም መግለጫ

ከሁሉም በላይ የሀገርንና የህዝብን ደህንነትና አንድነት ይቅደም!!
በዲያስፓራ የዓረና መድረክ ደጋፊዎች የተሰጠ የጋራ አቋም መግለጫ
በኢትዮጵያ በተለያዩ ቦታዎች እንደ ሰደድ እሳት እየተቀጣጠለ በመሄድ ላይ የሚገኘው ህዝባዊ ተቃውሞና ብሶት በማስመልከት በውጭ ዓለም የሚኖሩ የዓረና መድረክ ደጋፊዎች ከተለያዩ ቦታዎች ሰሞኑን ባደረጉት አስቸኳይ የቴሌ ኮንፈረስ ውይይት የሚከተለውን ባለስምንት ነጥብ የጋራ የአቋም መግለጫ ለመላ ኢትዮጵያውያን አስተላልፏል።
ዓይናቸውን በፍቅረ ንዋይና በስልጣን ጥምነት የተሰወሩ አምባ ገነኖች የትም ይብቀሉ የትም ተመሳሳይ ባህርይ አላቸው። ዙሪያቸውን በወታደራዊ ሐይል ተከቦ ሲያዩት ዓለምን በመዳፋቸው ውስጥ ያስገቡት ይመስላቸውና ልባቸውን በትዕቢትና በትምክህት ስለሚሞላ ነፃነትና ፍትሕ ከሌለ ነገ ፈራሽ መሆኑን ከታሪክ አይማሩም። ሰብኣዊ ርህራሄና የይቅርታ መንፈስ የላቸውም። የህልውናቸውን መሰረት ሕብረተሰቡን በዘር፣ በጥቅምና በሀይማኖት ለያይተህ ግዛ የሚል ስለሆነ የህዝቡን ነፃ እንቅስቃሴ፣ አንድነትና መደራጀት ከጦር በላይ ይፈሩታል። ራሳቸውን ልዩ ፍጡራንና ጀግኖች አድርገው በመመልከት ከሀገርና ከሕግ በላይ በመሆን የህዝቡን ጭኾትና ህይወት የዶሮን ያህል ግምት አይሰጡትም። የዓይን ብሌየናቸው ገንዘብና ስልጣን ስለሆነ የሀገርንና የወገንን ፍቅር የላቸውም። በርስትነት በያዙት የብዙሃኑ መገናኛ አማካኝነት ነጋ ጠባ የሚያስተጋቡት መዝሙርና የጉራ ነጋሪት በለው፣ ፍለጠው፣ ርግጠው፣ ቁረጠው፣ ግደለው ከሚል ቀረርቶ በስተቀር የህዝቡን ብሶት የማዳመጥና አርቆ የማየት ዓቅም፣ ሞራል፣ ብቃትና ተፈጥሮ የላቸውም። ይህ በመሆኑም የህዝቡን ዓመፅ ቤተ መንግስታቸው አፋፍ ላይ ደርሶ እንደ እሳተ ጎመራ እስከሚለበልባቸው ድረስ ተቻችሎና ተከባብሮ አብሮ ከመኖር ይልቅ እኔ ከሞትኩ ሰርዶ አይብቀል በማለት እስከመጨረሻ ህልፈታቸው ድረስ መሟሟትንና መተላለቅን ይመርጣሉ። ሀገርንና ህዝብን አጥፍቶ መጥፋት ማለት ትርጉሙ ይኸው ነው።
የህወሓት/ኢሕአዴግ መንግስትም ከአምባ ገነናዊ ተፈጥረው በመነሳት 90 ሚሊዮኑን የኢትዮጵያ ህዝብ በማግለልና የበይ ተመልካች በማድረግ ሀገሪትዋን ጠቅልሎ በሞኖፓል እየገዛ ይገኛል። ተቃውሞ ያነሳ ዜጋ ሁሉ በአግባቡ ከማስተናገድና ዴሞክራሲያዊ መፍትሔ ከመሻት ይልቅ ልክ ትናንት ደርጋውያን በመውደቂያቸው ዋዜማ ያሳይዋቸው የነበረ የቀቢፀ ተስፋ እርምጃዎችና ፉኮራዎች ዛሬም በተመሳሳይ መልኩ የመብት ጥያቄ ያነሱትን ዜጎች ሁሉ የተለያዩ የቂጥያ ሰሞችን በመለጠፍ የሻዕቢያ ተላላኪ፣ ሽብርተኞች፣ የደርግ ስርዓት ናፋቂዎች፣ ትምክህተኞች፣ የጎዳና ነውጠኞች፣ ቦዘኔዎች፣ ነፍጠኞች፣ ወዘተ በማለት ፍትሓዊ ጥያቂያቸውን በማናናቅና በማፈን ወታደራዊ የሐይል እርምጃው ትግራይን ጨምሮ በተለያዩ አካባቢዎች ሲተገብር ቆይቷል።
የተከበርከው የትግራይ ህዝብና መላው ወገናችን ይህ የሐይል እርምጃና የመብት ረገጣ ዛሬ በኦሮምያና በአማራ ክልሎች ብቻ የተጀመረ ሳይሆን በተለይም የትግራይ ህዝብ ነፃ አውጪ ነኝ የሚለው ህወሓት በአስር ሽዎች ሰማእታት የወደቁበትን የትግል አላማ ከህዝቡ እጅ ነጥቆ በመውሰድ ጥቂት በቤተሰብ: በጋብቻና በትውልድ ሐረግ የተሳሰሩትን ዘመድ አዝማድ መሪዎች ጥቅም ማስጠበቂያ በማድረግ የህዝቡንና የሰማእታቱን አደራ የበላ ድርጅት ነው። ዛሬ በትግራይ ምድር “እኔ ኢትዮጵያዊ ዜጋ ነኝ” ወይም ትግራዋይ ነኝ ብለህ በነፃነት ኰርተህ ለመረማመድ ቀርቶ እንደ ሰብኣዊ ፍጡር በህይወት ለመኖርም አስቸጋሪ የሆነበት ጊዜ ነው። እንደ መሪዎቹና ካድሬዎቻቸው አመለካከት ከሆነ በትግራይ የህወሓት ደጋፊ ያልሆነ የክልሉ ተወላጅ እንደ ትግራዋይ ተደርጎ ስለማይታይ ዴሞክራሲያዊ መብቱን ብቻ ሳይሆን ስብእናውን፣ ዜግነቱንና ማንነቱንም ጭምር የተነጠቀ ነው። ይህንን የህወሓት የሰብኣዊ መብት ረገጣን በመቃወም በተለያየ ጊዜ በክልሉ በተንቤን ዓቢይ ዓዲ፣ በነበለት፣ በእምባስነተይ፣ በሁለት አውላዕሎ፣ በእግሪ ሐሪባ፣ በዓዲ ረመፅ፣ በብዘትና በሌሎች ወረዳዎች ላይ የተደረጉትን የህዝቡን የተቃውሞ ሰላማዊ ሰልፎች በወታደራዊ ሐይል ከመበተንና ከማጥቃት አልፎ ሰልፉን አስተባብሯል የተባሉትን ግማሾቹ አምልጠው ወደ ስደት ሄዷል ሌሎቹ ደግሞ የት እንደገቡ የማይታወቅ የውሃ ሽታ ሆነው ቀርቷል። ቤተሰቦቻቸውንም እንደውሻ ከያሉበት እየታደኑ ታስሯል: ተሰዷል: አሊያም ደብዛቸው ጠፍቷል። ሌላ ቀርቶ ምርጫ መጣ በተባለ ቁጥርናበዋዜማው በመላ ትግራይ እስከ አፍንጫውን የታጠቀ መደበኛ ሰራዊትን በማዝመትና አካባቢውን በጥይት ጭኾት ነጎድጓድ በማደንቆር ሻዕቢያ ባንተ ላይ ሊዘምት ተንቀሳቅሷል እያሉ ህዝቡን በማሸበርና በማስደንገጥ የምርጫ ጎሮጀውን ከህዝቡ እጅ በአፈ ሙዝ ነጥቀው በመውሰድ መቶ በመቶ አሸንፈናል ይላሉ።
ከዚህም በላይ የፍትሕ፣ የነፃነትና የዴሞክራሲ ጥያቄን በማንሳት በሕግ ተመዝግበው: የህዝቡን ልዕልና አክብረው: ሰላማዊና ሕጋዊ ትግል አምነው: ሕገ መንግስቱ የፈቀደላቸውን መብት መሰረት አድርገው በመታገል ላይ በሚገኙት የዓረና ትግራይ ለሉዓላዊነትና ዴሞክራሲ ፓረቲ አባላት ላይ እየደረሰ ያለው በደል ስንመለከትም ህወሓት ምን ያህል የሰብኣዊ ፍጡር ደመኛና ባላንጣ መሆኑን ቁልጭ አድርጎ ያሳየናል። በትግራይ የተለየ አመለካከት መያዝ ወይም የዓረና ትግራይ ደጋፊ መሆን ማለት እንደ ነውር ወይም እንደወንጀለኛ ስለሚያስቆጥር ከማሰር፣ ከመግደልና ከማፈን አልፈው “የዓረና አባል ለሆነ ትግራዋይ ሁሉ እሳት እንዳታስጨሩ፣ ሲሞት እንዳትቀብሩ፣ ልቅሶ እንዳትደርሱ፣ በሃዘንም ሆነ በደስታ ከነርሱ ጋር በአካል እንዳትገናኙና እንዳትቆሙ፣ በተገኘው አጋጣሚ ሁሉ አግልሏቸው” የሚል ማሕበራዊና ሀይማኖታዊ ውግዘት እንዲደርስባቸው ያደርጋሉ። በመላ አባላቱ ላይ የከፈቱትን የስነ ልቦናዊ ጦርነት አልበቃ ብሏቸው በሆዳቸውና በህልውናቸው ለመቅጣት ሲባልም የስራ ዕድል እንዳያገኙ: ሀብት እንዳያፈሩ: ሌላ ቀርቶ ከለጋሽ ሀገሮች የሚመጣውን የስንዴ እርዳታም ሳይቀር እንዳይሰጣቸው ይከለከላሉ። ገበሬ ከሆነ ማዳበሪያና ምርጥ ዘር እንዳያገኝ፣ የመንግስት ሰራተኛ ከሆነ ከስራው እንዲባረር፣ ተማሪ ከሆነ ተምሮ የስራ ዕድል እንዳያገኝና ከተለያዩ የትምህርት ዕድሎች እንዲታገድ፣ ነጋዴ ከሆነ ደግሞ ንግድ ቤቱን እንዲዘጋ አሊያም ከመጠን በላይ ግብር እንዲጫንበት እየተደረገ ይገኛል። በቤተሰብ ደረጃም ዘልቀው በመግባት ልጆቻቸው የዓረና አባል ሆነው የተገኙትን ወላጆች ይቀጣሉ። ሚስት ወይ ባል የዓረና አባል ሆኖ ከተገኘ ሚስቱ ባልዋን እንድትፈታ በማድረግ ቤተሰብ ያፈርሳሉ ይበትናሉ። ህዝቡን ሳይወድ በግድ አንድ ለአምስት በማደራጀት እርስ በርሱ እየተናከሰ እንዲኖር በማድረግ በተለይም የዓረና አባላትን የማጥቂያ መሳሪያ አድርገው እየተጠቀሙበት ይገኛሉ። በዚሁ አስከፊ የአፈና እርምጃ ምክንያት በተለይም ወጣቶቹ ያላቸው ምርጫ ሳይወዱ በግድ ባርነትን አሜን ብሎ ተቀብሎ መኖር ወይም ዓይኑን ጨፍኖ ወደ ስደት መፍለስ ነው። ከዚህ በላይ ጭካኔ! አረሜንነትና በደል ምን ሊባል ይችላል። እውነት ህወሓት የትግራይ ህዝብ ጠበቃና ነፃ አውጪ? ህሊናችሁን ይፍረደው።
ዛሬ በኦሮሞያ: በአማራና በሌሎች ቦታዎች የተነሳው ህዝባዊ እምቢተኝነትና የፍትሕ ጥያቄ በትግራይ ምድር እየተፈፀመ ካለው የመብት ረገጣና ኢፍትሓዊ እርምጃ የተለየ አይደለም። የኢሕአዴግ መሪዎች በተለይም ህወሓት የሁሉንም ቅራኔዎች: ጭቆናዎችና ዓፈናዎች መንሲኤ እነርሱ ራሳቸው ሆኖ ሳለ ዛሬም እንደለመዱት የማደናገሪያና የማጨበርበሪያ ተንኰላቸውን በመቀጠል የህዝቡን ጠበቃ በመምሰል በሌሎች ክልሎች የተነሳውን ህዝባዊ ተቃውሞ በትግራይ ላይ ያነጣጠረ የእልቂት ጦርነት በማስመሰል የሽብር ፕሮፓጋንዳ መርዛቸውን በማሰራጨት ላይ ይገኛሉ። ይሁን እንጂ ከመጋረጃው በስተጀርባ ያለው ተግባር ግን ሐቁ ሌላ ነው። ህወሓት ከተፈጠረባት ቀን አንስቶ እስካሁን ድረስ ስንመለከተው በዘረጋው የዓፈናና የለያይተህ ግዛ ፓሊሲ መሰረት ትግራዋይን እየገደለ ያለው ራሱ ህወሓትና አጋሮቹ ናቸው እንጂ ሌላ ባዕድ አይደለም። ትግራዋይን ሆን ብሎ ከኤርትራ ህዝብም ሆነ ከሌሎች አጎራባች ወንድሞቹ ጋር እሳት እየጫረ በጠላትነትና በጥርጣሬ ዓይን እንዲታይ ሌት ተቀን ጥረት እያደረገ ወገኖቻችንን ለግድያና ለቃጠሎ እንዲዳረጉ ምክንያት እየሆነ ያለው ራሱ ህወሓት እንጂ ሌላ አይደለም። ትግራዋይን ከቤት ንብረቱንና ከየመንደሩ እየተፈናቀለ ወደ ባህር ማዶና በየቦታው እየተጣለና እየተሰደደ ያለው የህወሓትን አድልዎና አፈና የፈጠረው ጠንቅ እንጂ ሀገሩንና ህዝቡን ጠልቶ አይደለም። ትግራዋይን በሻዕቢያ አለንጋ እየተገረፈ ከየቤቱ እየታደነና እየታፈነ መረብ ተሻግሮ ደብዛው እንዲጠፋ ምክንያት እየሆነ ያለው ራሱ የትግራይ ህዝብ ነፃ አውጪና ጠበቃ ነኝ እያለ የሚመፃደቀው ህወሓት እንጂ ሌላ አይደለም። እንደነ ታደሰ አብርሃንና አረጋዊ ገብረዮሐንስን የመሳሰሉት ወጣት የዓረና መሪዎች የገደለና እነ አብርሃ ደስታን ጨምሮ በመቶዎች የሚቆጠሩ የድርጅቱን አባላትና ደጋፊዎች የተለየ አመለካከት ስለያዙ ብቻ እስር ቤት አጉሮ እያሰቃየና እያሳደደ ያለው ራሱ ህወሓት እንጂ ሌላ አይደለም። ህወሓት ራሱ ባመጣው ጣጣ ሻዕቢያ የትግራይ ህዝብን በወረረ ጊዜ ፈጥኖ ደራሽ በመሆን ከእልቂት ያዳነው ራሱ የትግራይ ህዝብን ጨምሮ ጠቅላላ ኢትዮጵያዊ እንጂ ህወሓት ብቻውን አይደለም። በሚሊዮን የሚቆጠረው ትግራዋይ በመላ ኢትዮጵያ ሀብትንና ንብረትን መስርቶ እየኖረ ያለው ህወሓት የቸረው መብት ሳይሆን ለዘመናት አብሮ ተፋቅሮ የቆየና የገዛ ሀገሩ መሆኑን ስለሚያቅ ነው። ትግራይም የትግርኛ ተናጋሪ ብቻ ሳትሆን የሌላውን ወገን አጥንት የተቀበረባት የሁሉም ኢትዮጵያዊ መሬት ናት። ስለዚህ የትግራይ ህዝብ ጠበቃና መድህን 90 ሚሊዮኑ የኢትዮጵያ ህዝብ እንጂ በምንም መልኩ ጠላቱ ሊሆን አይችልም። ስለዚህ በአጠቃላይ ለትግራዋይ ከህወሓት በላይ ጨቋኝና አፋኝ ስርዓት የለውም ቢባል ማጋነን አይሆንም።
የተከበራችሁ ውድ ኢትጵዮያውያን በሙሉ ከላይ የተጠቀሱትን ሐቆች እንደተጠበቀ ሆኖ በቅርቡ በኦሮሚያ፣ በአማራና በሌሎች አካባቢዎች የተደረጉትን ህዝባዊ ሰልፎች በአመዛኙ በመላ ሀገሪቱ ላይ ያሉት ችግሮች ተመሳሳይ ስለሆኑ ትግላቸው የሚደገደገፍ ነው ብለን እናምናለን። ይሁን እንጂ እኛም ሆነ ሌሎች ተመሳሳይ ቁስል ያላቸውን ጭቁን ወገኖች የትግሉን አጋር በመሆን በሙሉ ልባችንና ዓቅማችን እንዳንሳተፍ የሚያደርጉ አግላይ: ከኢትዮያዊነት ስነ ምግባርና ሃላፊነት ውጭ የሆኑትን አስጊ አዝማሚያዎችና ተግባራት ሲፈፀሙ ስናይ እጅጉን አሳዝኖናል። የሚያሳዝነውም ድርብ ድርብርብ ጉዳት ስላለው ነው። አንደኛ ድርጊቱ የጭቁኖች ኢትዮጵያውያንን የትግል አንድነት የሚያላላና የሚያዳክም ነው። ሁለተኛ በየአካባቢ የተነሳውን የህዝቡን እምቢተኝና እየተከፈለ ያለውን አኩሪ መስዋእትነት መንገዱንና አቅጣጫውን በማሳሳት እንደተለመደው ተዳፍኖና ደመ ከልብ ሆኖ እንዲቀር የሚያደርግ ነው። ሶስተኛ እነዚህ በማወቅም ሆነ ባለማወቅ የሚደረጉ ስህተቶች ዞሮ ዞሮ ተጠቃሚ የሚሆነው ፍትሕ የጠማውን ህዝብ ሳይሆን እኛን በዘርና በሀይማኖት ከፋፍለው እርስ በራሳችን አናቁረውና በታትነው በጭቁኖች ደም እነርሱ ዘላለማዊ ስልጣናቸውን አደላድለው ለመኖር የሚፈልጉ አምባ ገነን መሪዎችንና ተከታዮቻቸውን የሚያጎለብት ነው። አራተኛ እየተፈፀመ ያለው የተዛባ ተግባርና እንቅስቃሴ በቂም በቀልና በጥላቻ ላይ የተመሰረተ ስለሆነ በዘር ማጥፋት ወንጀለኝነትንም ጭምር የሚያስጠይቅ ጥቁር የታሪክ ጠባሳ ነው። አምስተኛ ሀገርን የሚበታትን ከመሆኑም በላይ የእርስ በርስ እልቂትን የሚጋብዝ ስለሆነ በአስቸኳይ እንዲቆም እንጠይቃለን። ይህንን አደገኛ አዝማሚያ በሰላማዊ መንገድ እንዲፈታና እንዲገታ ለማድረግም የፓለቲካ ድርጅቶች፣ የሀይማኖት አባቶች፣ ሲቢክ ማሕበረ ሰቦች፣ ምሁራን፣ ወጣቱ ትውልድና ጠቅላላ በሀገር ውስጥም ሆነ በውጭ ዓለም የሚኖሩት ሀገር ወዳድ ኢትዮጵያውያን ሁሉ የሰላም ትብብራቸውን እንዲያሳዩ ወገናዊ ጥሪያችንን እናቀርባለን። እዚህ ላይ መሰመር ያለበት ዓቢይ ጉዳይ ይህ የተዛባና መንገዱን የሳተ: በጥቂት ቡድኖች አነሳሽነት እየተፈፀመ ያለው ፀረ ህዝብና ፀረ አንድነት ተግባር ጨዋውና የዋሁን የአማራና የኦሮሞ ህዝብ ተግባር ነው ብለን ፍፁም አናምንም። ትናንትም: ዛሬም ሆነ ነገ በምንወደው በአማራውና በኦሮሞው ህዝባችን ላይ ያለንን ልባዊ ፍቅር: ፅኑ እምነትና አክብሮት ፍፁም አይለውጠውም። ተራራን የሚያህል የጋራ ጠላት ፊት ለፊታችን ተጎልቶ እያለ ነገር ግን የጀመርነውን ትግል በዋናው ዓቢይ ጉዳይ በጋራ ጨቋኞቻችን ላይ ያነጣጠረ እንዳይሆን መንገዳችንን በማሳሳት እነሱ በሚሰጡን አጀንደ ላይ ተጠምደን ነገ ሁላችንም በእኩል የሚያስተናግድና ድምፃችንን የሚሰማ ስርዓት ሲረጋገጥ እግረ መንገዳቸውን ሊፈቱ በሚችሉ ጥቃቅን ጉዳዮች ላይ በማትኮር ራሳችን በራሳችን ትግላችንን የሚጎዳ ተግባር መፈፀም ማለት ለጠላቶቻችን ዱላ ማቀበል ማለት ነው የሚሆነው።
ይህን ዓይነቱ ስሜት የወለደው ስህተት ደግሞ እውነተኛ የወገንና የሀገርን ፍቅር ካላቸውና ነገ ሁሉንም ብሄር ብሄረሰቦች በእኩል የሚስተናገዱባት: ነፃነትዋንና የግዛት አንድነትዋን የተጠበቀች: አንዲት የበለፀገች ዴሞክራሲያዊት ኢትዮጵያን እንድትረጋገጥ ከሚመኙና ከሚታገሉ ሐይሎች ይመነጫል ብለን ፍፁም አናምንም። ምክንያቱም በሀገራችን የነበረውና አሁን ያለው ታሪካዊና ነባራዊ እውነታ የሚያረጋግጥልን አንድና አንድ ብቻ ነው። እሱም ኢትዮጵያ እንደ ሀገር እውን እንድትሆንና ነፃነትዋንና ክብርዋንም ጠብቃ እስከ ዛሬ ድረስ እንድትኖር ያደረጉዋትና የመስዋእትነትን ዋጋ የከፈሉላት አንገፋና አናሳ ሳይባባሉ ሁሉም ብሄር ብሄረሰቦች ናቸው። ስለዚህ አንዱን ዘር በማግለል ወይም በመጥላት ነገ ሁላችንም የምንመኘው ፍትሕ: ነፃነት: ዴሞክራሲና ሰላም በፍፁም ሊረጋገጥ አይችልም ብቻ ሳይሆን ኢትዮጵያ የምትባል ሀገርንም መኖር አትችልም። በዘር ጥላቻና በሀይማኖት ላይ የተመሰረተ ፓለቲካዊ እንቅስቃሴ ውጤት ሊኖረውና የሀገርንና የህዝብን ሉዓላዊ ክብርና አንድነት ሊያስጠብቅ እንደማይችል ሩቅ ሳንሄድ በጎሮቤቶቻችንና በሌሎች ሀገሮች እየተካሄዱ ያሉትን አውዳሚ ክስተቶች ጉልህ አብነቶች ናቸው። በኛ እምነት ሀገር ማለት ህዝቡን ነው። ኢትዮጵያም የህዝቡን የትግል ቃል ኪዳን ውጤት ናት። በመሆኑም ህዝብዋን እየጠሉ ሀገር ወዳድ መሆንና ሀገር አለኝ ማለት አይቻልም። የሀገራችንን የአንድነት ሞሶሶ ተጠብቆ እንዲቆይ ያደረገው ዋናው ሚስጢሩም በመተማመን: በመከባበር: በመቻቻል: በመፈቃቀድ: በመረዳዳትና በመፈቃቃር ላይ የተመሰረተ የሁሉም ብሄር ብሄረሰቦች የአንድነት ቃል ኪዳን ነው። ከዚህ ውጭ አሁን ከደረስንበት 21ኛው የሰለጠነ ዘመንና የዓለም ህዝቦች ከጠባብ መንደራቸውን አልፈው በሁሉም መስክ በጋራ ጥቅምና በሰጥቶ መቀበል መርሕ ላይ የተመሰረተ አብሮ መኖር በጀመሩበት መዋእል ላይ እየኖርን ነገር ግን ይህን ሐቅ ማየት የተሳናቸው እንደገና እኛን ወደሗላ ወደ 16ኛው የመሳፍንት ዘመን መልሰው በዘርና በህዝብ ቆጠራ ላይ የተመሰረተ ስርዓት በመትከል ትልቁን ዓሣ ትንሹን ዓሣ እየበላና እየረገጠ የሚኖርባት ኢትዮጵያ እንድትሆን የሚመኙት ሐይሎች ፍፁም የማይሆንላቸው መሆኑን አውቀው በአስቸኳይ ከስህተታቸውንና ከሗላቀር ድርጊታቸውን እንዲታቀቡ ጥሪያችንን እናቀርባለን።
የተከበራችሁ ታጋይ ሐይሎችና ሲቪክ ማሕበረሰቦች አሁን በሀገራችን ያለው ሁኔታ ለሕግ ተገዝ የሆነ መንግስትና በሕግ የሚዳኝ ሕብረተሰብ በሌለበት፣ ሓላፊነት የሚሰማው መንግስትና የአመራር ብቃት ያላቸው የፓለቲካ መሪዎች በሌሉበት፣ ህዝብና መንግስት እሳትና ጭድ ሆነው በተፋጠጥ በቆሙበት፣ በአጠቃላይ ሀገራዊ የትግል አንድነት ባልተፈጠረበትና መልክ ባልያዘበት ሁኔታ ላይ እያለን ይህ ዓይነቱ የፓለቲካ ቀውስ መከሰቱ እጅግ የሚያሳስብና ፈታኝ ጊዜ ነው። ሰው እየሞተ ነው። በሽዎች የሚቆጠሩ ወጣቶችን ከማንም ጊዜ በላይ እየታፈሱ እስር ቤት እየተወረወሩ ናቸው። ሰዎች በማያውቁት ጉዳይ ላይ ጥቃት እየደረሰባቸውና ቤት ንብረታቸውን እየተው እየተፈናቀሉ ናቸው። ይህን ሁሉ ተደምሮ ሲታይ የሀገርንና የህዝብን ጥያቄ መልስ የሚሰጥና መስመር የሚያስይዝ ባሌቤት በማጣት ትልቅ የአመራር ክፍተት ተፈጥሯል። ሁኔታው በዚሁ ከቀጠለ ደግሞ ሀገሪቱን ወደ ባሰ የፓለቲካ ቀውስና ብጥብጥ ልታመራ እንደምትችል የሚያጠያይቅ አይደለም። ስለሆነም ይህንን አስፈሪ ሁኔታና የእልቂት ድባብ ለመለወጥ ህዝብ: መንግስትና ሌሎች ታጋይ ሐይሎች ሚና ምን መሆን አለበት? ለሚለው ጥያቄ ትእግስት: ጥበብ: በሳል: ብቃት: የነቃና የተዋሃሃደ ጥረት የሚጠይቅ ታሪካዊ ሓላፊነት የተጣለባቸው መሆኑን በሀገሪትዋ ያለውን ሁኔታ ራሱ ተናጋሪ ነው።
የኢሕአዴግ መንግስት አሁን ያለበት ሁኔታ ስናይ የህዝቡን ድምፅ ሰምቶ ዴሞክራሲያዊ መፍትሄ ለመስጠት የሚያስችል ዓቅምና ተፈጥሮ እንደሌለው ራሱም ጭምር እያመነ ነው። ዛሬ በስልጣን ላይ ያሉት የስርዓቱን መሪዎች ብቃትና ራእይ ማነስ ብቻ ሳይሆን ለራሳቸው የግል ጥቅማቸውን በማሳደድ ላይ የተጠመዱ ስለሆኑ ስለሀገርና የህዝብ ችግር ለማሰብ ጉዳያቸውም አይደለም። በአሁኑ ጊዜ ሓላፊነት የሚሰማው የመንግስት አካል ማን ነው ብለህ ለማወቅ አስቸጋሪ የሆነበት ጊዜ ነው ያለው። የመንግስት አካላትን ስንመለከት ሁሉም የየራሱ ቡድናዊና ቤተሰባዊ መንግስት በመመስረት የየግሉን አጀንዳ ይዞ የሚሯሯጥ ነው። ህዝቡም በመንግስቱ ላይ አሜኔታ በማጣቱ በራሱ መንገድ መሄድ ጀምሯል። ሰሞኑን የኢሕአዴግ ፓሊት ቢሮ ያካሄደው አስቸኳይ ስብሰባም ገና ከጅምሩ ውጤት አልባ እንደሆነ ያወጣውን መግለጫና ጠቅላይ ሚኒስትሩ ሀይለማሪያም ደሳለኝ ራሳቸውም ለጋዜጠኞች የሰጡትን ቃለ ምልልስ ያመላክታል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ የነገሩን መርዶ ኢሕአዴግ አሁንም በራሱ ጎጆ አጥር ግቢ ውስጥ እየተሽከረከረ እንደሚቀጥል ነው። እንደ ጠቅላይ ሚኒስትሩ አገላለፅ መተካካት (ትራንስፎርመሽን) የሚሉትም ትርጉሙ አረጌውን ስርዓት ፓሊሱና ርእዮተ ዓለም እንዳለ ሆኖ ነባር የኢሕአዴግ አባልን በአዲስ የኢሕአዴግ አባል መተካት ማለት ነው። ስለዚህ የመልክ መቀያየር እንጂ የባህርይና ያስተሳሰብ ለውጥ አልተደረገም ሁለቱም ያው ናቸው። ይህ ዓይነቱ ንግግርና መግለጫ ደግሞ ላለፉት ሃያ ዓመታት የህዝቡን ጆሮ ያደነቆረና የሰለቸ አነጋገር ነው።
ኢሕአደግ እውነት ለለውጥ ቆርጦ የተነሳ ቢሆን ኖሮ የመርፌን ቀዳዳ ያህል የጠበበውን የፓለቲካ ምሕዳር በሩን በመክፈት በሀገራችን ጉዳይ ላይ እኛም ያገባናል የሚሉትን ተቃዋሚ የፓለቲካ ሐይሎችን ለማስተናገድና ለመሳተፍ የሚችሉበትን የብዙሃን ፓርቲ ስርዓት ተግባራዊ ባደረገ ነበር። ስለዚህ ጠቅላይ ሚኒስትሩ በመግለጫቸው የነገሩን ነገር ካለ አሁንም የህዝቡን ድምፅ ለማፈን ወታደራዊ ጡንቻቸው እንዲሚያጠናኩሩ ነው። ሌላው በፓሊት ቢሮው የወጣውን መግለጫ ያነበብነው የኢሕአዴግ መንግስትን የግለ መሪዎችን ጥቅም ማካበቻ አድርጎ መጠቀም የሰርዓቱን ዋነኛ አደጋ እንደሆነ ይጠቁማል። ይሁን እንጂ ሁሉም ባለስልጣን በየደረጃው በኪራይ ሰብሳቢነት ስኳር የተለከፈ ስለሆነ ማን በማን ላይ ደፍሮይዘምታል የሚል ጥያቄ ምልክት ነው። መንግስት እወስዳለሁ ያለውን እርምጃም ምናልባት ግምገማ በሚል ሰበብ ህዝቡን እርስ በርሱ ለማናከስና ትግሉን ለማቀዝቀዝ ወይም አንዳንድ ባለስልጣናትን ለመምታት ይጠቀሙበት ይሆናል እንጂ የተነሳውን አንገብጋቢና ስር የሰደደውን የህዝብ መሰረታዊ ጥያቄ የሚመልስ አይሆንም። ሁሉንም በአንድ ድርጅት የበላይነት ሞኖፓላዊ አስተሳሰብ በተጠመቁ ግለ መሪዎች መካከል ሹም ሽር በማድረግና ወንበርን በመቀያየር የሚፈታ ችግር አይኖርም። የችግሩን መንሲኤ የግለ ሰቦችን ጉዳይ ሳይሆን የስርዓቱን መበስበስና አፋኝ ፓለሲያቸውን የወለደው ችግር ነው። ስለዚህ የችግሩን ምንጭ የሆነውን የስርዓቱን ፓሊሲ ለውጥ ሳይደረግ አንድ አምባ ገነን መሪን በማባረር በሌላ ተመሳሳይ አስተሳሰብ ያለውን አምባ ገነን መሪ ቢተካ ነገ ተመልሶ ወደ ሌብነት መግባቱ አይቀሬ ነው። ምክንያቱም ህዝቡን የስልጣን ባለቤትነቱን ሙሉ በመሉ ሳይረጋገጥ ማለት ነፃና ገለልተኛ የሆኑትን የፍትሕ: የዳኝነት: የዴሞክራሲና የምርጫ ተቋማት እስከሌሉ ድረስ ኪራይ ሰብሳቢነትንና የስርዓቱን መበላሸት መዋጋትና መቆጣጠር አይቻልም። የኢሕአዴግ ስርዓት ባህርይም ካለፈው ልምዱን ስንመለከት ስር ነቀል የሆነ የተሃደድሶና የፓለሲ ለውጥ(reform) ማድረግ ማለት ራስህን በራስህ የመግደል (suicidal) እርምጃ አድርጎ ስለሚያየው ከእባብ እንቁላል እርግብ ይወለዳል ብለን አንጠብቅም።
ውድ ኢትዮጵያውያን እኛ የዓረና መድረክ ደጋፊዎች ይህንን የአቋም መግለጫ እንድናወጣ የተገደድንበት ዋናው ምክንያት በሀገራችን ውስጥ የተከሰተውን የፓለቲካ ቀውስና በወገኖቻችን ላይ እያስከተለ ያለውን የህይወትና የንብረት መጥፋት አደገኛ አዝማሚያን በሚመለከት ያለንን ስጋት በሀገር ውስጥም ሆነ በውጭ ዓለም ለሚኖረው መላ ወገናችን መልእክታችንን ለማስተላለፍ ነው።
- 1. ሰብኣዊና ዴሞክራሲያዊ መብታችን ይከበር!! ድምፃችን ይሰማ!! በማለት ሕገ መንግስቱ የሰጣቸውን መብት ተጠቅመው በሰላም አደባባይ ወጥተው አቤት ስላሉ ብቻ ወታደራዊ እርምጃ ተወስዶባቸው በየጎዳናው የወደቁትን ወገኖቻችን የተሰማንን ጥልቅ ሃዘን እንገልፃለን። የከፈላችሁትን አኩሪ መስዋእትነት ለፍትሕ፣ ለነፃነትና ለዴሞክራሲ የተከፈለ ዋጋ ነውና ታሪካችሁን ለዘላለም ህያው ሆኖ ይኖራል። በዚሁ አጋጣሚም ለቤተሰቦቻቸው፣ ለወዳጅ ዘመዶቻቸው ለመላ ህዝባችን መፅናናትን እንመኛለን።
- 2. ህዝቡ በተለይም ወጣቱ ትውልድ ፍርሓትን ሰብሮ አደባባይ በመውጣት ለመብቱ እያደረገ ያለው የሞት ሽረት ትግል መበረታታ አለበት ብለን ስለምናምን ድጋፋችንና የትግል አጋርነታችንን እንገልፃለን። ለወደፊትም ከዘር ጥላቻ፣ ከቂም በቀልና ከጠባብ አስተሳሰብ በፀዳ መልኩ፣ ሀገርንና የ90 ሚሊዮን ህዝብን ጉዳይ ማእከል ያደረገ፣ ሀቀኛ ኢትዮጵያዊነትንና እውነተኛ ህዝባዊ አላማን መሰረት አድርጎ በሚካሄደው የለውጥ እንቅስቃሴ ከህዝባችንና ከታጋይ ወገኖቻችንን ጎን በመሰለፍ የበኩላችንን ድርሻ ለመወጣት ዝግጁነታችንን በዚሁ አጋጣሚ ለመግለፅ እንወዳለን።
- 3. በስልጣን ላይ ያለው የኢሕአዴግ መንግስት ለተፈጠረው ችግር መንሲኤና ተጠያቂ ራሱ ሆኖ ሳለ ነገር ግን በሰላማዊ መንገድ አደባባይ ወጥተው የፍትሕ ጥያቄ ያቀረቡትን ዜጎች ድምፃቸውን በማፈን እየወሰደ ያለው ጭካኔ የተሞላበት ግድያ፣ የማሰርና የመመንጠር እርምጃ አጥብቀን እናወገዛለን። ድርጊቱንም በአስቸኳይ እንዲቆምና በዚሁ ሳቢያ እስር ቤት የታጎሩትን የህሊና እስረኞች እንዲፈቱ እንጠይቃለን። ለተፈጠረው ችግርና ለተፈፀመው ግድያም በገለልተኛ አካል ተጣርቶ በደለኞቹ ለፍርድ እንዲቀርቡ እንጠይቃለን።
- 4. መንግስት ለሀገርና ለህዝብ ድህንነት ሲባልና ለራሱ ህልውናም ሲል የሰላም እጁን በመዘርጋት የህዝቡን ድምፅ የሚስተናገድበት ነፃና ገለልተኛ የፍትሕና የዴሞክራሲ ተቋማትን በመዘርጋት፣ ህዝቡ በሕገ መንግስቱ የሰፈሩትን ሰብኣዊና ዴሞክራሲያዊ መብቶችን በመጠቀም መፃኢ ዕድሉን የሚወስንበት ነፃ የምርጫ ስርዓትን በማቋቋም: የፓለቲካ ምሕዳሩን ከላይ እስከ ታች በማስፋት: በአጠቃላይ ኢሕአዴግንም ጨምሮ የለውጡን አጋር የሚሆንበትን ሰላማዊ የስልጣን ሽግግር ለማደረግ የሚያስችል የተመቻቸ የፓለቲካ ሁኔታ በአስቸኳይ እንዲፈጥር አጥበቀን እንጠይቃለን።
- 5. መከላኪያ ሰራዊት የገባኸው ቃል ኪዳን ከሁሉም ገለልተኛና ነፃ ሆነህ ለሕገ መንግስቱ፣ ለሀገር ሉዓላዊነትና ለህዝብ ልዕልና ታማኝና ዘብ በመሆን የዜጎችን ድህንነት በእኩል ለመጠበቅ ነው። የሚከፈልህን ደመወዝም ሆነ የታጠቅከውን መሳሪያ ከጥቂት መሪዎች ኪስ የምታገኘው ጉርሻና ስጦታ ሳይሆን የጭቁኑ የኢትዮጵያ ህዝብ አንጡራ ሀብት ነው። ስለሆነም አንተ ከህዝብ አብራክ የወጣኸው የኢትዮጵያ ወታደር እየከሰመ በመሄድ ላይ የሚገኘውን አምባ ገነን ስርዓትና በተለይም በፍቅረ ንዋይ ታውረው ሐቁን ማየት የሳናቸውና መንገዱን ጠፍቶባቸው በመደነባበር ላይ የሚገኙትን መሪዎች ጥቅም ለማስጠበቅ ሲባል አፈ ሙዙን በጭቁኑ ህዝብ ላይ ከማነጣጠር ይልቅ ከህዝቡ ጋር ወግነህ የለውጡን አጋር እንድትሆን ወገናዊ ጥሪያችንን እናስተላልፋለን።
- 6. ተቃዋሚ የፓለቲካ ሐይሎች፣ ሲቢክ ማሕበረ ሰቦች፣ ምሁራን፣ የሀይማኖት አባቶችና የሚዲያ ባለሙያዎች በሙሉ!! በመካከላችን በብዙ ጉዳዮች ዙሪያ የተለያዩ መለስተኛ ልዩነት መኖር ባህሪያዊ ነው። ነገር ግን በእናት ሀገርና በህዝብ ህልውናና ደህንነት ላይ ግን ልዩነት ሊኖረን ፍፁም አይገባም። ስለሆነም ጥቃቅን ልዩነቶቻችንና ቅራኔዎችን ወደጎን በመተው ከሁሉም በላይ ”የሀገርንና የህዝብን ደህንነትና አንድነት ይቅደም “ በሚል የሀገር አድን የጋራ መፈክር ዙሪያ ተሰባስበን የአባቶቻችንን ወኔና ጀግንነት ዳግም በማደስ ለእናት ሀገራችን ትንሳኤ አብረን ዘብ እንድንቆም ጥሪያችንን እናቀርባለን።
- 7. መንግስትንና ህዝብን በውል ለይቶ ማየት ያቃታቸውን ቡድኖችና ግለ መሪዎች በጉዳዩ ላይ ምንም በሌለበትና ለራሱ በህወሓትና በሻዕቢያ በሁለት አለንጋ እየተገረፈ በባርነት ስር እየማቀቀ የሚገኘውን የትግራይ ህዝብ ከወንለኛ መሪዎች ጋር ደምረው በጀምላ በመጥላት የህዝቡን ስሜትንና ክብርን የሚነካ ተግባር ሲፈፅሙ ይገኛሉ። በመሆኑም ለረጅም ዘመናት አብሮ ተፋቅሮና ተዋልዶ በኖረው ወንድማማች ህዝብ መካከል ሆን ተብሎ በዘር ጥላቻ ላይ የተመሰረተ እንዲሆን በመገፋፋት አላስፈላጊ ግጭትና የእርስ በርስ መናቆር ለመፍጠር የሚደረገውን ማንኛውም ሕገ ወጥ ድርጊት አጥብቀን እናወግዛለን። አንዳንድ የመንግስት አካላትም ሆኑ ሌሎች ግለ ሰቦችና ቡድኖች ወጣቱን ትውልድ የሀገርንንና የወገንን ፍቅር ተላብሶ በመቻቻል አብሮ መኖርን ከማስተማር ይልቅ ጥላቻን በመስበክ በገዛ ወገኑ ላይ እንዲዘምት ከማድረግ እንዲታቀቡ አበክረን እንጠይቃለን።
- 8. የኢትዮጵያ ህዝብ! ባንተ ላይ ነጋ ጠባ ሲካሄዱት የቆዩትን አደናጋሪና ከፋፋይ የጥላቻ ፕሮፓጋንዳ በምንም ሳትበገር፣ መንግስታትና መሪዎች አላፊ ሀገርና ህዝብ ግን ነባሪ መሆናቸውን በፅናት በማመን ላሳየኸው ትዕግስትን: ጨዋነትንና ሃላፊነትን የተሞላበት አኩሪ ተግባርና ባህል ምስጋናችንንና አንድናቆታችንን ስንገልፅ ታላቅ ኩራት ይሰማናል። ስለሆነም ዛሬም እንደትላንቱ ዓለም ያደነቀውን የአትንኩኝ ባይነትህን: እንግዳ ተቀባይ ተምሳሌነትህንና የአንድነት ቃል ኪዳንህን ጠብቀህ ከስርዓቱ ጭቆናና አፈና ለመላቀቅ በምታደርገው ህዝባዊ ተጋድሎ ላይ እኛም እስከመጨረሻ ከጎንህ የምንቆም መሆናችንን በልበ ሙሉነት ለመግለፅ እንወዳለን።
እግዚአብሄር የሀገራችንን ሰላምና አንድነት ይጠብቅ
ምንጭ: Email
Articles
በኦስሎ ዳይመንድ ሊግ የ5000ሜ ፉክክር ኢትዮጵያውያን አትሌቶች በሁለቱም ፆታዎች በአሸናፊነት አጠናቀዋል

ትላንት ምሽት በኖርዌይ ኦስሎ በተከናወነው የዳይመንድ ሊግ 5000 ሜ. ውድድር ኢትዮጵያውያን አትሌቶች በወንዶችም በሴቶችም ከአንደኛ እስከ ሶስተኛ ያሉትን ደረጃዎች በመቆጣጠር አሸንፈዋል፡፡ በዝናባማ የአየር ሁኔታ ውስጥ በተካሄደው የሴቶች 5000 ሜትር ፉክክር ዳዊት ስዩም በመጨረሻዎቹ መቶ ሜትሮች ውስጥ ፍጥነቷን በመጨመር ጉዳፍ እና ለተሰንበትን ቀድማ አንደኛ ወጥታለች፡፡ የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ለኦሪገን 2022 የአለም ሻምፒዮና ከመረጣቸው ዕጩ አትሌቶች ዝርዝር ውስጥ ያልተካተተችው ዳዊት በኦስሎ ያሸነፈችበት 14፡25.84 የሆነ ሰአት የራሷ ምርጥ ሲሆን እጅጋየሁ ታዬ (14.12.98) እና ለተሰንበት (14፡24.59) ባለፈው ወር በዩጂን ካስመዘገቧቸው በመቀጠልም የዘንድሮ የአለም ሶስተኛው ፈጣን ነው፡፡ በውድድሩ ላይ ከነበሩት ሌሎች ኢትዮጵያውያን መካከል በዘንድሮው የውድድር ዓመት በርቀቱ የመጀመሪያ ተሳትፎዋን ያደረገችው አልማዝ አያና በ14:32.17 ስድስተኛ ሆና አጠናቃለች፡፡ ሀዊ ፈይሳ በ14:33.66፣ ፅጌ ገብረሰላማ በ14:43.90፣ እና አበራሽ ምንሴዎ በ14:47.98 በቅደም ተከተል ሰባተኛ፣ አስረኛ እና አስራ አንደኛ ሆነው ሲያጠናቅቁ ሶስቱም ያስመዘገቡት ሰዓት የራሳቸውን ምርጥ ያሻሻሉበት ሆኗል፡፡ ጥሩነሽ ዲባባ እ.ኤ.አ. በጁን 2008 ዓ.ም. ያስመዘገበችውና 14:11.15 የሆነው የኦስሎ ዳይመንድ ሊግ የሴቶች 5000 ሜትር የውድድር ስፍራ ሪከርድ ይሰበራል ተብሎ ተጠብቆ የነበረ ቢሆንም ሳይሳካ ቀርቷል፡፡

ዳዊት ስዩም ውድድሩን በድል ካጠናቀቀች በኋላ ለውድድሩ አዘጋጆች በሰጠችው አስተያየት ‹‹ዛሬ ለእኔ ደስታን ስላመጣልኝ በውድድሩ ሰዓት የነበረውን ዝናብ ወድጄዋለሁ ማለት እችላለሁ፡፡ ጠንካራ ተፎካካሪዎች የነበሩበት ከባድ ውድድር ነበር እናም ሁሉንም ለማሸነፍ በቅቻለሁ። በርቀቱ የራሴን ምርጥ ሰዓት ማሻሻል መቻሌም አስፈላጊ ነበር፡፡ በስታድየሙ ውስጥ በከፍተኛ ስሜት ድጋፍ ይሰጡን የነበሩ ወገኖቻችን ነበሩ። ለሰጡን ድጋፍ እናመሰግናለን።›› ብላለች፡፡ በኦስሎ የወንዶች 5000 ሜትር የመጨረሻ ፉክክሩ በኢትዮጵያውያኑ ጥላሁን ሀይሌ እና ሳሙኤል ተፈራ መካከል የነበረ ሲሆን ጥላሁን የ1500 ሜትር ስፔሻሊስቱ ሳሙኤልን በአጨራረስ ፍጥነት ቀድሞ በ13:03.51 በአንደኛነት አጠናቋል፡፡ ሳሙኤል ተፈራ የራሱ ምርጥ በሆነ 13:04.35 ሁለተኛ ሲወጣ ጌትነት ዋለ የግሉ የዓመቱ ምርጥ በሆነ 13:04.48 ሶስተኛ ደረጃን ይዞ ጨርሷል። በውድድሩ ላይ የነበሩት ሌሎች ኢትዮጵያውያን ሚልኬሳ መንገሻ በ13:05.94 አምስተኛ እንዲሁም አሊ አብዱልመናን የራሱ ምርጥ በሆነ 13:16.97 አስረኛ ወጥተዋል፡፡

ጥላሁን ሀይሌ ውድድሩን በአሸናፊነት ካጠናቀቀ በኋላ ለውድድሩ አዘጋጆች በሰጠው አስተያየት ‹‹ሶስት ኢትዮጵያውያን የመጀመሪያዎቹን ሶስት ደረጃዎች ይዘን መጨረስ መቻላችን ጥሩ አፈጻጸም ነበር። እየጠነከርኩ እንደሆነ የተሰማኝ ሲሆን በውድድሩ እና ባስመዘገብኩት ሰዓትም ተደስቻለሁ። ለረጅም ጊዜ ጉዳት ላይ ስለነበኩ ወደ አሸናፊነቱ መመለስ መቻሌ በጣም ጥሩ ነው።›› ብሏል፡፡
በኦስሎ የሴቶች 800ሜ. ውድድር ላይ ተፎካካሪ የነበረችው ኢትዮጵያዊቷ ድሪቤ ወልቴጂ በ1፡58.69 አምስተኛ ሆና አጠናቃለች።
Articles
የዘንድሮው የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ብሄራዊ ሻምፒዮና በእኔ እይታ

ከመጋቢት19-24/2014 ዓ.ም በሐዋሳ አለም አቀፍ ስቴድዮም የተደረገው 51ኛዉ የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ሻምፒዮና ከሞላ ጎደል ስኬታማ በሚባል ሁኔታ ተጠናቋል፡፡ ከአምስት አመት በኋላ በድጋሚ በአካል በመገኘት ስለተከታተልኩት የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ሀገር አቀፍ ሻምፒዮና የግል ምልከታዬን እንደሚከተለው አጠናቅሬዋለሁ፡፡ የበለጠ ትኩረትን በሳቡት ውድድሮች ዙሪያ የተመዘገቡ ውጤቶችን በወፍ በረር በመዳሰስ ስጀምር ከፍተኛ ፉክክር በታየበት የመጨረሻ ቀን የወንዶች 5000ሜ. የአለም ከ20 አመት በታች ሻምፒዮና የ3000ሜ የብር ሜዳልያ አሸናፊው አሊ አብዱልመና 13፡45.0 በሆነ ሰዓት ከጥላሁን ሀይሌ፣ ጌትነት ዋለ እና ዮሚፍ ቀጄልቻ ቀድሞ አሸናፊ ሆኗል፡፡ የፉክክሩ አካል የነበረው እና የርቀቱ የወቅቱ የአለም ሻምፒዮን ሙክታር እድሪስ ስድስተኛ ወጥቷል። ከ20 ዓመት በታች የ3000ሜ የአለም ሻምፒዮኑ ታደሰ ወርቁ በ28፡12.0 የወንዶች 10,000ሜ. ሻምፒዮን ሲሆን በ1996 ዓ.ም. በአትሌት ስለሺ ስህን ተመዝግቦ የነበረውን 28፡16.23 የሆነ የሻምፒዮናው ሪኮርድ ለማሻሻልም በቅቷል፡፡ በ10 ሺህ ሜትር የሴቶች ፉክክር ግርማዊት ገብረእግዚአብሔር በቀዳሚነት የጨረሰችበት 31፡21.5 የሆነ ሰዓት አዲስ የሻምፒዮንሺፕ ሪኮርድ ሆኖ ተመዝግቧል፡፡ በርቀቱ የከዚህ ቀደሙ ሪኮርድ ለተሰንበት ግደይ ከሶስት ዓመት በፊት ያስመዘገበችው 32፡10.13 የሆነ ሰዓት ነበር፡፡ ሳሙኤል ፍሬው በዘንድሮ የወንዶች 3000ሜ. መሰናክል አፈፃፀም ከአለም ሁለተኛው ፈጣን በሆነ 8፡22.5 ሰዓት አሸናፊ ሲሆን ጌትነት ዋለ ከአራት ዓመት በፊት አስመዝግቦት የነበረውን 8፡28.98 የነበረ የሻምፒዮናው ሪኮርድም አሻሽሏል፡፡ በሴቶች 3000ሜ. መሰናክል ከ800ሜ ወደ ረጅም ርቀት የተሸጋገረችው ወርቅውሃ ጌታቸው በ9፡41.8 ሰዓት መቅደስ አበበን (9:43.8) በማስከትል በአሸናፊነት አጠናቃለች። አድሃና ካህሳይ (3:51.0) የወንዶች 1500ሜ ፉክክሩን በበላይት ሲያጠናቅቅ በሴቶች 1500 ሜ አያል ዳኛቸው (4:10.0) ተጠባቂዋ ዳዊት ስዩምን (4:11.1) በመቅደም በአንደኛነት አጠናቃለች። በ800ሜ. ወንዶች ቶሌሳ ቦደና (1:47.1) በሴቶች ወርቅነሽ መሰለ (2:02.1) አሸናፊ ሆነዋል። ዮብሰን ብሩ በ400ሜ/400ሜ መሰናክል (45.9/50.5) ድርብ ድል ሲቀዳጅ፣ በወንዶች ጦር ውርወራ ኡታጌ ኡባንግ ብሔራዊ ሪኮርድ በሆነ 73.28ሜ. አሸንፏል፡፡ የኋልዬ በለጠው እና ዮሃንስ አልጋው በእርምጃ ሩጫ የሻምፒዮንነት ክብርን ተቀዳጅተዋል። ጥቂት አስተያየቶች፡- የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ስፖርት አፍቃሪ እንደሆነ እና ለዕድገቱ እንደሚቆረቆር ሰው በብሔራዊ ሻምፒዮናው ላይ ስለተመለከትኳቸው አዎንታዊ እና አሉታዊ ጎኖች ጥቂት አስተያየቶቼን እንደሚከተለው አስቀምጣለሁ፡- አዎንታዊ ጎኖች • ባለው ነባራዊ ሁኔታ ውስጥ ሊገጥሙ የሚችሉትን ተግዳሮቶች በሙሉ በመቋቋም ፌዴሬሽኑ ውድድሩን ከአዲስ አበባ ውጭ አካሂዶ በሰላም ማጠናቀቅ መቻሉ አንደኛው ስኬቱ ነው፡፡ • በሻምፒዮናው ላይ ጥቂት የማይባሉ ታዋቂ አትሌቶች በሀገሪቱ ትልቁ የአትሌቲክስ ፉክክር ላይ ተሳታፊ ሆነው ሲወዳደሩ መመልከት የተቻለ ሲሆን በተለይም በወንዶች 5000 ሜትር ፍፃሜ ላይ የታየው የኮከብ አትሌቶች ፉክክር ልዩ ነበር፡፡ • በውድድሩ ወቅት ለአትሌቲክስ ዳኞች የብቃት ማሻሻያ ስልጠና መሰጠቱም የውድድሩን ጥራት ለማሳደግ የሚረዳ እንደመሆኑ እሰየው የሚባል ነው፡፡ • እንደ ኢትዮ ኤሌክትሪክ ያሉት ክለቦች ለአትሌቲክስ ስፖርት የበለጠ ትኩረት በመስጠትና ተጠናክሮ በመቅረብ ከዚህ ቀደም በጠንካራነታቸው ከሚታወቁት መከላከያ እና ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ጋር የቅርብ ተፎካካሪ ሆነው መታየት፤ የኦሮሚያ ክልል፣ ደቡብ ፖሊስ እና ሲዳማ ቡና ክለብ አትሌቶችም ጠንካራ ተሳትፎ ሳይዘነጋ የሻምፒዮናው ፉክክር ድምቀት ነበሩ፡፡ • የአንዳንዶቹ ተገቢነት አጠያያቂ ቢሆንም ብዛት ያላቸው የሻምፒዮናው ሪኮርዶች የተሻሻሉበት ውድድርም ነበር፡፡ አሉታዊ ጎኖች • የሀገሪቱ ትልቁ የአትሌቲክስ ውድድር ውጤት አሁንም በኤሌክትሮኒክስ የሰዓት መቆጣጠሪያ የማይደገፍ መሆኑ በተለይም በአጭር ርቀት እና በሜዳ ላይ ተግባራት ውድድሮች ላይ የሚሳተፉ አትሌቶች ልፋት ተገቢውን እውቅና እንዳያገኝ እያደረገ ይገኛል፡፡ የሻምፒዮናውን ውጤቶች በዘመናዊ እና ዓለም አቀፉን መለኪያ በሚያሟላ መልኩ አለመያዝ በአህጉራዊ እና አለም አቀፋዊ ውድድሮች ላይ ለተሳትፎ የሚያበቁ ውጤቶችን በማስመዝገቡ ረገድ የሚኖረው አሉታዊ ተፅዕኖ ከፍተኛ መሆኑ ከግምት ውስጥ ገብቶ አሁንም መፍትሄ ያልተበጀለት ጉዳይ ነው፡፡ • የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ወደ ሚዲያ/ለአጠቃላዩ ሕዝብ የሚያስተላልፈው የመጀመሪያዎቹን ሶስት ደረጃዎች ይዘው የሚያጠናቅቁ አትሌቶችን ውጤት ብቻ መሆኑ አወዳዳሪው አካል የሚያደርገውን የራሱን ውድድርም ሆነ አትሌቶቹ የለፉበትን ውጤት ከማስተዋወቅ አኳያ በቂ አይደለም፡፡ • በወንዶች የጦር ውርወራ እና የሴቶች ምርኩዝ ዝላይ ብሔራዊ ሪኮርዶች እንደተመዘገቡ ይታመናል፤ በሴቶች 100ሜ መሰናክል እና የወንዶች 400ሜ መሰናክል የተመዘገቡት ሰዓቶችም የምንግዜውም ፈጣን ሊሆኑ ይችላሉ፡፡ ነገር ግን ውድድሩ በኤሌክትሮኒክስ ታይሚንግ ያልተደገፈ እና የንፋስ ንባብ ያልነበረው መሆኑ ውጤቶቹ በዓለም አቀፍ ደረጃ ተቀባይነት እንዳይኖራቸው የሚያደርግ ነው። • በ20 ኪ.ሜ የእርምጃ ውድድር ላይ በሁለቱም ፆታዎች የተመዘገቡት ሰዓቶች ከሚጠበቀው በላይ እጅግ በጣም ፈጣን እና እውነታዊ አለመምሰላቸው በውድድሩ ላይ የተፈጠረ አንዳች ስህተት መኖሩን የሚያመላክቱ መሆኑ፡፡ እንዲህ አይነት ለማመን የሚከብዱ እና ጥርጣሬን የሚፈጥሩ አይነት ውጤቶች ሲመዘገቡም የተፈጠረ ስህተት መኖር አለመኖሩን ለማጣራት አለመሞከሩ፡፡ • የሴቶች 10 ኪሎ ሜትር ውድድር ላይ ለውድድር የማይፈቀድ የጎዳና ላይ መሮጫ ጫማን በመጠቀም የተመዘገበ ውጤት በሪኮርድነት ጭምር ተይዞ መፅደቁ። ብሔራዊ ፌዴሬሽኑ ከተከለከሉ ጫማዎች ጋር የተያያዙ ዓለም አቀፍ ሕገ ደንቦችን ማወቅና መተግበር ቢገባውም በሴቶች 10 ሺህ ሜትር ውድድር ላይ የተከሰተው ነገር የውድድር ሕገ ደንቦቹ መረጃ በፌዴሬሽኑ ውስጥ በትክክል የተሰራጩ እንዳልሆነ የሚያመላከት ነው፡፡ • በሴቶች 1500 ሜትር የግማሽ ፍፃሜ ውድድር ላይ አትሌት ዳዊት ስዩም የሻምፒዮናውን ሪኮርድ ያሻሻለችበት ውጤት እንደተመዘገበ በውድድሩ ወቅት በተደጋጋሚ ሲነገር ከተደመጠ በኋላ ግልፅ ባልተደረገ ምክንያት ውጤቱ በሐዋሳው ውድድር ላይ ተሻሻሉ ከተባሉት የሻምፒዮናው አዲስ ሪኮርዶች ዝርዝር ውስጥ ሳይካተት መቅረቱም የፌዴሬሽኑን ግልፀኝነት ጥያቄ ምልክት ውስጥ የሚከት ነው፡፡ ከላይ የተዘረዘሩት አዎንታዊ እና አሉታዊ ጎኖች ለረጅም ግዜ የኢትዮጵያን አትሌቲክስ ስፖርት እንቅስቃሴዎች በቅርበት ከመከታተሌ አንፃር በራሴ እይታ ያስቀመጥኳቸው እንደመሆናቸው አንዳንዶቹ ሀሳቦች አከራካሪ ሊሆኑ ይችላሉ፡፡ ሆኖም የውድድር ደንቦችን በአግባቡ ከማስፈፀም አኳያ በታዩት ክፍተቶች ዙሪያ ምንም የሚያከራክር ጉዳይ ስለሌለ በወቅታዊ የውድድር ደንቦች ዙሪያ የግንዛቤ እጥረት ላለባቸው የስፖርቱ ባለድርሻ አካላት በሙሉ አስፈላጊውን ገለፃ እና ትምህርት መስጠት የፌዴሬሽኑ ኃላፊነት ነው፡፡ ከውድድር ጋር የተያያዙ ደንቦችን ከመጣስ አኳያ በሀገር ውስጥ በሚደረጉ ውድድሮች እንደቀላል ነገር የሚታለፉ ጉዳዮች በዓለም አቀፍ ውድድሮች ላይም ተደግመው እንደግል አትሌቶችን እንደቡድን ሀገርን ትልቅ ዋጋ ሊያስከፍሉ ይችላሉና አስፈላጊው ጥንቃቄ ቢደረግ መልካም ነው፡፡ ባለፈው መስከረም ወር በቪየና ሲቲ ማራቶን ውድድሩን በአሸናፊነት ጨርሶ የነበረው ኢትዮጵያዊው ደራራ ሁሪሳ የገጠመውን አንዘንጋው! ሀገራችን ኢትዮጵያን በመልካም ጎኑ ስሟ እንዲነሳ በሚያደርገው እና በትልልቅ ዓለም አቀፍ የውድድር መድረኮች ላይ የኩራታችን ምንጭ በሆነው የአትሌቲክስ ስፖርት እንደጎረቤታችን ኬንያ ዓለም አቀፍ ውድድሮችን የማስተናገድ የብቃት ደረጃ ላይ ደርሰን ማየት የዘወትር ምኞቴ ነው፡፡ የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌደሬሽንም የውድድሮቹን ጥራት ለማሻሻል በትኩረት እንደሚሰራ ተስፋ አደርጋለሁ።
በመጨረሻም በሀዋሳ በተካሄደው 51ኛዉ የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ሻምፒዮና ከመሮጫ ጫማ ጋር የተያያዙ ደንቦችን በማስከበሩ ረገድ የተፈጠረውን ክፍተት እንደማስተማሪያ ብንጠቀምበት በሚል የሚከተለውን ለማለት ወደድኩ፡-
የመሮጫ ጫማ ደንቦች ለትራክ ውድድር
64 ደቂቃ ከ14 ሰከንድ በሆነ ሰዓት የዘንድሮ የራስ አል ካይማህ የግማሽ ማራቶን ውድድር አሸናፊ የሆነችው ግርማዊት ገብረእግዚአብሔር በሐዋሳ በተከናወነው 51ኛው የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ሻምፒዮና ላይ 31 ደቂቃ ከ21.5 ሰከንድ በመግባት የ10,000ሜ. አሸናፊ ሆናለች፡፡ የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽንም ዓለም አቀፉን ደንብ ከግምት ባላስገባ ሁኔታ ውጤቱን በአዲስ የሻምፒዮንሺፕ ሪኮርድነት ጭምር አፅድቆት አልፏል፡፡ ይሁን እንጂ መጋቢት 20/2014 በተደረገው የሴቶች የፍፃሜ ፉክክር ላይ በኢትዮጵያ ምድር የተመዘገበ የምንግዜውም ፈጣን የሴቶች 10 ሺህ ሜትር ሰዓት የሆነው ውጤት በአለም አትሌቲክስ ዘንድ እውቅና ሊሰጠው የማይችል ነው።
● ለምን?
አትሌቷ የሶል ውፍረቱ 40ሚሜ የሆነ ዙምኤክስ ቬፐርፍላይ (ZoomX Vaporfly) ጫማ አድርጋ በመወዳደሯ ምክንያት።
● ደንቡ ምን ይላል?
በትራክ ውድድሮች ላይ የሚፈቀደው ከፍተኛው የሶል ውፍረት ፡-
– 20ሚሜ ከ 800ሜ በታች ለሆኑ ውድድሮች እና ለሁሉም የሜዳ ላይ ተግባራት (ከስሉስ ዝላይ በስተቀር)
– 25ሚሜ ለ800ሜ እና ከዛ በላይ ለሆኑ ውድድሮች እንዲሁም ለስሉስ ዝላይ
– 40ሚሜ ለትራክ ላይ የእርምጃ ውድድሮች
እነዚህ ደንቦች እ.ኤ.አ. እስከ ኦክቶበር 31, 2024 ድረስ በሥራ ላይ ይውላሉ። ከኖቬምበር 1 ቀን 2024 ጀምሮ ለ800ሜ እና ከዚያ በላይ ለሆኑ ውድድሮች እንዲሁም ለስሉስ ዝላይ የሚፈቀደው ከፍተኛ የሶል ውፍረትም ወደ 20 ሚሜ ዝቅ የሚል ይሆናል።
● የትራክ ላይ መወዳደሪያ ስፓይክ ጫማ ከሌለኝስ?
ደንቡ የጎዳና ላይ የመሮጫ ጫማዎች በትራክ ላይ እንዳይደረጉ አይከለክልም ነገር ግን በ25 ሚሊ ሜትሩ ገደብ ምክንያት 30 ሚሜ ወይም 40 ሚሜ የሆኑ የጎዳና ላይ መሮጫ ጫማዎች በትራክ ውድድሮች ላይ እንዲደረጉ አይፈቅድም፡፡
● ለበለጠ መረጃ :-
https://www.worldathletics.org/news/press-releases/new-athletic-shoe-regulations-approved-2022
Opinions
On the TPLF’s Love Affair With ‘Genocide’

Today, the joint investigation report by the Ethiopian Human Rights Council and the UNHR
on human rights violations committed in Tigray concluded that there is no evidence that genocide has taken place so far. While this is a bit of a setback for the TPLF, which has wanted the world to believe—since the 1990s, even as the TPLF was dominating power in Addis—that a genocide has been perpetrated against the people of Tigray, unfortunately the group still appears to be determined to make genocide a reality. This is confusing for people who don’t understand why the TPLF is obsessed with genocide, why its internet cadres began using #TigrayGenocide in April 2020, months before the war began. So many weapons have been deployed in this war, and among them: confusion and obfuscation.
In the past several months and more so in the past few weeks, we have been getting
testimony after testimony from allied Amhara forces fighting the TPLF that Tigrayan residents of cities in Wollo have been collaborating with the TPLF by a) attacking ENDF and allied forces from behind; b) forcing ENDF and allied forces to withdraw from towns and cities afraid of committing large scale massacres by firing back at the civilians (Tigrayans) firing at them; c) helping the TPLF locate and execute young Amharas believed to be a threat; and d) in at least one horrifying account by an IDP who managed to escape occupied territories, handing TPLF soldiers a list of women to rape. Another shocking development in the past several months has been the widespread use of child soldiers by the TPLF, which, according to experts who have studied the practice, is an “alarm bell” calling attention to possible plans to commit mass atrocities. The use of child soldiers by the TPLF and its attendant implications, along with the widespread deployment of civilian sleeper agents in Amhara cities the TPLF has taken over, serves to create an overall perception of every Tigrayan as a potential enemy, sowing fear and mistrust.
Many Ethiopians are looking at this and wondering: why are Tigrayan elites on the internet
either celebrating the TPLF’s advance via these toxic methods or silent about all this? How can they not see how dangerous this is for everyone, especially for Tigrayans who live outside Tigray? How can they not see that there is no “winning” after stoking all this lasting animosity? Do Tigrayan elites not understand that there can be no justice for Tigray—whether Tigray secedes or not—unless there is justice for her neighbors, for Tigray does not exist in a vacuum? The questions are being asked but nobody is answering them. Our academic class has largely failed to offer viable analyses of the ideas driving this war, as they failed over the past fifty years in regards to coming up with a fitting paradigm for understanding Ethiopia’s unique situation.
Here is my humble attempt to explain what I think is happening with the TPLF’s obsession
with—and with its active attempt to inspire—genocide:
The most successful psychopaths in any field understand that, in order to win anything, one
must risk everything, including the very thing one is supposedly fighting for. In the case of the
TPLF (and associated Tigrayan political elites), whose motto appears to be “give me supremacy or give me death,” that “everything” they are risking is the lives of ordinary Tigrayans in whose names they are fighting. We have seen over the past several months the extent to which the TPLF is willing to go to sacrifice ordinary Tigrayans in order to get what it wants: wave after wave after wave of young poorly armed and inexperienced Tigrayans were unleashed upon ENDF and Amhara and Afar forces in order to force the latter to waste ammunition and energy before the more experienced soldiers are sent.
So, for a political group who sends tens of thousands, if not hundreds of thousands, of
young Tigrayans towards open fire, violence against hundreds of thousands of Tigrayans is nothing if it means the TPLF will in the end win the “prize” it has been obsessed with for decades: genocide. You see, merely attaining power in Addis Ababa is not enough for the TPLF, whose core driving ideology is Tigrayan supremacy. Power is temporary; anybody can take it away from you, and the 2018 uprisings demonstrated that. Genocide is forever. Nobody can take away from you the story of genocide committed against your people.
The TPLF looked at countries like Israel and Rwanda and realized what a potent instrument
genocide is for establishing perpetual minority rule. We have some indications suggesting that the TPLF views Israel as a model. When the war between Ethiopia and the TPLF began in November 2020, Sekoutoure Getachew, a TPLF official, went on TV to tell us that the TPLF’s decision to launch a preemptive attack on the Northern Command was inspired by how the young state of Israel, feeling threatened by her neighbors, launched preemptive attacks against them in the “six-day war” of 1967. Another indication is the manner in which the TPLF, during its 27 years in power, invested heavily in creating a wealthy and strongly networked Tigrayan diaspora which has been used to lobby and influence western governments and organizations much in the same way as the Jewish diaspora aids the state of Israel. The TPLF has figured out that truth does not matter in politics, especially in international politics. If you have the wealth and the personnel to peddle your preferred narrative, if you have the military power to subdue the people you want to subdue, if you are willing to make concessions to external forces (US, Egypt, etc), you can do unspeakable things to others (much like the state of Israel does to Palestinians) and still manage to portray yourself as the victim.
This calculation is so far working for the TPLF, but nothing would seal the deal like the actual
commission of genocide—or something that looks like it—against Tigrayans. As we have seen over the past twelve months, western governments and organizations have shown their willingness to adopt TPLF’s narratives without scrutiny and can easily reward the TPLF with its much pursued prize, genocide, even if actual genocide doesn’t take place.
But why does the TPLF need genocide to establish minority rule? Because, as we saw in their
first tenure in power, you can only rule with an iron fist for a limited period of time. Leaders of the TPLF are adherents of Tigrayan supremacy: the idea that Tigrayans, as the “only” heirs of the Axumite empire, are the natural rulers of the Ethiopian state, and cannot be ruled by “barbarians” south of them. The only acceptable power arrangement for the TPLF is one in which Tigrayans are either directly dominating political power or are the perpetual kingmakers pulling all the major strings. Anything outside that, any system that forces Tigrayans to live on equal footing with everyone else, is unacceptable. And this kind of domination by a minority cannot coexist with a democratic system that the majority of Ethiopians clearly prefer. So, the TPLF needs something more potent than pure political/economic/military power to justify bypassing democracy to establish itself as the permanent ruler/kingmaker of Ethiopia. It needs a new and powerful raison d’être to justify its domination not just to Tigrayans and the rest of Ethiopians but, and most importantly, to the rest of the world. If a genocide were to be committed against Tigrayans (or if the U.S. decides to reward the TPLF with the genocide label even in the absence of it), then the TPLF can license itself to impose all manner of drastic measures aimed at “protecting Tigray and
Tigrayans.” This could be anything from redrawing internal borders (and taking debilitating
measures against the peoples whose lands are being robbed—most likely Amharas and Afaris—so that they will never be in a position to assert themselves) to ethnic cleansing and genocide against populations considered to be a threat. And when you oppose it, the TPLF will say “you committed a genocide against Tigrayans” over and over and over, and its western backers will repeat the same chorus. If they have been this loud over a non-existent genocide over the past twelve months, just imagine what it would be like if the U.S. or UN rewards them with that label.
And this is where the Ethiopian government’s major dilemma comes from: if ENDF and
Amhara forces fight to regain their cities and towns, they risk committing large scale massacres. The TPLF networks reported to be operating within these cities wear civilian clothing and fire at the armies from inside civilian establishments, in an apparent attempt to set up pro-Ethiopia forces. Pro-Ethiopia forces are essentially being dared to commit large scale massacres in order to win back their own cities. So far, they are choosing to withdraw from these towns and cities. But that is another problem: not only is the TPLF committing unspeakable violence against civilians and destroying infrastructure in those cities, the takeovers are emboldening it to continue pressing, giving young people back in Tigray false hope that they are winning and—this is very important—the false idea that they are being “welcomed” by locals in those cities. Then more and more and more young Tigrayans are sent to their deaths.
So the Ethiopian government is stuck between a rock and a hard place. One option is
allowing its forces to do whatever it takes to take back territory, thereby offering protection to its citizens in Wollo and elsewhere, but also risking the “genocide” label by western governments who have been eagerly waiting for such an opportunity so that they can blackmail the government into submitting itself to their wishes on GERD and other issues. Option two is avoiding large scale violence and allowing the TPLF to take power in Addis Ababa and do to Ethiopia what it wishes. One of the things it might do to Ethiopia, according to its leaked strategy document, is force a confederation that will no doubt privilege some states, i.e. Tigray, more than others, and that will no doubt be designed to subdue some populations—mainly Amharas and Afaris—who are considered obstacles to Tigray’s aspirations of domination and expansion (in the TPLF’s original manifesto, Afar is claimed as Tigray land).
And there is absolutely no doubt that the TPLF will make big concessions on the GERD in
order to compensate its western and Egyptian backers, if not redraw borders to make Benishangul Gumuz Tigrayan territory. If you think this is wild, read about the history of the state of Israel, the TPLF’s model state. The redrawing of borders that the TPLF undertook in 1991 was also wild at the time; people don’t think of it as outrageous anymore because the fact that they held onto the territory for 30 years has normalized the event in our minds. And that’s all the TPLF needs: another thirty years to normalize all the outrageous things they will do next.
One may argue that this is a false dichotomy, that there is a third or even maybe fourth option: winning these cities back without mass violence much in the same way the ENDF managed to do during its first campaign in Tigray. We all should pray for such a miracle, of course. However, one can also say that in the early days of the war, the TPLF was mostly withdrawing from Tigrayan cities to avoid urban warfare. And even when they engaged in urban warfare, it was not at the same scale and intensity as has been the case over the past four and half months or so. Starting in mid June, the TPLF’s use of civilians as human shields and fighters stopped being just another weapon in its arsenal and became a center of its operations. The near collapse of the ENDF inside Tigray right before its withdrawal was precipitated by the TPLF’s intensified use of “civilians” to trap the ENDF. Many ENDF soldiers chose to surrender rather than fire at those “civilians.” It is still possible to avoid large scale violence in the attempt to retake towns in Wollo, but the risk for it is very high, and is possibly behind the federal government’s reluctance to take decisive actions.
The point is: barring miracles, the Ethiopian government is positioned to lose something
one way or another. All that is left is choosing its preferred poison. Perhaps one thing to consider for the federal government is: the rights of Amharas and Afaris to defend themselves against the existential threats posed against them by the TPLF is much bigger than the national government’s concerns about its place and relationships with the rest of the world. If the federal government decides to risk the disintegration of Ethiopia, like it has done so far either due to incompetence or severe fear of committing large scale violence, that is fine for the federal government. But when you allow that disintegration to happen, please don’t leave the people of Amhara and Afar in a vulnerable position, unable to defend themselves and their lands. If we must return to the State of Nature, at least give these two peoples, who have so far shed more blood than anyone else in defense of their country, a chance to preserve their lives and their lands. Give them the resources they need to defend themselves before it is too late for them even if you feel it is too late for Ethiopia. Anything less is just a continuation of the gross criminal negligence that the federal government has been guilty of so far.
-
EBS Mogachoch9 years ago
[New] EBS Drama Series – Mogachoch : ሞጋቾች | Episode 7
-
Articles9 years ago
Ethiopia’s renewable energy revolution shouldn’t fail to empower its poor
-
News2 years ago
መንግሥት ከሕወሓት ይልቅ ለአገሪቱ ሥጋት የሆኑ ሌሎች ችግሮች አሉብኝ አለ
-
Opinions2 years ago
On the TPLF’s Love Affair With ‘Genocide’
-
Music4 years ago
2019 ESFNA Atlanta: Ethiopian Day – Ethiopia Hagerachin : ኢትዮጵያ ሀገራችን
-
Music4 years ago
2019 #ESFNA Atlanta: Ethiopian Day | Neway Debebe – Hageren Alresam : ሀገሬን አልረሳም
-
Articles8 years ago
ሰበር ዜና፦ ተዋናይት ሰብለ ተፈራ (ትርፌ) በመኪና አደጋ ህይወቷ አለፈ
-
Bahilawi Zefenoch10 years ago
Bahilawi Zefenoch – ባህላዊ ዘፈኖች
Anonymous
September 4, 2016 at 4:46 am
I think we need to see this positively and approach eachother while we contribute the struggle to dismantle TPLF.
Anonymous
September 3, 2016 at 3:13 am
akatary hula
atakilti
September 2, 2016 at 8:15 pm
Not bad