Connect with us

Articles

በገንዘብ አቅርቦት ጥያቄ ውስጥ የሚዋልለው ኢኮኖሚ

Published

on

55d19fb9c2e729f68455beebbbe6de8b_XL

09 FEBRUARY 2014 ተጻፈ በ 

ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በአገሪቱ ውስጥ አስገራሚ ነገር መታየት ጀምሯል፡፡ በርካቶች በደረቅ ቼክ ምክንያት ወደ እሥር ቤት የሚወርዱት የእውነትም በደረቅ ቼክ አጭበርባሪ ለመሆን ተነሳስተውና ሆነው በመገኘታቸው እንዳልሆነ የዚሁ ጉዳይ ሰለባ የነበሩ ይገልጻሉ፡፡ በየፖሊስ ጣቢያውም እንዲህ ያለው ነገር እየተበራከተ መምጣቱ እየታየ ነው፡፡

በቅርቡ አዲስ አድማስ በደረቅ ቼክ ላይ ያስነበበው ዜና ጥቂት የማይባሉ ነጋዴዎች በደረቅ ቼክ ሰበብ እስር ቤት ከሚገቡባቸው ምክንያቶች አንዱ መሆኑን አመልክቷል፡፡ ገና ለገና ከውጭ ለሚያመጡት ዕቃ ቀብድና ዱቤ ተቀብለው ዕቃው ሲመጣ ሊከፍሉ ተስማምተው ባንክ የነበራቸውን ገንዘብ አውጥተው ዕቃ የሚያስመጡ ናቸው፡፡ በመሆኑም ዕቃቸው መጥቶ ወደ ገንዘብነት እስኪቀየር ድረስ ገንዘብ ከተቀበሉት ሰው ባንክ ያልገባው ገንዘብ እስኪገባ ድረስ ታግሶ በመጠበቅ ሒሳብ መዝገባቸው ውስጥ ከገባ በኋላ እንዲወስድ ማድረግ በአዲስ አበባና በክልል ከተሞች በነጋዴዎች መካከል የተለመደ የዕለት ተግባር ነው፡፡

በዚህ መካከል ግን ገንዘብ ሲያጥር፣ በተባለው ቀን አስገባለሁና እስከዚያ ድረስ ደረቁን ቼክ ይዘህ ጠብቅ የተባለው ነጋዴ ዕምነት እያጣ ወይም እየተጭበረበረ ይመስለውና ባንክ ቤት ሄዶ አቤት ይላል፡፡ ቼክ የተጻፈለት ነጋዴም የተባለው ገንዘብ ባለመኖሩ ምክንያት ቼኩን የጻፈው ሰው ላይ ክስ በመመሥረት የሕግ ጥያቄ ያቀርባል፡፡ ቼክ ሰጪው ለእሥር ይዳረጋል፡፡ እርግጥ የተመሰከረላቸውና የሰው ገንዘብ ይዘው እብስ የሚሉ እንዳሉ ሁሉ፣ በገንዘብ እጦት ሳቢያ፣ ያሰቡት እንዳላሰቡት እየሆነ በጻፉት ቼክ የሚታሰሩ ግን እየተበራከቱ መምጣታቸው እውነት ነው፡፡

ለመሆኑ ኢኮኖሚው ውስጥ ገንዘብ አለ ወይ?

ይህ ጥያቄ የብዙ ነጋዴዎች፣ የሥራ ተቋራጮችና የሌሎችም ዘርፎች የወቅቱ አንገብጋቢ ጥያቄ ሆኗል፡፡ የገንዘብ እጥረት አለ ወይ ለሚለው ጥያቄ ምላሹ ሁለት ሆኖ ይታያል፡፡ አለም የለምም፡፡ አምራቾችና ምሁራን የገንዘብ ዕጥረቱ አለ በሚለው ይስማማሉ፡፡ መንግሥት በበኩሉ የገንዘብ ችግር የለም እያለ ይገኛል፡፡ ባንኮች የገንዘብ እጥረት እንዳለባቸው ይናገራሉ፡፡ አምራቾችም ገንዘብ ለማግኘት መቸገራቸውን ይገልጻሉ፡፡ የገንዘብ አቅርቦት ችግር መኖሩን ኢኮኖሚስቶችም የሚስማሙበት ነጥብ ነው፡፡ ይብሱን የገንዘብ ዕጥረቱን መንግሥት እንደፈጠረው፣ ሊፈጠር የቻለውም ከሚከተላቸው የገንዘብና የፊስካል ፖሊሲዎች አኳያ እንደሆነ፣ በተለይ የዋጋ ንረትን ለመቆጣጠር ሲል የወሰደው እርምጃ ሊሆን እንደሚችል ይተነትናሉ፡፡ ወደ ቀደመው ነገር ስንመለስ የገንዘብ እጥረት ጥያቄ እየተነሳ ነው ብለናልና ከማኑፋክቸሪንግ ዘርፉ እንጀምር፡፡

የአምራቾች የገንዘብ እጦት 

በቅርቡ ለፓርላማ ጥያቄያቸውን ያቀረቡ 36 ኩባንያዎች ገንዘብ የለም ለሚለው መነሻ መንደርደሪያ ሊሆኑ ይችላሉ፡፡ የመከላከያው ብረታ ብረትና ኢንጂነሪንግ ኮርፖሬሽን (ሜቴክ)፣ ማሩ፣ መስፍን ኢንዱስትሪያል ኢንጂነሪንግ፣ አምቼ፣ በላይአብ ሞተርስ፣ ሊፋን የተባሉትን ኩባንያዎች ጨምሮ 36 የአገሪቱ ማኑፋክቸሪንግ ኩባንያዎች፣ በኢንዱስትሪ ሚኒስቴር ሥር በሚገኘው ብረታ ብረት ኢንዱስትሪ ልማት ኢንስቲትዩትና በሜቴክ በኩል፣ ለፓርላማው ኢንዱስትሪ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ካቀረቧቸው መሠረታዊ ጥያቄዎች ውስጥ የገንዘብ እጥረት ይጠቀሳል፡፡

ኩባንያዎቹ ፓርላማው ፊት ያቀረቡት ሰንድ ውስጥ ከቀረቡት በርካታ ጥያቄዎች መካከል፣ ከባንክ አገልግሎት ጋር በተያያዘ በሙሉ አቅማቸው ለመሥራት የሚያስችል የሥራ ማስኬጃ ብድር ወይም ካፒታል ሊያገኙ አለመቻላቸው አንገብጋቢ ሆኖባቸዋል፡፡ በሚፈልጉት መጠንና ጊዜ ውስጥ የሚያስፈልጋቸውን ያህል ብድር ወይም ካፒታል ለሥራ ማስኬጃ አለማግኘታቸውን ጠቁመዋል፡፡

እንደ ኩባንያዎቹ ከሆነ ከአምራች ኢንዱስትሪነታቸው አኳያ በሙሉ አቅማቸው ለመሥራት ከመንግሥትም ይሁን ከግል ባንኮች በቂ የብድርና የውጭ ምንዛሪ አቅርቦት አያገኙም፡፡ የውጭ ምንዛሪ ማግኘት ተስኗቸዋል፡፡ ከውጭ የሚገቡ የጥሬ ዕቃዎችን ለማስገባት የባንክ መተማመኛ ሰነድ (ኤልሲ) በአስቸኳይ ስለማይከፈትላቸው፣ ጥሬ ዕቃዎቹ ወደ አገር ውስጥ የሚገቡት እጅግ ዘግይተው ሆኗል፡፡ ባንኮች ከውጭ ለሚገቡ ልዩ ልዩ ሸቀጦች ብድር የሚሰጡ በመሆኑ ተጠቃሚዎች ከአገር ውስጥ ምርት ይልቅ ከውጭ በሚገባው ላይ እንዲያዘነብሉ የሚያመቻች አካሄድ መፍጠራቸውን፣ ከውጭ የሚገቡ ምርቶችን በአገር ውስጥ ለመተካት የሚሠሩት ሥራ ጫና ውስጥ መግባቱን፣ እነዚህ የአገር ውስጥ አምራቾች ለምርት ሥራቸው ምንም ዓይነት የማበረታቻ ድጋፍ እያገኙ አለመሆኑን በመግለጽ ለፓርላማው ተጠሪ ኮሚቴ አቅርበዋል፡፡

ከዚህ ባሻገር የኢትዮጵያ መንገዶች ባለሥልጣንም የበጀት እጥረት ውስጥ እንደሆነና ለመንገድ ሥራዎች የሚመደብለት ገንዘብ በቂ እንዳልሆነ ለፓርማላው አሳውቋል፡፡ ከዚህ ቀደም ተጨማሪ በጀት እየተባለ ይለቀቅለት የነበረው ገንዘብም ቀርቷል፡፡ የኢትዮጵያ መንገዶች ባለሥልጣን ዋና ዳይሬክተር አቶ ዛይድ ወልደ ገብርኤል ፓርላማ ቀርበው እንዳስረዱት፣ በተለይ ጥገና በሚያስፈልጋቸው የአገሪቱ መንገዶች ላይ የበጀት እጥረት አሳሳቢ እየሆነ ይገኛል፡፡ ከ200 ያላነሱ የመንገድ ፕሮጅክቶችን እያስኬደ የሚገኘው የኢትዮጵያ መንገዶች ባለሥልጣን፣ በአሁኑ ወቅት ለተቋራጮች ያልከፈለው ከሁለት ቢሊዮን ብር በላይ ዕዳ እንደላበት አስታውቋል፡፡ በበጀት እጥረት ምክንያት ይህንን ዕዳ መክፈል እንዳልቻለም ይፋ አድርጓል፡፡

የባንኮች የገንዘብ ጥያቄ

በአገሪቱ የሚንቀሳቀሱ የግል ባንኮች እየበዙ መምጣት፣ የመንግሥት ባንኮች የመስፋፋት ሒደት የባንክ ኢንዱትስሪውን ፉክክር እያበረታው መምጣቱ ይነገራል፡፡ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ብቻውን ከ750 በላይ ቅርንጫፎች በአገሪቱ መክፈቱ፣ በየከተማው ውስጥ ማስፋፋቱ፣ በአዲስ አበባ በየውስጣ ውስጡ ሳይቀር መንሰራፋቱ በግል ባንኮች ዘንድ ሥጋት ሆኗል፡፡

የንግድ ባንክ ቅርንጫፎች መስፋፋት የግል ባንኮች ከዚህ ቀደም በቀላሉ ያገኙት የነበረውን ደንበኛ፣ በአሁኑ ጊዜ በአቅራቢያው ወደሚያገኘው ንግድ ባንክ ቅርንጫፍ ጎራ በማለት ገንዘብ ማስቀመጥን ስለሚመርጥ ሽሚያው የግል ባንኮችን አሳስቧቸዋል፡፡ በዚያም ላይ ንግድ ባንክ ለ40/60፣ ለ20/80 እና ለ10/90 የቤቶች ልማት የሚሰበስበው ገንዘብም እንዲሁ ሌሎቹ ባንኮች ከዚህ ቀደም ያገኙት የነበረውን ዓይነት ተቀማጭ እንዳያገኙ እየተሻማ መጥቷል ተብሎለታል፡፡ በዚያም ላይ እንደግል ባንኮች ንግድ ባንክ የ27 ከመቶ የቦንድ ግዥ የመግዛት ግዴታ ስላልተጣለበት ጭምር የውድድሩ ሜዳ ሰፍቶ እንደተለቀቀለት በመግለጽ የግል ባንኮች ይተቹታል፡፡

ዋናው ፈተና ግን በያመቱ ለመንግሥት የልማት ሥራዎች ከሚያበድሯት እያንዳንዷ ብድር ብሔራዊ ባንክ የ27 ከመቶ ተቆራጭ በማድረግ ቦንድ እንዲገዙ ማስገደዱ በብድር አሰጣጥ ላይ የተወሰነ ጫና መፍጠሩን ሲገልጹ ቆይተዋል፡፡ አሁንም ጫናው መቀጠሉን የሚገልጹ የግል ባንክ ኃላፊዎች አሉ፡፡

‹‹ራስ ምታት ውስጥ ባይከተንም እንደቀድሞው ጥሩ እንቅስቃሴ የለም፡፡ የገንዘብ እጥረት አለ፤›› የሚሉት የባንክ ኃላፊዎች፣ ምንም እንኳ የ27 ከመቶ የቦንድ ግዥ አምናም ሲሠራበት የቆየ ቢሆንም፣ አዲስ ገንዘብ ወደ ባንኩ እስካልመጣ ድረስ፣ አምና ከሰጠው ብድር ላይ 27 ከመቶ ተቆርጦ የተሰጠበት ያው ብድር ዘንድሮ ተመላሽ ተደርጐ ለተበዳሪ ሲሰጥም፣ እንደገና ከዚያው ላይ 27 ከመቶ ይቆረጥለታል ማለት ነው፡፡ በምሳሌ ለማሳየት መቶ ብር ያበደረ ባንክ፣ ከዚህ ገንዘብ ላይ 27 ከመቶ አንስቶ ለብሔራዊ ባንክ ገቢ ያደርግና ቀሪውን ያበድራል፡፡ ይህ ሌላ ተቀማጭ አላገኘም ብለን ብናስብ፣ ከሚመለስለት ይኼው ብድር ላይ መቶ ብር ሲያበድር 27 ብር አንስቶለት አበድሮ ነበር፡፡ የሚመለስለት ብድር 73 ብር ይሆናል፡፡ ይኼንን ገንዘብ  እንደገና ለማደበር ሲፈልግም 27 ብር አሁንም ቆርጦ ማንሳት አለበት፡፡ ልብ መባል ያለበት ምሳሌው ብሔራዊ ባንክ የሚጠይቃቸው ሌሎች መሥፈርቶችን ሳይጨምር የቀረበ መሆኑ ነው፡፡ የተቀማጭ መጠባበቂያ መያዝ የመሳሰሉት ብድር ከመሰጠቱ በፊት የሚሟሉ ቅድመ ሁኔታዎች ናቸው፡፡ ከእያንዳንዱ ብድር ላይ ተቆርጠው አስቀማጩ ገንዘቡን በጠየቀ ጊዜ እንዲሰጠው ለማስቻል የሚያገለግሉ ናቸው፡፡ በእነዚህ ምክንያቶች ባንኮች አዳዲስ ተቀማጭ እስካላገኙ ድረስ፣ ያላቸውን ገንዘብ እያገላበጡ በሚያበደሩበት ወቅት ጫና ውስጥ የሚገቡት በዚህ የተነሳ ነው፡፡

ይህ ሥዕል የሚያሳየውና ባንኮችም እንደሚያብራሩት የገንዘብ እጥረት እንዳለባቸው ነው፡፡ ተበዳሪዎች በተለይ ተቋራጮችም ገንዘብ ማግኘት እንዳልቻሉ እየገለጹ ነው፡፡ የባንክ ብድር ማግኘት አልቻልንም እያሉ ነው፡፡ የአንድ ሚሊዮን ብር ብድር ለማግኘት አልቻልንም የሚሉ ቅሬታዎች እየተሰሙ ነው፡፡

የኢኮኖሚ ምሁራን ምን ይላሉ

በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ መምህር የሆኑትና የኢኮኖሚክስ ምሁሩ ዶክተር ቆስጠንጢኖስ በርኸ፣ የገንዘብ እጥረት አጋጥሟል በሚለው የግል ባንኮችም ሆነ የነጋዴዎች አስተያየት ላይ ይስማማሉ፡፡ ባንኮች በሚያበድሩ ጊዜ ከየብድሩ የሚቆረጠው 27 ከመቶ ወደ መንግሥት ፕሮጀክቶች የሚሔድ በመሆኑ ብድሩን እንደሚያጣብበው ያብራራሉ፡፡ መንግሥት ዋጋ ግሽበትን ለመቆጣጠር በገንዘብ ፖሊሲው የሚተገብረው ትልቁ ሥራ የገንዘብ አቅርቦቱን በመቆጣጠር እንደሆነ የገለጹት ዶክተር ቆስጠንጢኖስ፣ የአገሪቱ ባንኮች ‹‹በአብዛኛው ብድር ሲሰጡ የቆዩት ለቢሮ ኪራይ ለሚውሉ ሕንፃዎች መሥሪያ ወዘተ ነበር፡፡ አሁን ግን ለልማት አስተዋጽኦ ባላቸው ሥራዎች ላይ ገንዘቡ እንዲውል በመደረጉ የገንዘብ እጥረት መኖሩ የሚታመን ነገር ነው፡፡ የገንዘብ አቅርቦት ትልቅ እጥረት አለበት፤›› ብለዋል፡፡

የግል ባንኮች የ27 ከመቶ ቦንድ ግዥ ሲፈጽሙ ኖረዋል፡፡ ለገንዘብ እጥረቱ መኖር ይህ የቦንድ ግዥ አሁን ዛሬ ላይ እንዴት ምክንያት ሊሆን ይችላል ለሚለው ጥያቄ፣ ዶክተሩ የድምር ውጤት ተፅዕኖ ነው በሚል ምላሻቸውን መስጠት ይጀምራሉ፡፡ ከሁለት ዓመት በፊት የግል ባንኮች ምንም ዓይነት ብድር እንዳይሰጡ ተከልክለው እንደነበር ያስታወሱት ዶክተር ቆስጠንጢኖስ፣ አሁን እየተተገበረ ያለው የ27 ከመቶ ቦንድ ግዥ፣ የንግድ ባንክ መስፋፋትና የቤቶች ቁጠባ ፕሮግራም መምጣት፣ ሕዝቡ በሌሎች የግል ባንኮች ያስቀመጠውን ገንዘብ ወደ ንግድ ባንክ መውሰዱ የግል ባንኮች ላይ የገንዘብ እጥረት እንዲከሰት ሊያደርግ እንደሚችል ይስማማሉ፡፡

‹‹ኮንዶሚንየም ለመሥራት ወደ መንግሥት ኪስ የሚገቡ ገንዘቦች ናቸው፤›› ሲሉ የገለጹት ይህ የቤቶች ፕሮግራም፣ መንግሥት እንደሚለው ለልማት እስካዋለው ድረስ ገንዘቡ በገበያው ውስጥ የሚዘዋወር ነው፡፡ በእሳቸው ትንታኔ ገንዘቡ ከመንግሥት ወጣ ወይም ከግል ባንክ መውጣቱ አይደለም የሚያጨቃጭቀው ነጥብ፡፡ ዋናው ነገር መንግሥት ከፍተኛ ገንዘብ እየሰበሰበ መሆኑ መታወቁ ነው፡፡

መንግሥት ገንዘብ የሚሰበስበው ለልማት ሥራዎች ነው ከተባለ፣ እንደ ህዳሴው ግድብ ያለውን ለመገንባት የሚያወጣውን ወጪ የፊስካል ፖሊሲውን የሚመለከቱ ሲሆን፣ በገንዘብ ወይም ሞኒታሪ ፖሊሲው በኩል ሊታይ የሚችለው የ27 ከመቶ ቦንድ እየገዛችሁ ገንዘብ አምጡ ማለቱ ገንዘብ ከገበያው ውስጥ ለመሰብሰብ የሚሄድበትን የፖሊሲ መንገድ ያሳያል፡፡ በመሆኑም ‹‹መገመት የሚገባን ነገር የገንዘብ አቅርቦትን በመቆጣጠር የዋጋ ግሽበትን ለመቀነስ እየተሞከረ እንደሆነ ነው፤›› የሚሉት ዶክተሩ፣ ይህ የሚሆን ከሆነ አምራቾችና ሻጮች ዋጋቸውን እንዲቀንሱ የሚያስገድዳቸው መሆኑን ይገልጻሉ፡፡ ለምን ይሆናል ቢባል አቅርቦትና ፍላጎት አልተጣጣሙምና ነው፡፡ እንዲህ የሚያብራሩት ዶክተሩ፣ ሰው ገንዘብ ከሌለው ሊገዛ ስለማይችል ፍላጎት ይቀንሳል፡፡ የሚገዛው ከሌለ ነጋዴው ዋጋ ለመቀነስ ይገደዳል፡፡ በእጁ ያለውን ሸቀጥ ለማጣራት ዋጋ በግድ ቀንሶ መሸጥ ግድ እንደሚሆንበት ይተነትናሉ፡፡ ትልልቆቹ የብረታ ብረት አምራቾችን ጨምሮ የእህል ነጋዴዎች ሳይቀር ገበያ አጣን ማለታቸው በጋዜጣ መውጣቱን ዶክተሩ በዋቢነት ይጠቅሳሉ፡፡ ስለዚህ የገንዘብ አቅርቦት እጅጉን እየቀነሰ በመጣ ጊዜ ሰው እጅ የሚገባው ገንዘብ ስለሚቀንስ የገበያው ዋጋም ሊቀንስ እንደሚችል ተብራርቷል፡፡

በመሆኑም በአሁኑ ጊዜ ከአሥር በመቶ በታች ሆኗል የሚባልለት የዋጋ ግሽበት እየቀነሰ ያለው ዋጋ ስለቀነሰ ሳይሆን ሰው የመግዛት አቅም ስለሌው ፍላጎቱን እየገታ ስለመጣ ነው፤ ምሁሩ የሚደርሱበት ድምዳሜ ነው፡፡ ‹‹ለምሳሌ ድሮ 100 ዳቦ የሚገዛው፣ አሁን 50 ዳቦ ብቻ ለመግዛት ስለሚገደድ፣ ዳቦ ሻጩም እንደ ድሮው የሚገዛው ስለሌለ ዋጋውን ይቀንሳል ማለት ነው፡፡››

መንግሥት ግን ገንዘብ አለኝ ይላል

የገንዘብና ኢኮኖሚ ልማት ሚኒስቴር በአገሪቱ ውስጥ የገንዘብ እጥረት አለመኖሩንና ለበጀት ዓመቱ ከሚያስፈልገው ገቢ ውስጥ በስድስት ወራት ብቻ 63 ቢሊዮን ብር ከታክስ መሰብሰቡን አስታውቋል፡፡

የኢትዮጵያ ልማት ባንክ ፕሬዚዳንት አቶ ኢሳይያስ ባሕረ እንደሚገልጹት፣ ልማት ባንክ  የገንዘብ እጥረት የለበትም፡፡ የሥራ ማስኬጃ ካፒታል እጥረት ለገጠማቸውም ባንኩ በየጊዜው እየሰጠ እደሚገኝም አስታውቀዋል፡፡ ‹‹በኢትዮጵያ ልማት ባንክ በኩል የተንፀባረቀ ነገር የለም (የገንዘብ እጥረት)፡፡ ገንዘብ እየቀረበ ነው፤›› በማለት ለሪፖርተር የገለጹት አቶ ኢሳይያስ፣ የግል ባንኮች ተቀማጭ የማንቀሳቀስ አቅማቸው እያነሰ መጥቶ ከሆነ ማየቱ ተገቢ እንደሚሆንም አስታውቀዋል፡፡ የግል ባንኮች ተቀማጭ መሰብሰብ ካልቻሉ ችግር ሊያጋጥማቸው ስለሚችል በዚህ ላይ ትልቅ ሥራ መሥራት እንደሚጠበቅባቸውም ይመክራሉ፡፡ ከዚህ ባሻገር ኢኮኖሚው ውስጥ የሚንቀሳቀሰው ገንዘብ ወደ ባንክ መምጣት እንዳለበትም ያሳስባሉ፡፡

በዚህ ላይ ሥጋታቸውን የገለጹት ፕሮፌሰር ቆስጠንጢኖስ ጥናት የሚፈልግና በማስረጃ ያልተደገፈም ቢሆንም፣ አብዛኛው ነጋዴ ወደ ባንክ ሥርዓት ገብቶ መነገድ እንደማይፈልግ እየተነገረ መሆኑን ጠቁመዋል፡፡ ‹‹በጥሬ ገንዘብ የሚንቀሳቀስ ኢኮኖሚ እየሆነ መምጣቱ ይነገራል፤›› ያሉት ፕሮፌሰሩ፣ ይሄ አካሄድ ባንኮች ተቀማጭ የማከማቸት አቅማቸው ላይ ጫና እንደሚያሳርፍ ለማሳየት የተጠቀሙበት ነው፡፡

ሆኖም ባንኮች በያመቱ 40 እና 50 ከመቶ የትርፍ ድርሻ ክፍፍል ከመስጠት ይልቅ ካፒታላቸውን እያሳደጉ፣ ቅርንጫፍ እያስፋፉ ተወዳዳሪ መሆን እንደሚገባቸው ይመክራሉ፡፡ ‹‹አንድ ሰው ኢንቨስት ባደረገው ገንዘብ ሁለት ሦስት እጥፍ መመለስ ከቻለ ይኼ እንደ ኢንቨስትመንት ሳይሆን እንደ ፒራሚድ ስኪም የሚቆጠር ስለሆነ ባንኮቹ ራሳቸውን መገምገም ያስፈልጋቸዋል የሚል ግምት አለኝ፡፡››

የገንዘብና ኢኮኖሚ ልማት ሚኒስቴር የኮርፖሬት ኮሙዩኒኬሽን ዳይሬክተር አቶ ሐጂ ኢብሳም የገንዘብ እጥረት አለ በሚለው ሐሳብ አይስማሙም፡፡ የገንዘብ እጥረት አለ ወይ የሚለውን ጥያቄ በጥያቄ መልሰው ሲገልጹ፣ ‹‹ገንዘብ በቃኝ የሚል ስለሌለ መጀመሪያውኑ በጀትን አብቃቅቶ መጠቀም መቻል፣ በአግባቡ ማቀድ ይገባል እንጂ በየጊዜው ገንዘብ ጨምሩ ቀንሱ መባል የለበትም፤›› ብለዋል፡፡

ሚኒስቴሩ በአሁኑ ወቅት በፊት ይከተል የነበረውን የበጀት ሥርዓት፣ መቀየሩንና ፕሮግራም በጀት በሚባለው ስልት መሠረት እየሠራ በመሆኑ አንድ ጊዜ ታቅደው ለመጡ ሥራዎች ካልሆነ በቀር እንደቀድሞው ተጨማሪ በጀት መፍቀድ ማቆሙን አስታውቀዋል፡፡ መንግሥት ለዚህ ዓመት ካቀደው 150 ቢሊዮን ብር በላይ ተጨማሪ ሌላ በጀት የማይሰጠው፣ የዋጋ ግሽበቱን ባለበት ለማቆየት በመሆኑ ነው ብለዋል፡፡ ተጨማሪ ገንዘብ መልቀቅ ወይም እንደ ድሮው የሚጠየቀውን ያህል ገንዘብ አትሞ ጨምሮ በመስጠት መሥሪያ ቤቶች እንዳስፈለጋቸው እያዟዟሩ የሚጠቀሙበትን አሠራር አስቀርቷል፡፡ የፌደራልም ሆነ የክልል ኃላፊዎች ለሚያቀርቡት ዝርዝር የሥራ ዕቅድ ብቻ የሚውል ገንዘብ ይሰጣቸዋል፡፡ በዚያም ላይ ያቀዱትን ሥራ እውነትም ስለመሥራታቸው ሪፖርት እንዲያቀርቡ ይገደዳሉ፤ ቁጥጥርና ክትትልም ይደረግባቸዋል፡፡ የፕሮግራም በጀት በሰባት መሥርያ ቤቶች ላይ እየተሞከረ ይገኛል፡፡ ሙሉ ለሙሉ በአገሪቱ ለመተግበር ገና ይቀረዋል፡፡

በዚህ አኳኋን የፊስካል ፖሊሲውን ዲስፕሊን ይፋ ያደረገው ገንዘብና ኢኮኖሚ ልማት ሚኒስቴር፣ ይህንን ማድረጉ ከገንዘብ ፖሊሲው ጋር ተጣጥሞ እንዲሄድለት መሆኑን ይፋ አድርጓል፡፡ በመሆኑም መንግሥት ለዚህ ዓመት ካቀደው ገንዘብ ውጭ ተጨማሪ ገንዘብ ላለመልቀቅ የወሰነበት ምክንያት የዋጋ ግሽበት ነው ማለቱ በተዘዋዋሪ፣ እንደ መንገድ ያሉ ትልልቅ ፕሮጀክቶች የሚጠይቁትን ተጨማሪ በጀት እንዳያገኙ ማድረጉ ይታያል፡፡

የገንዘብ ፍሰት ችግር አላጋጠመኝም ያለው ገንዘብ ሚኒስቴር፣ ተጨማሪ በጀት የማልፈቅደው፣ መጀመሪያ በአግባቡ ካለማቀድ በሚመነጭ ችግር ነው ከማለቱ ባሻገር የዋጋ ግሽበትን የሚያባብስ ሆኖ አግኝቼዋለሁ በማለቱም ጭምር ነው፡፡ ዕቅድ እየከለሱ ገና ሲታቀድ የተረሱ ሥራዎች፣ በመንገድ ሥራ ላይ ደግሞ ጨረታ መጀመሪያ ሲወጣና በኋላ ላይ ሲታይ ወጪውን ሊጨምሩ የሚችሉ ነገሮች ሊከሰቱ ስለሚችሉ ተብሎ የተጨማሪ በጀት ጥያቄ ቢቀርብም መንግሥት የማያስተናግደው ጥያቄ ሆኗል፡፡ ለምን ቢባል ዋጋ ግሽበትን መነሻ ስለሚያደርግ ነው ተብሏል፡፡ ስለዚህ ‹‹ከጥር ጀምሮ እስከ ሰኔ ወር መጨረሻ ድረስ መሥሪያ ቤቶች የሚያስፈልጋቸውን ትክክለኛ በጀት፣ በአግባቡ ማቅረብ ካልሆነ በቀር፣ በመካከሉ አንድ ነገር ሲገጥማቸው ብር እንዲታተም መጠየቅ፣ ዋጋ ግሽበትን የሚያመጣ ነው፤›› በማለት አቶ ሐጂ አብራርተዋል፡፡

ይህ ከሆነ መንግሥት የዋጋ ግሽበቱን የሚቆጣጠርበትን የገንዘብ ፖሊሲ ከፊስካል ፖሊሲው ጋር ለማጣጣም ሲል ከፍተኛ ወጪ የሚጠይቁ የግንባታ ሥራዎች ላይ የበጀት ማዕቀብ እያደረገ ነው ማለት ነው፡፡ ዕርምጃው ይህ መሆኑ፣ እንኳንና የንግድና የአገልግሎት ዘርፎቹ ቀርተው፣ የመንግሥት ትልልቅ ፕሮጀክቶች ሳይቀር ገንዘብ ማጣታቸውን መግለጻቸው፣ በስተመጨረሻ ላይ የኢኮኖሚውን ግለት ወይም የዕድገት ሒደት ሊገታ እንደሚችል የሚጠበቅ መሆኑን ምሁራኑ ይስማሙበታል፡፡

ከዚህ ባሻገር ሁለቱን የሞኒታሪና የገንዘብ ፖሊሲዎች ለማጣጣም የሚያስገድዱ የብድር ዕዳና የበጀት ጉድለት መባበስ እንደሆነም ጸሐፍት ይዘክራሉ፡፡ ሆኖም የግል የገንዘብ ድርጅት ይፋ ባደረገው ሪፖርት መንግሥት በብድር ዕዳ ችግር ውስጥ እንደማይገኝ ይገልጻሉ፡፡ ይህ ማለት ግን ዕዳ ለመቀነስ በያመቱ የሚከፈል ገንዘብ የለም ማለት እንዳልሆነ ያስታውቃሉ፡፡

ምንጭ፦ ሪፖርተር

Continue Reading
Click to comment

Leave a Reply

Your email address will not be published.

Articles

በኦስሎ ዳይመንድ ሊግ የ5000ሜ ፉክክር ኢትዮጵያውያን አትሌቶች በሁለቱም ፆታዎች በአሸናፊነት አጠናቀዋል

Published

on

Dawit-Seyaum-1
ትላንት ምሽት በኖርዌይ ኦስሎ በተከናወነው የዳይመንድ ሊግ 5000 ሜ. ውድድር ኢትዮጵያውያን አትሌቶች በወንዶችም በሴቶችም ከአንደኛ እስከ ሶስተኛ ያሉትን ደረጃዎች በመቆጣጠር አሸንፈዋል፡፡ 

በዝናባማ የአየር ሁኔታ ውስጥ በተካሄደው የሴቶች 5000 ሜትር ፉክክር ዳዊት ስዩም በመጨረሻዎቹ መቶ ሜትሮች ውስጥ ፍጥነቷን በመጨመር ጉዳፍ እና ለተሰንበትን ቀድማ አንደኛ ወጥታለች፡፡ የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ለኦሪገን 2022 የአለም ሻምፒዮና ከመረጣቸው ዕጩ አትሌቶች ዝርዝር ውስጥ ያልተካተተችው ዳዊት በኦስሎ ያሸነፈችበት 14፡25.84 የሆነ ሰአት የራሷ ምርጥ ሲሆን እጅጋየሁ ታዬ (14.12.98) እና ለተሰንበት (14፡24.59) ባለፈው ወር በዩጂን ካስመዘገቧቸው በመቀጠልም የዘንድሮ የአለም ሶስተኛው ፈጣን ነው፡፡ በውድድሩ ላይ ከነበሩት ሌሎች ኢትዮጵያውያን መካከል በዘንድሮው የውድድር ዓመት በርቀቱ የመጀመሪያ ተሳትፎዋን ያደረገችው አልማዝ አያና በ14:32.17 ስድስተኛ ሆና አጠናቃለች፡፡ ሀዊ ፈይሳ በ14:33.66፣ ፅጌ ገብረሰላማ በ14:43.90፣ እና አበራሽ ምንሴዎ በ14:47.98 በቅደም ተከተል ሰባተኛ፣ አስረኛ እና አስራ አንደኛ ሆነው ሲያጠናቅቁ ሶስቱም ያስመዘገቡት ሰዓት የራሳቸውን ምርጥ ያሻሻሉበት ሆኗል፡፡ ጥሩነሽ ዲባባ እ.ኤ.አ. በጁን 2008 ዓ.ም. ያስመዘገበችውና 14:11.15 የሆነው የኦስሎ ዳይመንድ ሊግ የሴቶች 5000 ሜትር የውድድር ስፍራ ሪከርድ ይሰበራል ተብሎ ተጠብቆ የነበረ ቢሆንም ሳይሳካ ቀርቷል፡፡  
ዳዊት ስዩም ውድድሩን በድል ካጠናቀቀች በኋላ ለውድድሩ አዘጋጆች በሰጠችው አስተያየት ‹‹ዛሬ ለእኔ ደስታን ስላመጣልኝ በውድድሩ ሰዓት የነበረውን ዝናብ ወድጄዋለሁ ማለት እችላለሁ፡፡ ጠንካራ ተፎካካሪዎች የነበሩበት ከባድ ውድድር ነበር እናም ሁሉንም ለማሸነፍ በቅቻለሁ። በርቀቱ የራሴን ምርጥ ሰዓት ማሻሻል መቻሌም አስፈላጊ ነበር፡፡ በስታድየሙ ውስጥ በከፍተኛ ስሜት ድጋፍ ይሰጡን የነበሩ ወገኖቻችን ነበሩ። ለሰጡን ድጋፍ እናመሰግናለን።›› ብላለች፡፡
 
በኦስሎ የወንዶች 5000 ሜትር የመጨረሻ ፉክክሩ በኢትዮጵያውያኑ ጥላሁን ሀይሌ እና ሳሙኤል ተፈራ መካከል የነበረ ሲሆን ጥላሁን የ1500 ሜትር ስፔሻሊስቱ ሳሙኤልን በአጨራረስ ፍጥነት ቀድሞ በ13:03.51 በአንደኛነት አጠናቋል፡፡ ሳሙኤል ተፈራ የራሱ ምርጥ በሆነ 13:04.35 ሁለተኛ ሲወጣ ጌትነት ዋለ የግሉ የዓመቱ ምርጥ በሆነ 13:04.48 ሶስተኛ ደረጃን ይዞ ጨርሷል። በውድድሩ ላይ የነበሩት ሌሎች ኢትዮጵያውያን ሚልኬሳ መንገሻ በ13:05.94 አምስተኛ እንዲሁም አሊ አብዱልመናን የራሱ ምርጥ በሆነ 13:16.97 አስረኛ ወጥተዋል፡፡
ጥላሁን ሀይሌ ውድድሩን በአሸናፊነት ካጠናቀቀ በኋላ ለውድድሩ አዘጋጆች በሰጠው አስተያየት ‹‹ሶስት ኢትዮጵያውያን የመጀመሪያዎቹን ሶስት ደረጃዎች ይዘን መጨረስ መቻላችን ጥሩ አፈጻጸም ነበር። እየጠነከርኩ እንደሆነ የተሰማኝ ሲሆን በውድድሩ እና ባስመዘገብኩት ሰዓትም ተደስቻለሁ። ለረጅም ጊዜ ጉዳት ላይ ስለነበኩ ወደ አሸናፊነቱ መመለስ መቻሌ በጣም ጥሩ ነው።›› ብሏል፡፡

በኦስሎ የሴቶች 800ሜ. ውድድር ላይ ተፎካካሪ የነበረችው ኢትዮጵያዊቷ ድሪቤ ወልቴጂ በ1፡58.69 አምስተኛ ሆና አጠናቃለች።
Continue Reading

Articles

የዘንድሮው የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ብሄራዊ ሻምፒዮና በእኔ እይታ

Published

on

IMG_0110
ከመጋቢት19-24/2014 ዓ.ም በሐዋሳ አለም አቀፍ ስቴድዮም የተደረገው 51ኛዉ የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ሻምፒዮና ከሞላ ጎደል ስኬታማ በሚባል ሁኔታ ተጠናቋል፡፡ ከአምስት አመት በኋላ በድጋሚ በአካል በመገኘት ስለተከታተልኩት የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ሀገር አቀፍ ሻምፒዮና የግል ምልከታዬን እንደሚከተለው አጠናቅሬዋለሁ፡፡

የበለጠ ትኩረትን በሳቡት ውድድሮች ዙሪያ የተመዘገቡ ውጤቶችን በወፍ በረር በመዳሰስ ስጀምር ከፍተኛ ፉክክር በታየበት የመጨረሻ ቀን የወንዶች 5000ሜ. የአለም ከ20 አመት በታች ሻምፒዮና የ3000ሜ የብር ሜዳልያ አሸናፊው አሊ አብዱልመና 13፡45.0 በሆነ ሰዓት ከጥላሁን ሀይሌ፣ ጌትነት ዋለ እና ዮሚፍ ቀጄልቻ ቀድሞ አሸናፊ ሆኗል፡፡ የፉክክሩ አካል የነበረው እና የርቀቱ የወቅቱ የአለም ሻምፒዮን ሙክታር እድሪስ ስድስተኛ ወጥቷል። 

ከ20 ዓመት በታች የ3000ሜ የአለም ሻምፒዮኑ ታደሰ ወርቁ በ28፡12.0 የወንዶች 10,000ሜ. ሻምፒዮን ሲሆን በ1996 ዓ.ም. በአትሌት ስለሺ ስህን ተመዝግቦ የነበረውን 28፡16.23 የሆነ የሻምፒዮናው ሪኮርድ ለማሻሻልም በቅቷል፡፡ በ10 ሺህ ሜትር የሴቶች ፉክክር ግርማዊት ገብረእግዚአብሔር በቀዳሚነት የጨረሰችበት 31፡21.5 የሆነ ሰዓት አዲስ የሻምፒዮንሺፕ ሪኮርድ ሆኖ ተመዝግቧል፡፡ በርቀቱ የከዚህ ቀደሙ ሪኮርድ  ለተሰንበት ግደይ ከሶስት ዓመት በፊት ያስመዘገበችው 32፡10.13 የሆነ ሰዓት ነበር፡፡

ሳሙኤል ፍሬው በዘንድሮ የወንዶች 3000ሜ. መሰናክል አፈፃፀም ከአለም ሁለተኛው ፈጣን በሆነ 8፡22.5 ሰዓት አሸናፊ ሲሆን ጌትነት ዋለ ከአራት ዓመት በፊት አስመዝግቦት የነበረውን 8፡28.98 የነበረ የሻምፒዮናው ሪኮርድም አሻሽሏል፡፡ በሴቶች 3000ሜ. መሰናክል ከ800ሜ ወደ ረጅም ርቀት የተሸጋገረችው ወርቅውሃ ጌታቸው በ9፡41.8 ሰዓት መቅደስ አበበን (9:43.8) በማስከትል በአሸናፊነት አጠናቃለች። 

አድሃና ካህሳይ (3:51.0) የወንዶች 1500ሜ ፉክክሩን በበላይት ሲያጠናቅቅ በሴቶች 1500 ሜ አያል ዳኛቸው (4:10.0) ተጠባቂዋ ዳዊት ስዩምን (4:11.1) በመቅደም በአንደኛነት አጠናቃለች። በ800ሜ. ወንዶች ቶሌሳ ቦደና (1:47.1) በሴቶች ወርቅነሽ መሰለ (2:02.1) አሸናፊ ሆነዋል።
ዮብሰን ብሩ በ400ሜ/400ሜ መሰናክል (45.9/50.5) ድርብ ድል ሲቀዳጅ፣ በወንዶች ጦር ውርወራ ኡታጌ ኡባንግ ብሔራዊ ሪኮርድ በሆነ 73.28ሜ. አሸንፏል፡፡ የኋልዬ በለጠው እና ዮሃንስ አልጋው በእርምጃ ሩጫ የሻምፒዮንነት ክብርን ተቀዳጅተዋል።

ጥቂት አስተያየቶች፡-
የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ስፖርት አፍቃሪ እንደሆነ እና ለዕድገቱ እንደሚቆረቆር ሰው በብሔራዊ ሻምፒዮናው ላይ ስለተመለከትኳቸው አዎንታዊ እና አሉታዊ ጎኖች ጥቂት አስተያየቶቼን እንደሚከተለው አስቀምጣለሁ፡-

አዎንታዊ ጎኖች
• ባለው ነባራዊ ሁኔታ ውስጥ ሊገጥሙ የሚችሉትን ተግዳሮቶች በሙሉ በመቋቋም ፌዴሬሽኑ ውድድሩን ከአዲስ አበባ ውጭ አካሂዶ በሰላም ማጠናቀቅ መቻሉ አንደኛው ስኬቱ ነው፡፡

• በሻምፒዮናው ላይ ጥቂት የማይባሉ ታዋቂ አትሌቶች በሀገሪቱ ትልቁ የአትሌቲክስ ፉክክር ላይ ተሳታፊ ሆነው ሲወዳደሩ መመልከት የተቻለ ሲሆን በተለይም በወንዶች 5000 ሜትር ፍፃሜ ላይ የታየው የኮከብ አትሌቶች ፉክክር ልዩ ነበር፡፡

• በውድድሩ ወቅት ለአትሌቲክስ ዳኞች የብቃት ማሻሻያ ስልጠና መሰጠቱም የውድድሩን ጥራት ለማሳደግ የሚረዳ እንደመሆኑ እሰየው የሚባል ነው፡፡
 
• እንደ ኢትዮ ኤሌክትሪክ ያሉት ክለቦች ለአትሌቲክስ ስፖርት የበለጠ ትኩረት በመስጠትና ተጠናክሮ በመቅረብ ከዚህ ቀደም በጠንካራነታቸው ከሚታወቁት መከላከያ እና ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ጋር የቅርብ ተፎካካሪ ሆነው መታየት፤ የኦሮሚያ ክልል፣ ደቡብ ፖሊስ እና ሲዳማ ቡና ክለብ አትሌቶችም ጠንካራ ተሳትፎ ሳይዘነጋ የሻምፒዮናው ፉክክር ድምቀት ነበሩ፡፡  
• የአንዳንዶቹ ተገቢነት አጠያያቂ ቢሆንም ብዛት ያላቸው የሻምፒዮናው ሪኮርዶች የተሻሻሉበት ውድድርም ነበር፡፡ 

አሉታዊ ጎኖች
• የሀገሪቱ ትልቁ የአትሌቲክስ ውድድር ውጤት አሁንም በኤሌክትሮኒክስ የሰዓት መቆጣጠሪያ የማይደገፍ መሆኑ በተለይም በአጭር ርቀት እና በሜዳ ላይ ተግባራት ውድድሮች ላይ የሚሳተፉ አትሌቶች ልፋት ተገቢውን እውቅና እንዳያገኝ እያደረገ ይገኛል፡፡ የሻምፒዮናውን ውጤቶች በዘመናዊ እና ዓለም አቀፉን መለኪያ በሚያሟላ መልኩ አለመያዝ በአህጉራዊ እና አለም አቀፋዊ ውድድሮች ላይ ለተሳትፎ የሚያበቁ ውጤቶችን በማስመዝገቡ ረገድ የሚኖረው አሉታዊ ተፅዕኖ ከፍተኛ መሆኑ ከግምት ውስጥ ገብቶ አሁንም መፍትሄ ያልተበጀለት ጉዳይ ነው፡፡ 
 
• የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ወደ ሚዲያ/ለአጠቃላዩ ሕዝብ የሚያስተላልፈው የመጀመሪያዎቹን ሶስት ደረጃዎች ይዘው የሚያጠናቅቁ አትሌቶችን ውጤት ብቻ መሆኑ አወዳዳሪው አካል የሚያደርገውን የራሱን ውድድርም ሆነ አትሌቶቹ የለፉበትን ውጤት ከማስተዋወቅ አኳያ በቂ አይደለም፡፡
  
• በወንዶች የጦር ውርወራ እና የሴቶች ምርኩዝ ዝላይ ብሔራዊ ሪኮርዶች እንደተመዘገቡ ይታመናል፤ በሴቶች 100ሜ መሰናክል እና የወንዶች 400ሜ መሰናክል የተመዘገቡት ሰዓቶችም የምንግዜውም ፈጣን ሊሆኑ ይችላሉ፡፡ ነገር ግን ውድድሩ በኤሌክትሮኒክስ ታይሚንግ ያልተደገፈ እና የንፋስ ንባብ ያልነበረው መሆኑ ውጤቶቹ በዓለም አቀፍ ደረጃ ተቀባይነት እንዳይኖራቸው የሚያደርግ ነው።

• በ20 ኪ.ሜ የእርምጃ ውድድር ላይ በሁለቱም ፆታዎች የተመዘገቡት ሰዓቶች ከሚጠበቀው በላይ እጅግ በጣም ፈጣን እና እውነታዊ አለመምሰላቸው በውድድሩ ላይ የተፈጠረ አንዳች ስህተት መኖሩን የሚያመላክቱ መሆኑ፡፡ እንዲህ አይነት ለማመን የሚከብዱ እና ጥርጣሬን የሚፈጥሩ አይነት ውጤቶች ሲመዘገቡም የተፈጠረ ስህተት መኖር አለመኖሩን ለማጣራት አለመሞከሩ፡፡
     
• የሴቶች 10 ኪሎ ሜትር ውድድር ላይ ለውድድር የማይፈቀድ የጎዳና ላይ መሮጫ ጫማን በመጠቀም የተመዘገበ ውጤት በሪኮርድነት ጭምር ተይዞ መፅደቁ። ብሔራዊ ፌዴሬሽኑ ከተከለከሉ ጫማዎች ጋር የተያያዙ ዓለም አቀፍ ሕገ ደንቦችን ማወቅና መተግበር ቢገባውም በሴቶች 10 ሺህ ሜትር ውድድር ላይ የተከሰተው ነገር የውድድር ሕገ ደንቦቹ መረጃ በፌዴሬሽኑ ውስጥ በትክክል የተሰራጩ እንዳልሆነ የሚያመላከት ነው፡፡  

• በሴቶች 1500 ሜትር የግማሽ ፍፃሜ ውድድር ላይ አትሌት ዳዊት ስዩም የሻምፒዮናውን ሪኮርድ ያሻሻለችበት ውጤት እንደተመዘገበ በውድድሩ ወቅት በተደጋጋሚ ሲነገር ከተደመጠ በኋላ ግልፅ ባልተደረገ ምክንያት ውጤቱ በሐዋሳው ውድድር ላይ ተሻሻሉ ከተባሉት የሻምፒዮናው አዲስ ሪኮርዶች ዝርዝር ውስጥ ሳይካተት መቅረቱም የፌዴሬሽኑን ግልፀኝነት ጥያቄ ምልክት ውስጥ የሚከት ነው፡፡

ከላይ የተዘረዘሩት አዎንታዊ እና አሉታዊ ጎኖች ለረጅም ግዜ የኢትዮጵያን አትሌቲክስ ስፖርት እንቅስቃሴዎች በቅርበት ከመከታተሌ አንፃር በራሴ እይታ ያስቀመጥኳቸው እንደመሆናቸው አንዳንዶቹ ሀሳቦች አከራካሪ ሊሆኑ ይችላሉ፡፡ ሆኖም የውድድር ደንቦችን በአግባቡ ከማስፈፀም አኳያ በታዩት ክፍተቶች ዙሪያ ምንም የሚያከራክር ጉዳይ ስለሌለ በወቅታዊ የውድድር ደንቦች ዙሪያ የግንዛቤ እጥረት ላለባቸው የስፖርቱ ባለድርሻ አካላት በሙሉ አስፈላጊውን ገለፃ እና ትምህርት መስጠት የፌዴሬሽኑ ኃላፊነት ነው፡፡ ከውድድር ጋር የተያያዙ ደንቦችን ከመጣስ አኳያ በሀገር ውስጥ በሚደረጉ ውድድሮች እንደቀላል ነገር የሚታለፉ ጉዳዮች በዓለም አቀፍ ውድድሮች ላይም ተደግመው እንደግል አትሌቶችን እንደቡድን ሀገርን ትልቅ ዋጋ ሊያስከፍሉ ይችላሉና አስፈላጊው ጥንቃቄ ቢደረግ መልካም ነው፡፡ ባለፈው መስከረም ወር በቪየና ሲቲ ማራቶን ውድድሩን በአሸናፊነት ጨርሶ የነበረው ኢትዮጵያዊው ደራራ ሁሪሳ የገጠመውን አንዘንጋው! 

ሀገራችን ኢትዮጵያን በመልካም ጎኑ ስሟ እንዲነሳ በሚያደርገው እና በትልልቅ ዓለም አቀፍ የውድድር መድረኮች ላይ የኩራታችን ምንጭ በሆነው የአትሌቲክስ ስፖርት እንደጎረቤታችን ኬንያ ዓለም አቀፍ ውድድሮችን የማስተናገድ የብቃት ደረጃ ላይ ደርሰን ማየት የዘወትር ምኞቴ ነው፡፡ የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌደሬሽንም የውድድሮቹን ጥራት ለማሻሻል በትኩረት እንደሚሰራ ተስፋ አደርጋለሁ።      
      
የ10,000ሜ. አሸናፊ የሆነችው ግርማዊት ገብረእግዚአብሔር (Photo by EAF)

በመጨረሻም በሀዋሳ በተካሄደው 51ኛዉ የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ሻምፒዮና ከመሮጫ ጫማ ጋር የተያያዙ ደንቦችን በማስከበሩ ረገድ የተፈጠረውን ክፍተት እንደማስተማሪያ ብንጠቀምበት በሚል የሚከተለውን ለማለት ወደድኩ፡-

የመሮጫ ጫማ ደንቦች ለትራክ ውድድር

64 ደቂቃ ከ14 ሰከንድ በሆነ ሰዓት የዘንድሮ የራስ አል ካይማህ የግማሽ ማራቶን ውድድር አሸናፊ የሆነችው ግርማዊት ገብረእግዚአብሔር በሐዋሳ በተከናወነው 51ኛው የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ሻምፒዮና ላይ 31 ደቂቃ ከ21.5 ሰከንድ  በመግባት የ10,000ሜ. አሸናፊ ሆናለች፡፡ የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽንም ዓለም አቀፉን ደንብ ከግምት ባላስገባ ሁኔታ ውጤቱን በአዲስ የሻምፒዮንሺፕ ሪኮርድነት ጭምር አፅድቆት አልፏል፡፡ ይሁን እንጂ መጋቢት 20/2014 በተደረገው የሴቶች የፍፃሜ ፉክክር ላይ በኢትዮጵያ ምድር የተመዘገበ የምንግዜውም ፈጣን የሴቶች 10 ሺህ ሜትር ሰዓት የሆነው ውጤት በአለም አትሌቲክስ ዘንድ እውቅና ሊሰጠው የማይችል ነው።

ለምን?

አትሌቷ የሶል ውፍረቱ 40ሚሜ የሆነ ዙምኤክስ ቬፐርፍላይ (ZoomX Vaporfly) ጫማ አድርጋ በመወዳደሯ ምክንያት።

ደንቡ ምን ይላል?

በትራክ ውድድሮች ላይ የሚፈቀደው ከፍተኛው የሶል ውፍረት ፡-
– 20ሚሜ ከ 800ሜ በታች ለሆኑ ውድድሮች እና ለሁሉም የሜዳ ላይ ተግባራት (ከስሉስ ዝላይ በስተቀር)

– 25ሚሜ ለ800ሜ እና ከዛ በላይ ለሆኑ ውድድሮች እንዲሁም ለስሉስ ዝላይ

– 40ሚሜ ለትራክ ላይ የእርምጃ ውድድሮች

እነዚህ ደንቦች እ.ኤ.አ. እስከ ኦክቶበር 31, 2024 ድረስ በሥራ ላይ ይውላሉ። ከኖቬምበር 1 ቀን 2024 ጀምሮ ለ800ሜ እና ከዚያ በላይ ለሆኑ ውድድሮች እንዲሁም ለስሉስ ዝላይ የሚፈቀደው ከፍተኛ የሶል ውፍረትም ወደ 20 ሚሜ ዝቅ የሚል ይሆናል።

የትራክ ላይ መወዳደሪያ ስፓይክ ጫማ ከሌለኝስ?  

ደንቡ የጎዳና ላይ የመሮጫ ጫማዎች በትራክ ላይ እንዳይደረጉ አይከለክልም ነገር ግን በ25 ሚሊ ሜትሩ ገደብ ምክንያት 30 ሚሜ ወይም 40 ሚሜ የሆኑ የጎዳና ላይ መሮጫ ጫማዎች በትራክ ውድድሮች ላይ እንዲደረጉ አይፈቅድም፡፡

ለበለጠ መረጃ :-
https://www.worldathletics.org/news/press-releases/new-athletic-shoe-regulations-approved-2022

Continue Reading

Opinions

On the TPLF’s Love Affair With ‘Genocide’

Published

on

WhatsApp-Image-2021-11-04-at-12.41.51-AM
Ethiopia's Lalibela, a UN World Heritage Site, now under Tigrayan forces control

Today, the joint investigation report by the Ethiopian Human Rights Council and the UNHR
on human rights violations committed in Tigray concluded that there is no evidence that genocide has taken place so far. While this is a bit of a setback for the TPLF, which has wanted the world to believe—since the 1990s, even as the TPLF was dominating power in Addis—that a genocide has been perpetrated against the people of Tigray, unfortunately the group still appears to be determined to make genocide a reality. This is confusing for people who don’t understand why the TPLF is obsessed with genocide, why its internet cadres began using #TigrayGenocide in April 2020, months before the war began. So many weapons have been deployed in this war, and among them: confusion and obfuscation.


In the past several months and more so in the past few weeks, we have been getting
testimony after testimony from allied Amhara forces fighting the TPLF that Tigrayan residents of cities in Wollo have been collaborating with the TPLF by a) attacking ENDF and allied forces from behind; b) forcing ENDF and allied forces to withdraw from towns and cities afraid of committing large scale massacres by firing back at the civilians (Tigrayans) firing at them; c) helping the TPLF locate and execute young Amharas believed to be a threat; and d) in at least one horrifying account by an IDP who managed to escape occupied territories, handing TPLF soldiers a list of women to rape. Another shocking development in the past several months has been the widespread use of child soldiers by the TPLF, which, according to experts who have studied the practice, is an “alarm bell” calling attention to possible plans to commit mass atrocities. The use of child soldiers by the TPLF and its attendant implications, along with the widespread deployment of civilian sleeper agents in Amhara cities the TPLF has taken over, serves to create an overall perception of every Tigrayan as a potential enemy, sowing fear and mistrust.

Many Ethiopians are looking at this and wondering: why are Tigrayan elites on the internet
either celebrating the TPLF’s advance via these toxic methods or silent about all this? How can they not see how dangerous this is for everyone, especially for Tigrayans who live outside Tigray? How can they not see that there is no “winning” after stoking all this lasting animosity? Do Tigrayan elites not understand that there can be no justice for Tigray—whether Tigray secedes or not—unless there is justice for her neighbors, for Tigray does not exist in a vacuum? The questions are being asked but nobody is answering them. Our academic class has largely failed to offer viable analyses of the ideas driving this war, as they failed over the past fifty years in regards to coming up with a fitting paradigm for understanding Ethiopia’s unique situation.


Here is my humble attempt to explain what I think is happening with the TPLF’s obsession
with—and with its active attempt to inspire—genocide:


The most successful psychopaths in any field understand that, in order to win anything, one
must risk everything, including the very thing one is supposedly fighting for. In the case of the
TPLF (and associated Tigrayan political elites), whose motto appears to be “give me supremacy or give me death,” that “everything” they are risking is the lives of ordinary Tigrayans in whose names they are fighting. We have seen over the past several months the extent to which the TPLF is willing to go to sacrifice ordinary Tigrayans in order to get what it wants: wave after wave after wave of young poorly armed and inexperienced Tigrayans were unleashed upon ENDF and Amhara and Afar forces in order to force the latter to waste ammunition and energy before the more experienced soldiers are sent.


So, for a political group who sends tens of thousands, if not hundreds of thousands, of
young Tigrayans towards open fire, violence against hundreds of thousands of Tigrayans is nothing if it means the TPLF will in the end win the “prize” it has been obsessed with for decades: genocide. You see, merely attaining power in Addis Ababa is not enough for the TPLF, whose core driving ideology is Tigrayan supremacy. Power is temporary; anybody can take it away from you, and the 2018 uprisings demonstrated that. Genocide is forever. Nobody can take away from you the story of genocide committed against your people.


The TPLF looked at countries like Israel and Rwanda and realized what a potent instrument
genocide is for establishing perpetual minority rule. We have some indications suggesting that the TPLF views Israel as a model. When the war between Ethiopia and the TPLF began in November 2020, Sekoutoure Getachew, a TPLF official, went on TV to tell us that the TPLF’s decision to launch a preemptive attack on the Northern Command was inspired by how the young state of Israel, feeling threatened by her neighbors, launched preemptive attacks against them in the “six-day war” of 1967. Another indication is the manner in which the TPLF, during its 27 years in power, invested heavily in creating a wealthy and strongly networked Tigrayan diaspora which has been used to lobby and influence western governments and organizations much in the same way as the Jewish diaspora aids the state of Israel. The TPLF has figured out that truth does not matter in politics, especially in international politics. If you have the wealth and the personnel to peddle your preferred narrative, if you have the military power to subdue the people you want to subdue, if you are willing to make concessions to external forces (US, Egypt, etc), you can do unspeakable things to others (much like the state of Israel does to Palestinians) and still manage to portray yourself as the victim.
This calculation is so far working for the TPLF, but nothing would seal the deal like the actual
commission of genocide—or something that looks like it—against Tigrayans. As we have seen over the past twelve months, western governments and organizations have shown their willingness to adopt TPLF’s narratives without scrutiny and can easily reward the TPLF with its much pursued prize, genocide, even if actual genocide doesn’t take place.


But why does the TPLF need genocide to establish minority rule? Because, as we saw in their
first tenure in power, you can only rule with an iron fist for a limited period of time. Leaders of the TPLF are adherents of Tigrayan supremacy: the idea that Tigrayans, as the “only” heirs of the Axumite empire, are the natural rulers of the Ethiopian state, and cannot be ruled by “barbarians” south of them. The only acceptable power arrangement for the TPLF is one in which Tigrayans are either directly dominating political power or are the perpetual kingmakers pulling all the major strings. Anything outside that, any system that forces Tigrayans to live on equal footing with everyone else, is unacceptable. And this kind of domination by a minority cannot coexist with a democratic system that the majority of Ethiopians clearly prefer. So, the TPLF needs something more potent than pure political/economic/military power to justify bypassing democracy to establish itself as the permanent ruler/kingmaker of Ethiopia. It needs a new and powerful raison d’être to justify its domination not just to Tigrayans and the rest of Ethiopians but, and most importantly, to the rest of the world. If a genocide were to be committed against Tigrayans (or if the U.S. decides to reward the TPLF with the genocide label even in the absence of it), then the TPLF can license itself to impose all manner of drastic measures aimed at “protecting Tigray and
Tigrayans.” This could be anything from redrawing internal borders (and taking debilitating
measures against the peoples whose lands are being robbed—most likely Amharas and Afaris—so that they will never be in a position to assert themselves) to ethnic cleansing and genocide against populations considered to be a threat. And when you oppose it, the TPLF will say “you committed a genocide against Tigrayans” over and over and over, and its western backers will repeat the same chorus. If they have been this loud over a non-existent genocide over the past twelve months, just imagine what it would be like if the U.S. or UN rewards them with that label.


And this is where the Ethiopian government’s major dilemma comes from: if ENDF and
Amhara forces fight to regain their cities and towns, they risk committing large scale massacres. The TPLF networks reported to be operating within these cities wear civilian clothing and fire at the armies from inside civilian establishments, in an apparent attempt to set up pro-Ethiopia forces. Pro-Ethiopia forces are essentially being dared to commit large scale massacres in order to win back their own cities. So far, they are choosing to withdraw from these towns and cities. But that is another problem: not only is the TPLF committing unspeakable violence against civilians and destroying infrastructure in those cities, the takeovers are emboldening it to continue pressing, giving young people back in Tigray false hope that they are winning and—this is very important—the false idea that they are being “welcomed” by locals in those cities. Then more and more and more young Tigrayans are sent to their deaths.


So the Ethiopian government is stuck between a rock and a hard place. One option is
allowing its forces to do whatever it takes to take back territory, thereby offering protection to its citizens in Wollo and elsewhere, but also risking the “genocide” label by western governments who have been eagerly waiting for such an opportunity so that they can blackmail the government into submitting itself to their wishes on GERD and other issues. Option two is avoiding large scale violence and allowing the TPLF to take power in Addis Ababa and do to Ethiopia what it wishes. One of the things it might do to Ethiopia, according to its leaked strategy document, is force a confederation that will no doubt privilege some states, i.e. Tigray, more than others, and that will no doubt be designed to subdue some populations—mainly Amharas and Afaris—who are considered obstacles to Tigray’s aspirations of domination and expansion (in the TPLF’s original manifesto, Afar is claimed as Tigray land).


And there is absolutely no doubt that the TPLF will make big concessions on the GERD in
order to compensate its western and Egyptian backers, if not redraw borders to make Benishangul Gumuz Tigrayan territory. If you think this is wild, read about the history of the state of Israel, the TPLF’s model state. The redrawing of borders that the TPLF undertook in 1991 was also wild at the time; people don’t think of it as outrageous anymore because the fact that they held onto the territory for 30 years has normalized the event in our minds. And that’s all the TPLF needs: another thirty years to normalize all the outrageous things they will do next.

One may argue that this is a false dichotomy, that there is a third or even maybe fourth option: winning these cities back without mass violence much in the same way the ENDF managed to do during its first campaign in Tigray. We all should pray for such a miracle, of course. However, one can also say that in the early days of the war, the TPLF was mostly withdrawing from Tigrayan cities to avoid urban warfare. And even when they engaged in urban warfare, it was not at the same scale and intensity as has been the case over the past four and half months or so. Starting in mid June, the TPLF’s use of civilians as human shields and fighters stopped being just another weapon in its arsenal and became a center of its operations. The near collapse of the ENDF inside Tigray right before its withdrawal was precipitated by the TPLF’s intensified use of “civilians” to trap the ENDF. Many ENDF soldiers chose to surrender rather than fire at those “civilians.” It is still possible to avoid large scale violence in the attempt to retake towns in Wollo, but the risk for it is very high, and is possibly behind the federal government’s reluctance to take decisive actions.


The point is: barring miracles, the Ethiopian government is positioned to lose something
one way or another. All that is left is choosing its preferred poison. Perhaps one thing to consider for the federal government is: the rights of Amharas and Afaris to defend themselves against the existential threats posed against them by the TPLF is much bigger than the national government’s concerns about its place and relationships with the rest of the world. If the federal government decides to risk the disintegration of Ethiopia, like it has done so far either due to incompetence or severe fear of committing large scale violence, that is fine for the federal government. But when you allow that disintegration to happen, please don’t leave the people of Amhara and Afar in a vulnerable position, unable to defend themselves and their lands. If we must return to the State of Nature, at least give these two peoples, who have so far shed more blood than anyone else in defense of their country, a chance to preserve their lives and their lands. Give them the resources they need to defend themselves before it is too late for them even if you feel it is too late for Ethiopia. Anything less is just a continuation of the gross criminal negligence that the federal government has been guilty of so far.

Continue Reading

Trending