Connect with us

Articles

በገብረመድህን አርአያ – በሰሜን በጌምድር (ጎንደር) ወልቃይት ፀገዴ፣ ፀለምት በአማራው ላይ ተስፋፊው ተሓህት/ህወሓት የፈጸመው የዘር ማጽዳት ወንጀል

Published

on

Hand Draw - Ethiopa Map 1

በገብረመድህን አርአያ
በሰሜን በጌምድር (ጎንደር) ወልቃይት ፀገዴ፣ ፀለምት በአማራው ላይ ተስፋፊው ተሓህት/ህወሓት የፈጸመው የዘር ማጽዳት ወንጀል

ይህ ታሪካዊ መረጃ በተቀነባበረ መልኩ የሚጀምረው ገና ተጋድሎ ሓርነት ህዝቢ ትግራይ (ተሓህት) ሲፈጠር ጀምሮ አስቀድሞ ለማጥፋት ያነጣጠረው በአማራው ህዝብ ላይ እንደሆነ በማስገንዘብ ነው።
ከዚህ በመነሳት የተሓህት ፕሮግራም ገና ከ1967 ጀምሮ የረቀቀው በዲማ ኮንፈረንስ በየካቲት ወር 1968 ከ150 ያነሱ የተሓህት ታጋዮችን በማሰባሰብ ሕጋዊ ሆነ ተብሎ ቢነገርም፣ ሁሉም ታጋዮች ግን አልተቀበሉትም። በመጥፎ መልኩ የተዘጋጀውና አማራውን በማውገዝና ጠላት ብሎ የፈረጀ ነው። በኢትዮጵያና በህዝቧ፣ 1ኛ፣ የኢትዮጵያን ሉአላዊነት አውዳሚ፣ 2ኛ፣ አንድነቱን ጠብቆ ለዘመናት አብሮ የኖረውን የኢትዮጵያ ህዝብ በጎሳ በዘር ለመበታተን ተደምሮና ተቀንሶ የተቀነባበረ አደገኛ ፕሮግራም በማለት አውግዘውት ነበር። ከነዚህ ካወገዙት መካከል ለምሳሌ ለመጥቀስ፤ አስገደ ገብረሥላሴ፣ ካህሳይ በርሄ (ዶ/ር ግንጽል)፣ ተሾመ ጉዶ፣ ሲሆኑ እነዚህ በህይወት ያሉ ሲሆን፣ እቁባዝጊ በየነ፣ አሰፋ ገብረዋእድ፣ አጽብሃ ዳኘው፣ ዘርኡ ገሰሰ (አጋአዚ) ገሰሰው አየለ፣ ዶ/ር አታክልት ቀጸላ፣ ዘወንጀል በየነ፣ መሃረ ተክሌ ወዘተ እነዚህ ፕሮግራሙን በጠነከረ አቋም ስለተቃወሙ የተገደሉ ናቸው። ተሓህት የፕሮግራም ዝግጅቱን ንድፈ ሃሳብ የጀመረው ገና በረሃ ሳይወጣ ማገብት ተብሎ በሚጠራበት ከ1966 ጀምሮ ነው። ይህንን ፕሮግራም በሃላፊነት ያዘጋጀው አረጋዊ በርሄ ሲሆን፣ ጥር 1967 ለወታደራዊ ስልጠና ኤርትራ፣ ስህል ወርደው
ፕሮግራሙን በማጠናከር የተሰማሩት የትጥቅ ትግሉ መሪዎች አረጋዊ በርሄ፤ በዋና ሃላፊነት፣ ግደይ ዘርአጽዮን፣ አስፍሃ ሃጎስ፣ በህመም የሞተ፣ ዘርኡ ገሰሰ፣ በወያኔ የተገደለ፣ ሥዩም መስፍን፣ ሃይሉ /ነጠበ/መንገሻ ሲሆኑ ብዙ የጎደለው እንዳለ ተስማምተው በይደር ወደ ደደቢት ተዘዋወረ።


የካቲት 11፣ 1967 ታጋዮቹ ደደቢት በረሃ እንደገቡና የትጥቅ ትግሉ እንደተጀመረ፣ ግንባር ቀደም ተግባራቸው ሶስት ነጥቦች ላይ ነበር ትኩረት ይሰጠው። 1ኛ፣ የድርጅቱን ስም ማውጣት፣ 2ኛ፣ ለወደፊቱ ለምትመሰረተው የትግራይ ዲሞክራሲያዊ ሪፓብሊክ የግዛት ስፋት ከውጭ ሃገር፣ ሱዳን በሚገኘው መልኩ ማዘጋጀት፤ 3ኛ፣ ፕሮግራሙን ለመጨረሻው ዝግጅቱ ታማኝ ታጋዮችን በማሰባሰብ ለሚከተሉት ሰዎች፣ ማለትም፣ አረጋዊ በርሄ፣ ሊቀመንበር፣ ሥዩም መስፍን፣ አባይ ፀሃየ፣ ስብሃት ነጋ፣ መለስ ዜናዊ፣ አውአሎም ወልዱ፣ ስየ አብርሃ፣ ግደይ ዘርአጽዮን ወዘተ ሃላፊነቱ ተሰጠ። ለዚህ መሰናዶ ከበጌምድር ጠቅላይ ግዛት፣ ፀገዴ፣ ፀለምት፣ ሁመራ፣ ወልቃይት እንዲሁም ከወሎ ጠ/ግዛት፣ ራያና ቆቦ፣ ወልድያ፣ አላማጣ እስከ ላይኛው ሃሸንጌ ሃይቅ ድረስ በማጠቃለል የትግራይ መሬት ነው ተብሎ በመወሰን የፕሮግራሙን አቋም ደመደመ። ይህ ፕሮግራም ለመጀመሪያ ጊዜ በእጅ ጽሑፍ ተዘጋጅቶ ወደ 30 ገጽ የሚሆን ተባዝቶ በመጽሓፍ መልክ ተጠርዞ በብዛት ተያዘ።በሃላፊነት የጻፉት አረጋዊ በርሄ፣ ስብሃት ነጋ፣ ሥዩም መስፍን፣ መለስ ዜናዊ፣ አባይ ፀሃየ ናቸው። በየቦታው እንዲሰራጭም ተደረገ።

ከመጀመሪያ እስከ መጨረሻው ኢትዮጵያን ለመበታተን፣ ሕዝቧን በዘርና በጎሳ የከፋፈለ፣ አማራውን ደመኛ ጠላት ብሎ ያወገዘ ሆኖ የመጣና እነሆ ዛሬ የኢትዮጵያ ሕገመንግሥት የሆነ አስተሳሰብ ነበር።
አማራ የትግራይ ህዝብ ደመኛ ጠላት ነው፣ ከሚለው ቀጥሎም ለብዙ ዓመታት ነፃ ሃገር ትግራይ ነፃነቷ ተገፎ በአማራው (ኢትዮጵያ) ቅኝ አገዛዝ ወድቃለች፣ በማለት ብዙ ይተነትናል። በአጼ ዮሃንስ ዘመነ መንግሥት ሃይሏ በርትቶ በአካባቢዋ የነበሩትን ነገሥታት በቁጥጥር ስር አውላ ነበር። ይሁን እንጂ አፄ ዮሃንስ ከሞቱ በኋላ በዳግማዊ ምኒልክ አማካኝነት ትግራይ በሸዋው ማእከላዊ ግዛት ስር ወደቀች። ከዚህ ጊዜ በኋላ ነው አማራው የመሳፍንት ቡድን እና ተከታዮቹ የትግራይን ነፃነት ገፈው የህዝቧን አንድነት ያናጉት። በግልጽና ስውር በሆነ ዘዴዎች (ሸዋዊ ዘይቤዎች) የትግራይ ህዝብ በድንቁርና፣ በበሽታ፣ በረሃብ አዘቅት ውስጥ እንዲሰምጥ ያደረጉት እያለ ይቀጥላል። ከላይ የተጠቀስውና ሌላውን ጨምሮ ተሓህት የትግራይ ህዝብ ጠላት አማራ ነው፣ ነፃ ሃገር የነበረቸው ትግራይ ሃገርህ በአማራ (ኢትዮጵያ) ቅኝ ግዛት ሆና አንተ ለክፉ መከራ ተረግህ በማለት አመራሩ በሙሉና የተሓህት ታጋዮች ወደ ህዝቡ ተበታትነው ፖለቲካቸውን አስተማሩት። ማንኛውም የትግራይ ህብረተሰብ ይህ የምትናገሩት ሁሉ ፈጽሞ ከእውነት የራቀና የራሳችሁ የፈጠራ ፖለቲካ ነው። አማራ ለትግራይ ህዝብ ጠላቱ አይደለም፣ ወንድሙና እህቱ እንጂ። ሁላችንም ተቃቅፈን በጋብቻ ተሳስረን በፍቅርና በሰላም የምንንሮር የአንዲት ኢትዮጵያ ልጆች ነን። ከትወልድ ወደ ትውልድ ሲተላለፍ የመጣውን ፍቅርና ወንድማማችነትን እህታማችነት አታፍርሱብን። አማራ (ኢትዮጵያ) ትግራይን በቅኝ ግዛት ስር አድርጋለች የምትሉት ከየት ያገኛችሁት እንደሆነ እኛ አናውቅም። ትግራይ ዱሮም አሁንም የኢትዮጵያ የታሪክ ማእከል ናት በማለት የትግራይ ህዝብ ከገጠር እስከ ከተማ ተቃውሞ አደረሰባቸው። በዚህም ምክንያት የገጠርና የከተማ ኗሪው በቀን እና በሌሊት እየተለቀመ በሽብርተኞች ቡድን ተገደለ፣ ቤቱ ፈረሰ፣ ህፃናት በየቦታው ወድቀው ቀሩ። ለኢትዮጵያ አንድነትና ሉአላዊነት ከፋሽስቱ ጣሊያን ጋር የተዋጉ የትግራይ ኢትዮጵያዊ አርበኞች በወያኔ ትሓህት ከየቤታቸው እየተለቀሙ ሃለዋ ወያኔ ገብተው በጥይት እየተረሸኑ መስዋእትነት ከፈሉ። ይህ በዚህ እንዳለ፣ በ1969 የተሓህት መሪዎች ስብሃት ነጋ፣ አረጋዊ በርሄ፣ አባይ ፀሃየ፣ መለስ ዜናዊ፣ ሥዩም መስፈን፣ ስየ አብርሃ፣ አውአሎም ወልዱ ተሰባስበው በትግራይ ውስጥ የሚኖረው አማራ፣ ኦሮሞና ሌላውም ከትግራይ ይውጡ፣ ትግራይ2 ለትግራይ ህዝብ ብቻ ናት የሚል አዋጅ አስተላለፉ። ይህንን ሃሳብ ያልደገፉት ግደይ ዘርአጽዮን እና ዶ/ር አታክልት ቀጸላ ብቻ ነበሩ።

በዚህ የዘረኝነት አጥር ውስጥ የገባው የተሓህት አመራር ከ1969 መጨረሻ በፕሮግራሙ ያካተተው የትግራይ መሬት ብሎ ያስቀመጠው ወልቃይት፣ ፀገዴ፣ ፀለምት፣ ሁመራ ቃፍታ ላይ ማነጣጠር ጀመረ። በተቻለ መጠንም በፍጥነት ተቆጣጥረን በትግራይ ውስጥ ገብተው በተሓህት አመረር ስር መተዳደር አለባቸው የሚል እቅድ ያዘ። ከዚህ ቀደም ብሎ በአርከበ እቁባይ የተዘጋጀ ካርታ ከበጌምድር ጠ/ግዛት ከላይ የተጠቀሱትን ቦታዎ ች፣ ከወሎ ጠ/ግዛት ራያና ቆቦ፣ አላማጣ፣ ወልዲያ፣ አፍላ ደራ ለምትመሰረተው አዲሲቷ ዲሞክራቲክ ሪፑብሊክ ትግራይ ሲካተቱ፣ በምእራብ በኩል ደግሞ ወልቃይት፣ ሁመራ ፀለምት፣ ፀገዴ ተጨምረው ትግራይ ከሱዳን ጠረፍ ጋር እንደትገናኝ፣ በደቡብ በኩል ደግሞ ወደውሃ ምላሽ ትግራይ እንድትሰፋ ሲወስን፣ እነዚህቦታዎች ሁሉ ለምና ሃብታም መሬቶች ናቸው። ይህንን ውጥን ለማሳካት በወልቃይት ፀገዴ ተሓህት ህዝቡን እያፈነ ማጥቃት ጀመረ። የወያኔ/ህወሓት/ተሓህት መሰረታዊ የታሪክ ወንጀል የወላቅይት ፀገዴ፣ ፀለምት፣ ሁመራ ኢትዮጵያ ከተፈጠረች ጀምሮ ለብዙ ሺህ ዘመናት ሲወርድ ሲዋረድ የመጣው ታሪካዊ ቦታዎች የበጌምድር (ጎንደር) ግዛት መሬት ነው። ታሪክም የሚያረጋግጠው ይህ ነው።። በምንም ተአምር ከትግራይ ግዛት ጋር ግንኙነት የለውም። የሚገናኙበት ኢትዮጵያውያን እና ኢትዮጵያዊነት ነው። በጌምድርም ሆነ ትግራይ የአንዲት ኢትዮጵያ ልጆች ናቸው። በሃይማኖትና በጋብቻ ተያይዘዋል። ይህ ደግሞ በሁለቱ ህዝብ ማካከል ብቻ ሳይሆን በመላው ኢትዮጵያ ውስጥም ያለ ነው። ኦሮሞው ከትግሬ፤ ትግሬው ከአማራ፣ አፋሩ ከጋምቤላው፣ ጉራጌው ከሌላው ዘር ጋር ወዘተ የተደባለቀ ህዝብ ነው። የኢትዮጵያ ህዝብ በደም የተቆራኘና አንድ ህዝብ ነው። አመቺ ጊዜ እስኪያገኝ በመጠባበቅ የቆየው የተሓህት አመራር በየካቲት መጨረሻ በ1968 በድርጅቱ የተሰባሰቡት ታጋዮች ዲማ በተባለው በአጋሜ አውራጃ ውስጥ የዲማ ኮንፈረንስ በመባል የሚታወቅ ኮንፈረንስ በማካሄድ ከ150 የማይበልጡ ታጋዮች በአረጋዊ በርሄ ሊቀመንበርነት በሚመራ ስብሰባ ፕሮግራሙ ቀርቦ እንዲጸድቅ ቢጠይቅም ታጋዩ አልተቀበለውም። ይሁንና፣ ሊቀመንበሩ ጸድቋል ብሎ የድረጅቱ የፖሊሲ አቋም ሆኖ እስከመጨረሻው ቀጥሏል። የተሓህት የሰሜን በጌምድር የወረራ ዝግጅት ተሓህት ወደ ሰሜን በጌምድር/ጎንደር በቀጥታ ሃይሉን አሰባስቦ አልገባም። ምክንያቱም፡

1. በመጀመሪያ ጊዜና ሁኔታውን ማስተከካል ፈለገ፤
2. ኢህአፓ በአካባቢው በስፋት ይንቀሳቀስ ስለነበር በአቅምና በትጥቅ ጥራት ህወሓት ዝቅተኛ ስለሆነ፣ ኢህአፓዎቹ ይመቱናል፣ ያጠቁናል የሚል ስጋት ስለአደረበት፣
3. የወልቃይት ፀገዴ ፀለምት ህዝብ አይቀበለኝም ብሎ በማመኑ፣ አቅሙን እስኪያጠናክር መዘግየቱን እንደ አማራጭ ወሰደ። ቢሆንም ግን፣ ተሓህት በድብቅ በ1969 መጨረሻ ወደ ፀገዴና ፀለምት መሽሎክሎኩን ቀጠለ። በዚህ ጊዜ ደጀና ውስጥ ሽሬላ ተብላ በምትታወቀው ትንሽ ከተማ የተሓህት ታጋዮች ቅዳሜ ቀን ህዝቡን ሲያንገላቱ በነበሩበት ወቅት ማንነቱ ባልታወቀ ቡድን ሁለቱን የተሓህት ታጋዮች በገበያው መሃከል ገደሏቸው። በታህሳስ 1972 በሻእቢያና በጀብሃ፣ በወያኔና በኢህአፓ መካከል በተነሳው ጦርነት በኢህአፓ በሰነዘረውጥቃት ተበታትነው ሱዳን ገቡ። በወልቃይት ፀገዴ ፀለምት የኢህአፓን ሠራዊት በበላይነት ሲመሩት የነበሩት ታምራት ላይኔ፣ በረከት ስምኦን፣ አዲሱ ለገሰ፣ ተፈራ ዋለዋ፣ ታደሰ ቅንጥሾ ወዘተ አስቀድመው ለወያኔ ህወሓት እጃቸውን ስለሰጡ፣ እየመሩም የኢህአፓን ሠራዊት እንዲጠቃ አደረጉ። በጥቃቱም ብዙዎቹ ተገደሉ፣ ተማረኩ፤ የተማረኩትም ተረሸኑ። ለዚህ ተጠያቂቆቹ ስብሃት ነጋና አባይ ፀሃየ ናቸው። ይህ ጊዜ ወያኔ ህወሓት ፍላጎቱ የተሳካበት ወቅት ነበር። አሁን ያለው የህወሓት አመራር በ1971 የካቲት 5 ቀን የተመረጡት፤ ስብሃት ነጋ፣ የድርጅቱ ሊቀመንበር፤ አረጋዊ በርሄ፣ ወታደራዊ አዛዥ፤ አባይ ፀሃየ፤ ግደይ ዘርአጽዮን፤ ስዩም መስፈን፤ መለስ ዜናዊ፤ አውአሎም ወልዱ፤ አርከበ እቁባይ፤ ዘርአይ አስገዶም፤ ተወልደ ወ/ማርያም፤ ገብሩ አስራት፤ ስየ አብርሃ፤ ጽድቃን ገ/ተንሳይ፤ ዶ/ር አታክልት ቀጸላ፣ በወያኔ የተገደለ፤ አስፍሃ ሃጎስ፣ ታሞ የሞተ ናቸው። የህወሓት ከፍተኛ አመራር የነበሩና ሁሉን ትእዛዝ የሚሰጡት ደግሞ፣ ስብሃት ነጋ፤ መለስ ዜናዊ፤ አረጋዊ በርሄ፤ አባይ ፀሃየ፤ ስዩም መስፍን፤ ግደይ ዘርአጽዮን ናቸው። በወልቃይት ፀገዴ ጥቃቱን ያቀነባበሩት አመራሮች፤ ስየ አብርሃ፤ አርከበ እቁባይ፤ ጻድቃን ገ/ተንሳይ፤ ዘርአይ አስገዶም፤
አውአሎም ወልዱ ናቸው። እነዚህ በሰሜን በጌምድር፣ ወልቃይት ፀገዴ ትእዛዝ ይጠባበቁ የነበሩ ሲሆኑ፤ ይህንን ሁሉ በበላይነት የመራው ስብሃት ነጋ ሲሆን፤ የቅርብ ተባባሪዎቹ ደግሞ አባይ ፀሃየና አርከበ እቁባይ ነበሩ። ከላይ የተጠቀሱት የህወሓት አመራር የሰሜን ጎንደር ኗሪ ሰላማዊ ህዝብ ለማጥቃት የታየው ሁኔታ አመራሩ ዝግጅት ያደረገው ነበር። በሪጅን 1 የህዝብ ግንኙነት ሃላፊ የነበረው፣ በአባቱ ወልቃይት ፀገዴ፣ በእናቱ ሽሬ የሆነው መኮንን ዘለለው፣ የተወጠነውን
ትልእኮ ይዞ ወልቃይት ፀገዴ ፀለምት እየተዘዋወረ ህዝቡን በመሰብሰብ ይህ መሬት የትግራይ መሬት ስለሆነ እናንተ ከእንግዲህ ወዲህ የሰሜን ጎንደር ዜጎች አይደላችሁም፣ የትግራይ መሬት ስለሆነ እንኖራለን ካላችሁ ትግሬዎች መሆናችሁን አምናችሁ ተቀበሉ፤ የትግራይ ዜጎች አይደለንም፣ ሰሜን በጌምድር የትግራይ አይደለም ካላችሁ ደግሞ የድርጅቱን የህወሓትን ውሳኔ ተጠባባቁ፤ የምታምኑበትን አሁን ተናገሩ በማለት ሲያስጠነቅቅ፣ ከህዝቡ በኩል ያገኘው መልስ ግን አንድ ነበር። የቀረበውን ሃሳብ ከህፃን እስከ አዋቂ፣ የወልቃይት ፀገዴና የፀለምት ህዝብ፣ እኛ የሰሜን በጌምድር (ጎንደር) አማሮች እንጂ ትግሬዎች አይደለንም፣ የታሪካችን ስር መሰረቱ የበጌምድር አማሮች ነን። ይህ ቆመህ የምትናገርበት መሬት ሰሜን በጌምድር ይባላል። ከጥንቱ ታሪካችን 3 ብትነሳም ይህ መሬት ታሪካዊ ነው። ያለፉት የኢትዮጵያ ነገሥታት ከጥንት ጀምሮ እስከ አሁኗ ሰአት በመንግሥት እውቅና ያገኘ የጎንደር፣«”የበጌምድር” ጠቅላይ ግዛት እየተባለ የሚጠራ ነው። ዋና ከተማችን ደግሞ ጎንደር ነው። የእናንተም ትግራይ ጠቅላይ ግዛት ይባላል፣ ዋና ከተማው ደግሞ መቀሌ ነው። ስለዚህ ኣናንተ የተሓህት ታግዮች ጉዳዩን ብታሱብበት ጥሩ ነው። ወደ እርስ በርስ ግጭ ያመራል።በተጨማሪም ታሪካዊ የወሰን ክልል አለን፣ እሱም ተከዜ ወንዝ ነው። የትግራይና በጌምድር የድንበር ክልሉ ተከዜ ወንዝ ነው። ከጥንት ጀምሮ የሁለቱ ኢትዮጵያውያን የድንበር ወሰን መሆኑን ልናረጋግጥ እንፈልጋለን በማለት በአንድነት ድምፅ ህዝቡ ራሱ አረጋገጠ።
ሁመራን በተመለከተ ወያኔ ተሓህት/ህወሓት የትግራይ ነው ቢልም በወቅቱ እስከ ግንቦት 1983 የኢትዮጵያ ምድር ጦር ሰፊ ጥበቃ ስለነበረው፣ ወያኔ ህወሓት መሬቱን የተቆጣጠረው አዲስ አባባን በያዘበት ጊዜ ነው። ወያኔ ህወሃት በትግ ላይ በነበሩበት ጊዜ 17 ዓመታት ሙሉ ሁመራ አልገባም፣ አልተቆጣጠረም። በአካባቢውም ድርሽ አላለም። ከላይ የተጠቀስው እንደተጠበቀ ሆኖ፣ መኮንን ዘለለው የህዝቡን አንበገርም ባይነትና የሰሜን በጌምድር አማሮች ነን ባይነት፣ ለወራት የቆየበትን ሪፖርት ለህወሓት አመራር ለስብሃት ነጋና ሌሎችም አቀረበ። ስብሃት ነጋ በመኮንን ዘለለው ላይ ወረደበት፣ ወዲያውኑም ከሪጅን 1 የህዝብ ግንኙነት ሃላፊነት አወረደው። በዚህ ክስተት ባይታሰርም የአእምሮ በሽታ ሰለባ በማድረግ አሰቃዩት። ከዚህ በመቀጠል የተነሳንበትን ታሪካዊ ትንተና በተጨባጭ ለማረጋገጥ የቀድሞውን የሃገራችን ኢትዮጵያን ካርታ በ “ሀ” እንዲሁም ወያኔ ህወሃት ኢትዮጵያን ወሮ ከያዘ በኋላ ያዘጋጀውን ካርታ በ”ለ”፣ የበጌምድር ጠ/ግዛትን እና የትግራይን ጠ/ግዛት የወሰን ክልል ደግሞ በ “ሐ” ና “መ” ላይ በማነጻጸር እንመልከት።

(ስእሎቹን ከታች ይመልከቱ )

Hand Draw - Ethiopa Map 1Hand Draw - Ethiopa Map 2Hand Draw - Ethiopa Map 3Hand Draw - Ethiopa Map 4

“ሀ” በሚለው የኢትዮጵያ ካርታ በኢትዮጵያ የነገሡ ነገሥታትና ህዝብ ያመኑበት፣ እንዲሁም በተባበሩት መንግሥታትና በአፍሪካአንድነት ድርጅት ተቀባይነት ያለው የኢትዮጵያ ግዛት መልክአ ምድር ካርታ ነው። በኢትዮጵያ በቅደም ተከተል የመጡ መሪዎች እስከ ደርግ ዘመን መንግሥት ይህንኑ ተቀብለውና አምነው ኢትዮጵያና ህዝቧ አንድነቱን ጠብቆ የሃገሪቷን ዳር ድንበር በመጠበቅ ኢትዮጵያን የመሩበት ረጅም ዘመናት ያስቆጠረ ካርታ ነው። በዚህ መሰረት የኢትዮጵያ ህዝብ የጠቃላይ ግዛቶች የወሰን ድንበር ሳይካልለው ኢትዮጵያዊ ዜጋ ሁሉ በፈለገውና በመረጠው ጠ/ግዛት ሄዶ በመንግሥት ሥራ፣ በእርሻ፣ በንግድ፣ በአንጥረኛነት፣ በሸማኔነት ወዘተ በመሥራትና የሃገሪቱን ሕገመንግሥት በመከተል ትዳር መስርቶ፣ ኢትዮጵያዊነትን ከደመ ስጋው ቀላቅሎና ኮርቶ የሚኖር ህዝብ ነው። ኢትዮጵያ በልጆቿ ተከብራ ለዘመናት የቆየች ሃገር ናት። ሁሉም ኢትዮጵያዊ የሚኮራባት ሃገርም ነበረች። ዛሬስ? የሚለውን ጥያቄ እንደሚከተለው እንመለከተዋለን። ታሪካዊው የጠ/ግዛቶች የንድንበር ክልል የኢትዮጵያ ጠ/ግዛቶች ድንበር በ “ሀ” ላይ ያለውን የኢትዮጵያ ካርታን ብንመለከተው በቂ ግንዛቤ ይሰጠናል። ይህ ደግሞ ለዘመናት ጸንቶ የቆየ ነው። ለዚህም ነው ከኢትዮጵያ ታሪክ ጋር የተቆራኘው። የበጌምድር ጠ/ግዛትና የወሎ ጠ/ግዛትን ስንመለከት የበጌምድር ጠ/ግዛትና የትግራይ ጠ/ግዛት ድንበርን ያካለለው ታሪካዊው የተከዜ ወንዝ ነው። ተከዜ ወንዝ በምእራብ በኩል በጌምድርን፣ በምስራቅ በኩል ትግራይን ለይቶ በማካለል ለብዙ ዘመናት ጸንቶ የቆየና የኢትዮጵያ ነገሥታትም ያመኑበት ድንበር ነው። ወልቃይት፣ ፀገዴ፣ ፀለምት፣ ቃፍታ፣ ሁመራ በሰሜን በጌምድር (ጎንደር) ስለሚገኙም ሰሜን በጌምደር (ጎንደር) ተብለው ይጠራሉ። ይህ ደግሞ በተልያዩ የታሪክ መጽሐፍት የሚገኝ እውነት ነው። የኢትዮጵያ ግዛቶች በወሰን ክልላቸው የሚታወቁት ከጥንት ተያይዞ የመጣ በመሆኑ በትግራይና በጌምድር፣ በትግራይና በወሎ እስከ ደርግ ዘመነ መንግሥት ድረስ ያስነሳው ግጭትም ሆነ ይገባኛል የሚል ጥያቄ ተንስቶም አያውቅም፣ አይታሰብብምም። የትግራይ ህዝብ ሰሜን በጌምድር የትግራይ ነው አላለም። ይህንን ተስፋፊነት የፈጠረው የተሓህት አመራር ነው።ይህ በህ.ወ.ሓ.ት የተፈፀው ሰባአዊ መብት ረገጣም በከፍተኛ የወንጀል ተጠያዊው ወያኔ ነው።ሰሜን ጎንደር ‹፣አማራ ነው ግዛቱም የጎንደር ነው። በኢትዮጵያ ታሪክም የሚታወቀው ወልቃይት..ፀገዴ..ፀለምት..ሁመራ..ወ፣ዘ፣ተ.የጎንደር ግዛቶች መሆናቸው ነው። የድንበርን ቋንቋ በተመለከተ በዚህ ዓለም በድንበር የሚገናኙ የተለያዩ ሃገራት አንዱ የአንዱን ቋንቋ ይናገራሉ። ለምሳሌ፤ ቤልጂየምን ብንመለከት፣ ፈረንሳይና፣ደች፣ ጀርመንኛ የሚናገሩ ሕዝቦ አሏት። ነገር ግን የቤልጂየም ዜጎች እንጂ ቋንቋውን በመናገራቸው የፈረንሳይ፣ ጀርመን ወይም የኔዘርላንድ ዜጎች አይደሉም። በኢትዮጵያ ውስጥም በድንበር የሚዋሰኑ ጠቅላይ ግዛቶች፣ አፋሩ ትግርኛና አማርኛ ይናገራል፤ ትግራይም አማርኛና ትግርኛ ይናገራል፤ አማራውም ኦሮምኛና ትግርኛ፣ አርጎብኛ፣ ጉራጌኛ ይናገራል። በቋንቋ ድንበርን ለመወሰን ፈጽሞ አይቻልም። ተስፋፊው ተሓህት/ህወሓት ግን የታላቋን የትግራይ ሪፓብሊክ ለመፍጠር፣ የበጌምድር ጠ/ግዛትን እና የወሎ ጠ/ግዛትን ለም መሬቶች ትግርኛ ይናገራሉ በሚል ቁንጽል አስተሳሰብ በጉልበቱ መሬት ነጥቋል። የሰሜን በጌምድር፣ ወልቃይት፤ ፀገዴ፣ ፀለምት፣ ሁመራ፣ ባህላቸውና ቋንቋቸው አማራ ነው። ይህም ለብዙ ዘመናት እየዳበረ የመጣ ሲሆን፣ በተከዜ ወንዝ ዳር የሚኖሩ ዜጎች ትግርኛ መናገር ቢችሉም ዋናው ቋንቋቸው አማርኛ ነው። ሙሉው የዘር ሃረጋቸውም አማራ ነው። ስለሆነም እነዚህ ዜጎች የአማራ ሕብረተሰብ አካል ናቸው። ከትግራይ ሕብረተሰብ ጋር የሚያገናኛቸው ኢትዮጵያዊነታቸው ነው። በጋብቻ በመተሳሰር በሰላምና በፍቅር የኖሩ፣ በኢትዮጵያዊነታቸው የሚኮሩ ህዝብ ናቸው። በዚህም ምክንያት የትግራይ ህዝብም በበጌምድርና በወሎ ህወሓት የፈጸመውን ተስፋፊነት አልተቀበሉትም። በእነዚህ ሶስት ጠ/ግዛቶች፣ ማለትም በጌምድር፣ ትግራይና ወሎ የመሬት ይገባኛል የድንበር ክልል ተነስቶ አያውቅም። የሚነሳበት ምክንያትም የለም። የሕግ መሰረት እነዚህ ከበጌምድር ጠ/ግዛት በተሓህት/ህወሓት የተነጠቁት መሬቶች፣ ወልቃይት፣ ፀገዴ፣ ፀለምት፣ ቃፍታ፣ ሁመራ፣ ከወሎ ጠ/ግዛት ደግሞ ደቡብ ወሎ የተነጠቁት ቦታዎች ሕገወጥ ናቸው። ተስፋፊው ተሓህት በፕሮግራሙ መቅድም በሚለው አርእስት ያካተተው የትግራይ ቦታዎች ናቸው የሚለው የትግራይ ህዝብ ከመጀመሪያው፣ ከ1969 ጀምሮ በቁርጠኝነት የተቃወመው ነው። እኛን ከህዝቡ በመነጠል ችግር እንዲፈጠር አታድርጉ፤ የምትሉት መሬት በታሪክም የትግራይ አልነበረም ባለበት ጊዜ ነበር “ትግራዋይ ሸዋዊ” የሚል ስም የሰጡት። ህዝብ ያልተቀበለው ተስፋፊነት ደግሞ አምባገነን እና ፋሽስትነት ነው። ስለሆነም በሕግ ተቀባይነት የለውም።ተሓህት/ህወሓት በጉልበት የነጠቃቸው መሬቶች ካለምንም ውጣ ውረድ ወደ ቀድሞ ይዞታቸው ይመለሳሉ። ህዝብ በጠራራ ጸሓይ መሬቱ አይነጠቅም አይፈናቀልም ።በህዝብ ሬፈሬንደም ይወሰናሉ፣ ለምን? በካርታ “ሀ” ላይ የተመለከተውን ታሪካዊ የሚያደርገው፣ በኢትዮጵያ የነገሡ ነገሥታት ተቀብለውት የጸና ሆኖ ብዙ ዘመናት ያስቆጠረ ስለሆነ ነው። የኢትዮጵያ ህዝብ አምኖበት የተቀበለው፣ በምንም መልኩ የድንበር ግጭትና ኹከት ያልፈጠረ፣ ዜጎች
ሁሉ አምነውበትና ኮርተውበት ኢትዮጵያውያዊነታቸውን አጠናክሮና አቅፎ የተጓዘም ስለሆነም ነው።
አንዳንድ የተሓህት/ሀውሓት አመራርና ነባር አባላቱ የድንበሩ ጉዳይ በህዝበ ወሳኔ ይፈታ የሚሉ አሉ። ይህ በተሓህት/ህወሓት የተፈጸመው የመስፋፋት ጉዳይ ሕገወጥ ነው። የሰሜን በጌምድር መሬት፣ የደቡብ ወሎ መሬት ለድርድር ሳይቀርቡ በቀጥታ ወደ ቀድሞ ግዛታቸው ይመለሳሉ። ለህዝበ ውሳኔ ይቅረብ ማለት ፌዝና ቀልድም ጭምር ነው። ስለሆነም ህዝበ ውሳኔ ሕገወጥ ነው። ፀገዴ፣ ወልቃይት፣ ፀለምት፣ ሁመራ የበጌምድር (የጎንደር) ግዛት ናቸው። በወሎም፣ ወልዲያ፣ አፍላ ደራ፣ ራያና ቆቦ፣ አላማጣ የወሎ ጠ/ግዛት ናቸው። የወያኔ ህወሓት አመረራርና አባላቱም ጭምር ይህንን አምነው መቀበል ግዴታቸው ነው። የደረሰው የዘር ማጥፋት ወንጄል ተሓህት/ህወሓት ሲፈጠር ተስፋፊነትን የፖሊሲው አቋም አድርጎ የተነሳ ድረጅት ነው። 5ኛ ፕሮግራሙን እንመልከት።

ተስፋፊነት ደግሞ ፋሽስት፣ አምባገነን፣ ጨካኝ፣ ምህረት የለሽ ነው። ተፈጥሯዊው ባህሪውም ስለሆነ በዚሁ ነው የሚያድገው። ተሓህት/ህወሓት ታህሳስ 1972 በቀጥታ የዘመተው ወደ ሰሜን በጌምድር ነበር። ዘመቻው ሰላማዊ ኢትዮጵያውያን የአማራ ዜጎችን ለማጥፋት የወጣ እቅድ ነው። በትግራይ ውስጥም አማራ ደመኛ ጠላትህ ነው ሲሉት፣ አማራ ለትግራይ ጠላት አይደለም፣ ወንድማችን ነው፣ በጋብቻና በዘር ደማችን የተቀላቀለ ኢትዮጵያዊ ነን በማለት በቆራጥነት አቋሙን የገለጸ ህዝብ ነው። “የትግራይ የሸዋ” በሚል ከገጠሩ ጀምሮ እሰክ ከተሞች የግድያ እልቂት የሚፈጸምበት ጊዜም ነበር። የትግራይ ህዝብ አማራ ወንድሜ፣ እህቴ፣ ልጆቹ ልጆቼ፣ ሁላችንም የአንዲት ኢትዮጵያ ልጆች ነን በማለቱ በስንት ሺህ የሚቆጠር ህዝብ በህወሓት 06 ሓለዋ ወያነ እየገባ በጥይት ተደብድቦ ከባድ መስዋእትነት የከፈለ የአማራው አጋር ኢትዮጵያዊ ነው። ወያኔ ህወሓት ወደ ሰሜን በጌምድር ሲዘምት ዋናው አስተባባሪ ሆኖ እልቂቱ እንዲፈጸም ያስተባበረው የድርጅቱ ሊቀመንበር ስብሃት ነጋ ነበር። ከስብሃት ነጋ ጋር በመተባባር በተግባር የዘር እልቂት እንዲፈጽሙ የተመደቡት የማእከላዊ ኮሚቴ አባላት ደግሞ፣ አርከበ እቁባይ፣ ስዩም መስፈን፣ ዘርአይ አስገዶም፣ ስየ አብርሃ ናቸው። በእልቂቱ የታሰተፉ ተዋጊ ሃይሎች የተመሩት ደግሞ፣ በሳሞራ የኑስ፣ ተከስተ እስጢፋኖስ፣ ታደሰ ወረደ፣ መኮንን አሊሱም ሲሆኑ፤ ክርቢት ተብለው የሚታወቁት ሽብርተኛ ጋንታ የተመሩት ደግሞ፤ በሻሸይ በላይ፣ አሰፋ ማሞ፣ ጸጋይ ቆማጥ፣ መሃሪ፣ ዳሳ ጉግሳ ነበሩ። አምስተኛ ክርቢት ደግሞየተመራው በአርከበ እቁባይ ሲሆን፣ ስምሪታቸው በፀገዴ፣ ወልቃይት፣ ፀለምት ነበር። እዚህ የሚኖረው ህዝብ በኢትዮጵያዊነቱ የሚያምን ነው። እኛ በታሪክ ሲወርድ ሲዋረድ የመጣን አማሮች ነን በማለታቸው፣ በቀንና በሌሊት እሳተ ነበልባል ወረደባቸው። በስብሃት ነጋ በሚመራው የህወሓት ሰራዊት ከያሉበት እየተለቀሙ በጥይት እየተደበደቡ አለቁ። ሃብት ንብረታቸው፣ እንቁላል፣ ዶሮ፣ የጋማ ከብት፣ ያፈሩት ንብረት ሁሉ በህወሓት እየተዘረፈ ወደ ትግራይ እየመጣ የሰራዊቱ ቀለብ ሆነ። ቤት ፈረሰ፣ ወላጆች፣ ህፃናትን ጨመሮ በህወሓት አለቁ። ቤተሰቦች እየተሰበሰቡ እቤት ወስጥ እየታጎሩ አርከበ እቁባይ በሚመራው ክርቢት እሳት እየተለቀቀባቸው በእሳት አጋይተው ጨረሷቸው።
በሌላ በኩል ደግሞ፤ በብስራት አማረ የሚመርው ጨካኝና አረመኔ ሰራዊት፣ የቡድኑ አባላት፤ አሰፋ ጉሬዛ፣ ሃይሉ በርሄ፣ ልኡል በርሄ፣ ዘርአይ ይህደጎ፣ ካህሳይ ቆራጽ፣ ዘውዱ፣ ገብረዮሃን ለህወሓት የስለላ ሥራ ወልቃይት ፀገዴ ተሰማርተው ነበር። በፀለምት በኩል ደግሞ በዘአማኑኤል ለገሰ የሚመራና ተጠሪነቱ ለብስራት አማረ የሆነ ቡድን ተሰማርቶ ነበር። የቡድኑ አባላት፣ አደም፣ ታደሰ 06፣ ታደስ መሰረት፣ ተስፋየ አፅብሃ (አፍርሰው)፣ መሃመድ፣ ፍሬ ጎይትኦም (ሴት) ነበሩ። ይህ በዚህ እንዳለ፣ ሃለዋ ወያኔ እያስገቡ መግደል ስለሚመቻቸው፣ ለወልቃይት ፀገዴ፣ ፀለምት አመቺ የሆኑ ሃለዋ ወያኔ ተከፈቱ። እነሱም፣
1. ፍየል ውሃ ፀገዴ፣ በክንፈ ገ/መድህን የሚመራ፣
2. ባኽላ ሳሞረ፣ የፀገዴ ዳር፣ በሙሉጌታ ወዛም (ማይዶ አስክን) ዛሬ በአሜሪካ የሚኖር፣
3. ሱር ለፀለምት አቅራቢያ፣ በአበበ ተክላሃይማኖት የሚመራ (የአየር ሃይል አዛዥ ጄነራል ነበር)
የወልቃይት ፀገዴ ፀለምት ህዝብ በነብስራት፣ አማራው በቀንና በሌሊት እየታፈነ በሶስቱ ሃለዋ ወያኔ እየገባ በአማራው የሰሜን
በጌምድር ህዝብ የዘር ማጥፋት ወንጄል ህወሓት በመፈጸም ላይ እንዳለ፣ ቦታው በመጣበቡ ምክንያት ሌላ ሃለዋ ወያነ መጀመሪያ በሃሰን ሹፋ የሚመራ ሃለዋ ወያነ የአማራው ሕይወት ተቀጠፈ፤ በጅምላ ጉድጓዶች እየገቡ በፍየል ውሃ፣ በባኸላ፣ በሱር፣ በገሃነብ፣ በህወሓት ጥይት እየተደበደበ ያለቀው ህዝብ ቤት ይቁጠረው። መሬቷና በአካባቢው ከሞት የተረፈው ምስክርነት ይሰጥበታል። ተሓህት/ህወሓት የአማራውን ህዝብ ዘር ማጥፋት የጀመረው ከ1969 መጀመሪያ ቢሆንም በክፉና
አሰቃቂ መልኩ የጀመረው በ1972 ታህሳስ ሲሆን ለረጅም አመታት ግድያው ቀጠለ።
ከዚህ የዘር ማጥፋት እልቂት ከደረሰበት የወልቃይት ፀጋዴ ፀለምት ህዝብ አሁን በእድል ከሞት ተርፎ ቤተሰቦቹ ያለቁበት ዜጋ፣ በዛን ጊዜ የህወሓት አመራር ጠላቶቼ እነማን ይሆኑ? የሚል አእምሮውን የሚረብሹ ጥያቄዎች አሉ። ስለሆነም እዚያ የነበሩ የተሓህት/ህወሓት መሪዎች እነሆ ተቀበሉ። ጊዜውም ከ1967 እሰከ 1977 ነበር።
1. ስበሃት ነጋ፣ የህወሓት ሊቀመንበር ፖሊት ቢሮ
2. አረጋዊ በርሄ፣ ወታደራዊ አዛዥ ፖሊት ቢሮ
3. ግደይ ዘርአፅዮን፣ የህወሓት ም/ሊቀመንበር ፖሊት ቢሮ፣ ፕሮግራሙን ያልጠበቀ
4. አባይ ፀሃየ፣ ፖለቲክዊ ጽ/ቤት ፖሊት ቢሮ
5. ሥዩም መስፈን፣ የውጭ ጉዳይ ሃላፊ ፖሊት ቢሮ
6. መለስ ዜናዊ፣ የፖለቲካ አዘጋጅ ማ/ኮ
7. አውአሎም ወበዱ፣ የሪጅን 1-2 ሃላፊ ማ/ኮ
8. አርከበ እቁባይ፣ ወታደራዊ ማ/ኮ
9. ስየ አብርሃ፣ ወታደራዊ ማ/ኮ
10. ዘርአይ አስገዶም፣ ከተማ ግንኙነት ማ/ኮ
11. ተወልደ ወ/ማርያም፣ የገጠር ግንኙነት ማ/ኮ በህመም ምክንያት ሱዳን የሄደ
12. ገብሩ አስራት፣ የሪጅን 3 ሃላፊ ማ/ኮ
13. አስፍሃ ሃጎስ፣ የውጭ ጉዳይ ማ/ኮ
14. አታክልት ቀፀላ፣ በአመራሩ የተገደለ ማ/ኮ፣ በ1971 የተገደለ
15. ጻድቃን ግ/ተንሳይ፣ ወታደር ማ/ኮ

ከዚህ የዘር ማጥፋት ወንጄል፣ የአማርኛ ቁንቋ የአማራው ገዢ መደብ ቋንቋ ስለሆነ አብሮ መጥፋት አለበት ተብሎም ከዘመቻው አንዱ ሆነ። ከዚህ በተጨማሪ፣ ክርስትና ሃይማኖት ተከታይ በመሆኑ ኢትዮጵያዊነት የሚለው ስር የሰደደ እምነት አብሮ ይጠፋል ሲሉ ነበር። የህወሓት ፋሽስት ቡድን ኢትዮጵያን እንደተቆጣጠረ ከዚህ ቀጥዬ የማቀርበው፣ እኔ የዚህ ጽሑፍ አዘጋጅ በወቅቱ የነበርኩት አዲስ አበባ ውስጥ ነበር። እነሱ ኢትዮጵያን ወረው ሲቆጣጠሩ ደግሞ ዩጋንዳ፣ ካምፓላ ስለነበርኩ የማቀርበው ሃተታ በትግሉ ወቅት ጓዳኛዬ የነበረ፣ በ1968 በተሓህት አበርን የተሰለፍን ግለሰብ የነገረኝን ነው። ገና ከመነሻው ጀምሮ የጋንታ መሪ፣ የሃይል መሪ፣ የባታልዮን መሪ፣ የብርጌድ መሪ፣ የክፍለ ጦር መሪ፣ እየሆነ የመጣ በትግሉ ታዋቂ የነበረ ታጋይ ነበር። ኢትዮጵያን እነደተቆጣጠሩ፣ የሽግግር መንግሥት ተብሎ ሲቋቋም በጸረ- መለስ ዜናዊና ስብሃት ነጋ ተፈርጄ ህዳር 1984 ተባረርኩ ያለኝ የህወሓት ታጋይ የነበረ ነው። ይህ ግለሰብ ከህወሓት ሰራዊት ብቻውን ሳይሆን በርካቶች መባረራቸውን ነግሮኛል። አሁን የምተዳደረው በግሌ በአነስተኛ ንግድ ነውም ብሎኛል። የተገናኘነው ዩጋንዳ፣ ካምፓላ ለግል ሥራ በመጣ ጊዜ ነበር። ወሩና ዓ. ምን ጭምር እቤቴ እንደገባሁ በማስታወሻ ይዤው ነበር። ህወሓት በኔ ላይ በዙ ችግሮች እየፈጠረብኝ የነበረበት ጊዜ ስለነበር፣ እንኳን ለማነጋገር ለመቆም እንኳን አእምሮዬ ሊቀበልልኝ አልቻለም። እሱም እንደተጠራጠርኩት ስላወቀ፣ እኔን አትጠራጠረኝ፣ በኔ ላይ የፈጸሙብኝን ብነግረህ ታለቅሳልህ ሲለኝ በመጠኑም ቢሆን ተቀበልኩት። የተገናኘነው ሚያዚያ 1985 ነበር። ኢትዮጵያን ለመቆጣጠር ምንም ችግር ሳይገጥመን ካለ ምንም ጦርነት ከትግራይ በመኪና ተጭነን አዲስ አበባ መጥተን ነበር። ሃገሪቷ በእጃችን በወደቀችበት ጊዜበየመንገዱና በየቦታው የሃገሪቷን ሃብትና ንበረት ዘርፈናል። ደርግ ዘራፊ ይመስለኝ ነበር። ነገር ግን አንዲት ብር ሳትነሳ ያገኘነው ባንክ ቤቶች፣ የመንግሥት ግምጃ ቤቶች፣ ያለውን ገንዘብ ጠራርገን ነበር የወሰድነው። አዲስ አበባ ስንገባ ሁለት ክፍለ ጦሮች ባንክና ማንኛውንም የገንዘብ ተቋሞች እንድንጠብቅ ከተመደቡት አንዱ የኔ ክ/ጦር ስለነበር፣ የህወሓት አመራር በቀንና በሌሊት ፖሊት ቢሮ አመራር የበላይ ሆነው የሚቆጣጠሩት ስብሃት ነጋና አዲስ አበባ ስንገባ ለሁለት ቀናት ለንደን የቆየው መለስ ዜናዊ ሆነው ለዘርፊያ ተሰማሩ። በዝርፊያው የተሰማሩት የፖሊት ቢሮ አባላትም፣ ጻድቃን ገብረተንሳይ፣ አርከበ እቁባይ፣ አውአሎም ወልዱ፣ ክንፈ ገብረመድህን፣ ስየ አብርሃ፣ አበበ ተ/ሃይማኖት፣ አባይ ፀሃየ፣ የማነ ኪዳነ (ጃማይካ) በዋናነት የሃገር ሃብት፣ ገንዘብ፣ ወርቅና ልዩ ልዩ ውድ ቅርሳቅርስ ዘርፈዋል። የተዘረፈው ሃብትም መለስ ዜናዊ በሚኖርበት ምኒሊክ ቤተ መንግሥት ተከመረ። እኛም ዘርፈናል በማለት የጀመረውን ጨዋታ ቀጠለ። ይህ የትግል ጓደኛዬ በአድዋ አውራጃ ቢወለድም አብዛኛው ቤተሰቦቹ ጎድንደርና አዲስ አበባ ይሚኖሩ ናቸው። የትምህርት ደረጃው ከአንደኛ ደረጃ ባይዘልም በኢትዮጵያ ላይ ጥሩ አመለካከት እንዳለው ከፊቱ ይነበባል። ከአጫወተኝ ሁሉ ትኩረት የሰጠሁት፤

1ኛ፣ የህወሓት ፖሊት ቢሮ ኢትዮጵያን እንደሚቆጣጠርና እንደሚመራ የአሜሪካና የእንግሊዝ መንግሥታት በእርግጠኝነት ሲናገሩ፣ የኢትዮጵያ ምድር ጦር፣ አየር ሃይል፣ ባህር ሃይል በቀላሉ እንደማይሸነፉ ያውቁ ስለነበር፣ ሁለቱ መንግሥታት ይጨነቁ ስለነበር፣ በርካታ የጦር መሳሪያ ለህወሓት ይሰጧቸው ነበር። 2ኛ፣ የህወሓት የትግራይ ነፃ አውጪ ድርጅት ተብሎ ኢትዮጵያን ለመምራት ስለማይችል በፍጥነት ስማቸውን እንዲለውጡ ማድረግ። በዚህ መሰረትም የህወሓት ፖሊት ቢሮ፣ መለስ ዜናዊ፣ ስብሃት ነጋ፣ አባይ ፀሃየ፣ ሥዩም መስፍን፣ ገብሩ አስራት፣ ስየአብርሃ፣ አለምሰገድ ገ/አምላክ፣ አርከበ እቁባይ፣ ጻድቃን ገ/ተንሳይ፣ አበበ ተክለሃይማኖት፣ አውአሎም ወልዱ፣ አረጋሽ አዳነ፣ ተወልደ ወ/ማርያም ህዳር 1982 መቀሌ ከተማ ተሰብስበው የሚፈለገው ስም ለማውጣት አራት ቀን ተዘግተው በጭንቀት ላይ ቆዩ። በመጨረሻም ተወልደ ወ/ማርያምና አለምሰገድ ገ/አምላክ የመጨረሻ አማራጭ በለው ያቀረቡት ስም፣ “የኢትዮጵያ ሕዝቦች አብዮታዊ ዲሞክራሲያዊ ግንባር” (ኢህአዴግ) እንዲባል ፖሊት ቢሮ ተቀብሎ አጸደቀው። እንደ ወጥ ማጣፈጫ የሚጠቀሙበት ብአዴን በግንባሩ ውስጥ ከተቀላቀለ ኢህአዴግ አስተማማኝና ተቀባይነት ያለው ስም ይሆናል ተባለ። ውሳኔውን እንግሊዝና
አሜሪካም ተቀብለውታል። ብአዴን የተጨመረው አማራ ብሄር ሆኖ፣ “ህዝቦች” የምትለው ቃል ስትሸፍን፣ ‘አብዮት’ የምትለው ቃል ደግሞ ወያኔን ትሸፍናለች። የህወሓትን የበላይነትንም ታረጋግጣለች። በሌላ መልኩ ደግሞ፣ ህዝቦች የሚለው ቃል የኢትዮጵያን ህዝብ አንድ ኢትዮጵያ ሳይሆን በዘፈቀደ የተሳባሰበ ነው ለማለትና በዘርና በቋንቋ ከፋፍለው ለመግዛት የሚጠቀሙበት፣ ለሥልጣናቸው እድሜ ማራዘሚያ የሚያደርጉበት ነው። 3ኛ፣ ህወሓት በሚከተለው ፖሊሲ መሰረት የአሰብ ወደብ የኢትዮጵያ አለ መሆኑ ሻእቢያም የኤርትራ መሬትና ወደብ አይደለም፤ የኢትዮጵያ ነው፣ በማለት ስለአረጋገጡ አሰብን ወደ ኢትዮጵያ አካለለች። እንግሊዝ ሃገር ልካችሁ ካርታችሁን አዘጋጁ የሚል ሃሳብም ቀርቦላቸዋል። ፖሊት ቢሮው በሙሉ ወደ እብደት ወሰዳቸው። አሰብ የኤርትራ እንጂ የኢትዮጵያ አይደለም፣ አሰብን አናካትትም በማለት፣ በተለይም ስብሃት ነጋ፣ መለስ ዜናዊ፣ ስየ አብርሃ፣ ስዩም መስፍን፣ ብርሃን ገ/ክርስቶስ ወዘተ በጥብቅ በማውገዛቸው የተነሳ እንግሊዝና አሜሪካም ሃሳባቸውን በመቀልበስ ኢትዮጵያን የባህር በር አልባ አደረጓት። ይህንን ሁሉ የነገረኝ ይህ የቀድሞ ጓደኛዬ በንጹህ ልቦና ቢሆንም፤ እኔ ግን የህወሓትን እርኩስ ተግባር ስለማውቀው እስክንለያይ ድረስ መጠርጠሬ ከፍተኛ ነበር። ከላይ የተጠቀሱት ነገሮች ከማንም የማላገኘው እውነታ በመሆኑ ጥሩ ግንዛቤ ስጥቶኛል። ቀደም ብዬ የማውቀው የወያኔ ህወሓት ፀረ-ሃገርና ፀረ-ህዝብ የመሆኑን እምነቴን አዳብሮልኛል። በተለይ በአማራውና በኦሮም ህዝብ ላይ የሚፈጸምውን ክፈተኛ ግፍ በጽናት አውግዞታል። ይህንን ካልኩ በኋል ወደ ወናው ሃሳቤ ስመለስ፣ ኢትዮጵያን እንደተቆጣጠረ፣ ፋሽስቱ ህወሓት ወያኔ ከሰኔ 1983 ጀምሮ ይፋ ያደረገው የኢትዮጵያ ካርታ ሃገር የሚያፈርስ፣ ህዝብ የሚበትን፣ ደመኛ ጠለትነቱን ያረጋገጠ መሆኑን ሁሉም ኢትዮጵያዊ በትክክል ያውቃል። ሆኖም፣ ሃሳቦቼን በገጽ 5 ስላስቀመጥኩት፣ በትኩረት እንመልከተው። በ “ለ” ላይ የተመለከተው የኢትዮጵያ ካርታ የተዘረዘሩት የህወሓት አመራር ያዘጋጀውና ሆን ተብሎ የተሰራና የተወጠነ ነው። ምክንያቱም፣1ኛ፣ ካርታው እንደሚያመለክተው፣ የአማራውን ነገድ በታትኖ ዘሩን ለማጥፋት፣ ሰሜን በጌምድር ፀለምት፣ ፀገዴ፣ ወልቃይት፣ ቃፍታ፣ ሁመራ፣ በቀጥታ ወደ ትግራይ ግዛት ሲካለሉ ከወሎ ደግሞ ራያና ቆቦን፣ አላማጣን፣ አፍላ ደራ፣ ወልዲያ፣ እነዚህንም ወደ ትግራይ ግዛት ተካለሉ። ህወሓት ታላቋን ትግራይ በጉልበቱ ነጥቆ ፈጠራት። ወሎ አሁንም ቀድሞ ከነበረው ግዛቷ ከግማሽ በላይ ወደ አፋር ተካለለ። የቀድሞዋ ጠ/ግዛት ወሎ አሁን የለችም። የቀድሞዋ የበጌምድር ጠ/ግዛት አሁን የለችም። ጎጃም፣ ሸዋ የሉም። መተማና ሌሎች ወረዳዎች ወደ ቤኒሻንጉል ተካለዋል። ወያኔ ህወሓት ኢትዮጵያን እንደተቆጣጠረ አማራው ተበታትኖ መኖሪያ አልባ ሆነ። ከተወለደበት፣ ካደገበት ቀዬ ተባረረ። ከርታታና ማደሪያ የሌለው ሆኖ ለረሃብ፣ ለበሽታና ለብዙ ችግር ተዳረገ። የአማራው ህዝብ የሚኖርባት ክልል ከአንድ አውራጃ ያነሰች ሆነች።
2ኛ፣ ይህ የህወሓት የካርታ ክልል ኢትዮጵያዊነንት ፍጽሞ የሚያጠፋ ነው። የኢትዮጵያ ህዝብ ግን አንድ ህዝብ ሆኖ በአንድነቱና በኢትዮጵያዊነቱ እንዳልኖረ ሁሉ፣ የህወሓት አመራር ይህን እውነታ በመጻረር ሃገርን በጎሳ፣ በቋንቋ ከፋፍለውታል። የቀድሞው የወያኔ ግፈኛው ፋሽስት መሪ የነበረው መለስ ዜናዊ በጻፈው “TPLF’s Strategies for Establishing its Hegemony and Perpetuating its Rule” በሚለው ጽሁፍ የህወሓትን ዓላማ፣ ማለትም ሁሉንም የሃገሪቷን ጉዳይ በመቆጣጠር በቀጣይነት መግዛት ነው፣ በማለት አስቀምጦታል። ይሄንን ከገቡ ለማድረስ፣ ተቃዋሚ ሃይሎችን ማጥፋት፣ ነፃ ሚዲያን በማጥፋት የህወሓት ልሳናትን ማሳደግ፣ የህወሓት ደጋፊዎችን የሥራ እድል መስጠት፣ ቁልፍ የፕሮፓጋንዳ መሥሪያ ቤቶችን፣ ማለትም፣ ትምህርት ቤቶችን፣ የሃይማኖት ተቋማትን፣ የብዙሃን መገናኛዎችን፣ ጋዜጣ፣ መጽሔት፣ ሬዲዮ፣ ቲሌቪዥን ወዘተ በመቆጣጠር የህወሓት አገልጋይ ማድረግ በማለት ጽፏል። በዋናናት ያስቀመጣቸው ደግሞ፣ ሃይማኖት ከአድሃሪው ህብረተሰብ ጋር የተቆራኙ ስለሆነ ያ መቋረጥ እንዳለበት ጽፏል። መለስ ዜናዊ አድሃሪ ህብረተሰብ የሚለው፣ ሙስሊሙን፣ ክርስቲያኑን፣ ወዘተ ነው። አስከትሎም፣ አድሃሪ፣ የለውጥና የእድገት ተቃዋሚ የሚላቸው ደግሞ መላውን ኢትዮጵያዊ ሲያንቋሽሽ ነው።
3ኛ፣ ያለፈው የአማራው ትምክህተኛ አገዛዝ ኢትዮጵያዊነት ዘልቆ የተዋሃደውና ከደመ ነፍሱ ጋር የተሳሰረ ነው። ይህንን ከህዝቡ ሰነአእምሮ ነቅለን ለመጣል፣ በዘር፣ በጎሳ፣ በቁንቋ ማደራጀትና በዚህ ዓላማ የሚመሩ ድርጅቶችን መፈጠር ይላል። እነዚህ ከላይ የተጠቀስኳቸው የህወሓት መርሆዎች ገና ትግሉ እንደተጀመረ በኢህአፓ ላይ የፈጸመውን ወንጀል ማስታወስ ይበቃል። ኢህአፓ በኢትዮጵያዊነቱ ያመነና የተደራጀ፣ ሁሉንም ኢትዮጵያዊ፣ ማለትም አፋን፣ አማራውን፣ ትግሬውን፣ ኦሮሞውን፣ ጉራጌውን፣ ኦጋዴኑን፣ ጋምቤላውን ወዘተ ያቀፈ፣ በዘር፣ በቋንቋ የማያማን ድርጅት ነበር፤ ለዚህም ነው በህወሓት የተደመሰሰው። በሃይማኖቶች ላይ እየተፈጸመ ያለው ግፍም ህወሓት ገና በትግሉ ጊዜ እስልምና እና ክርስትናን ለማጣፋት ታጥቆ የተነሳ እንደነበርና አሁንም በትገባር እያሳየው ያለ ጉድይ ነው። ህወሓት ኢትዮጵያዊነትን ለማጥፋት የተነሳውም ገና ከትግሉ መነሻ ጀምሮ ነው። እንደዋናው ዓላማው አድርጎ የተጠቀመበት ኢትዮጵያዊነትን ለማጥፋት አስቀድመን አማራውን ማጥፋት ብሎ ከ1969 መጀመሪያ ጀምሮ ነበር። አማራውን ከትግራይ ውጡ በማለት የግፍ ግድያ የተፈጸመባቸው በዚህ ምክንያት ነው። ከዚያ ጊዜ ጀምሮ ህወሓት የአማራን ዘር ማጥፋቱን ቀጠለበት፣ አሁንም አላቋረጠም። የካርታው ዓላማ ህወሓት በዘር፣ በጎሳና በቋንቋ የከፋፈለው፣ የህወሓት መሪዎችን የግዛት እድሜአቸውን ለማራዘም ነው። በተጨማሪም በኢትዮጵያ ውስጥ የመግባቢያ ቋንቋ እንዳይኖር ለማድረግ ነው። በኢትዮጵያ ውስጥ አማርኛ የህዝብ መግባቢያ ቋንቋ በመሆኑ ይህንን በማጥፋት ኢትዮፕያዊነቱን እና አንድነቱን ለማጥፋት የሸረበው ተንኮል ነው። አዲሱን ትውልድ በጥቅማ ጥቅም በመያዝ ሊያዘናጋ ቢሞክርም፣ ዛሬ የኢትዮጵያ ህዝብ ከዱሮው በበለጠ አማርኛ ቋንቋን በንግግርና በሥነጽሑፍ አስፋፍቶ በኢትዮጵያ ውስጥና ውጩንም ጨምሮ ኢትዮጵያዊነቱን በማጠናከርና በማቀፍ በበለጠ እድገት እየተራመደ ነው። የወያኔ ህወሓት መሪዎች እቅድ ከሽፎ የኢትዮጵያ ህዝብ ይበልጥ ኢትዮጵያዊንቱን በማጠናከር ተከፋፍለን አንገዛም በማለት ሁሉም በሃይማኖቱ፣ ሙስሊሙ፣ ካቶሊኩ፣ ፕሮቴስታንቱ፣ ኦርቶዶክሱ አንድነት ፈጥረው የህወሓት ፋሽስቱን መሪዎች መፈናፈኛ ያሳጣቸው ጊዜ አድርገውታል። ከዚህም የተነሳ የመለስ ዜናዊ ጽሑፍ ውድቅ ሆኖ ቀረ። (ይህንን የመልስ ዜናዊን ጽሑፍ ያገኘሁት፣ Solidarity Movement for a New Ethiopia (SMNE) ድረገጽ ሲሆን፣ ሁሉም ኢትዮጵያዊ ቢያነበው የህወሓት ወያኔን ዓላማ ለማወቅ ያስችለዋል። አርእስቱ፣ “TPLF’s Strategies for Establishing its Hegemony and Perpetuating ኢts Rule” ነው።

በህወሓት አመራ የተፈጸመ የዘር ማጣፋት ወንጄል
ወደ ዘር ማጥፋት ከማቅናታችን በፊት ህወሓት ማን ነው የሚለውን በአጭሩ እንመልከት፤
1ኛ፣ ተሓህት/ህወሓት ከመጀመሪያ ጀምፎ ቅጥረኛ ነፈሰ ገዳይ ሆኖ የተፈጠረ፣ የባእዳንን ተልእኮ ለማስፈጸም የተደራጀ ድርጅት ነው። ጥቁር የአፍሪካ ናዚ።
2ኛ፣ ተሓህት/ህወሓት ተስፋፊ ድርጅት ነው። ታላቋን የትግራይ መንግሥት ለመመስረት ከበጌምድር ጠ/ግዛትና ከወሎ ጠ/ግዛት በህገወጥ መንገድ የነጠቀውን ቦታዎች እንመልከት፣
3ኛ፣ ተሓህት/ህወሓት ጠባብ፣ ዘረኛ፣ ፀረ-የኢትዮጵያ ሉአላዊነትና ፀረ-የኢትዮጵያ ህዝብ የሆነና በባእዳን የተፈጠረ ድረጅት ነው፣
4ኛ፣ ተሓህት/ህወሓት ሽበርተኛ ድርጅት ነው። ከ1969 ጀምሮ በጠራራ ፀሃይና በሌሊት ፈዳያን ብሎ ባሰለጥገናቸውና በብስራት አማረ በመመራት ህዝብ ፈጁ
5ኛ፣ ተሓህት/ህወሓት ፀረ-ዲሞክራሲ፣ ጸረ-ሃይማኖት፣ ፀረ-ሕዝብ ሆኖ የተፈጠረ ድረጅት ነው። ይህ የማፊያ ድረጅት ኢትዮጵያን ለ24 ዓመታት እየገዛ ያለ ድርጅት ነው።
6ኛ፣ ተሓህት/ህወሓት የሰው ሃብት ቀማኛና የሃገር ታሪካዊ ቅርሶችን፣ የሃገር ሃብትን ዘራፊ ድርጅት ነው። ከዚህም አልፎ፣ ህዝብ እያፈናቀለ ኢትዮጵያን ለባለሃብት ባእዳን ሃገሮች በመሸጥ የተሰማራ ድርጅት ነው። ይህ የባእዳን ቅጥረኛ ደርጅት ብዙ የከፋ ባህሪ ያለው ድርጅት ነው። ኢትዮጵያ ለዘመናት ብዙ ነገሥታትን ያሳለፈች፣ ዝነኛና ባለታሪክ ሃገር ናት። እንደ ወያኔ ህወሓት የመሰለ በታሪኳ አጋጥሟት አያውቅም። በ845 በዮዲት ጉዲት፣ በ15ኛው ክፍለ ዘመን በግራኝ መሃመድ አጥፊ ወራሪ ቢገጥማትም፤ ህወሓትን የመሰለ አረመኔና ፋሽስት፣ ኢትዮጵያን እና ህዝቧን ለማጥፋት የተሰማራ፣ ተወዳዳሪ የሌለው እኩይ ድርጅት ህወሓት ብቻ ነው። የህወሓት የዘር ማጥፋት ዓላማና ተግባር ህወሓት በአማራው ላይ የዘር ማጥፋት ወንጄልን ስራዬ ብሎ የተያያዘው ከ1969 ጀምሮ ነው። በትግራይ ሰላማዊ ዜጎችና ታጋዮችንም በተመሳሳይ ሁኔታ ጎን ለጎን ማካሄዱን ቀጠለበት። ማሰቃየትና መግደል የተጀመረው በዚሁ ወቅት ነበር። ህወሓት በአሁኑ ወቅት ከሚጠቀምባቸው

የዘር ማጣፍት ወንጄሎች መካከል ጥቂቶቹን እንመልከት፤
1ኛ፣ በየክልሉ በወያኔ ሰራዊትና ካድሬዎች ዜጎችን በግልጽ በመትረየስና በነብስ ወከፍ ጠመንጃ መጨፍጨፍ፣
2ኛ፣ ቤት ውስጥ አሰባስቦ በሩን በመዝጋት በእሳት ማጋየት፣
3ኛ፣ አፍኖ በመሰወር፣
4ኛ፣ ብርሃን እና ነፋስ በማይገባበት የጉድጓድ እስር ቤቶች ወስጥ በማጎርና በማጨናነቅ በተላላፊ በሽታ እንዲያልቁ ማድረግ። ዓይነ ስውር እንዲሆኑና አእምሮአቸውን በመሳት እንዲያብዱ ማድረግ፣
5ኛ፣ ኦሮሞ፣ አማራ ወዘተ በመሆኑ ብቻ ያለምንም ፍርድ ወህኒ ቤት ተሰቃይቶ እንዲሞት ማድረግ፣ ከዘመድ አዝማድ በማራቅ በሌላ ክልል ወስዶ ማሰር፣
6ኛ፣ በዘጠኙ ክልሎች በወያኔ የተቋቋሙት እስር ቤቶች ውስጥ ያሉ ታሳሪዎች ሲታመሙ ህክምና ማግኘት ስለማይፈቀድላቸው፣ ብዙ ታሳሪዎች በዚህ ምክንያት በበሽታ እንዲያልቁ ማድረግ፣
7ኛ፣ በፈዋሽ መድሃኒት ስም ጽንስ የሚያሰውርድና የሚያመክን መድሃኒት በመስጠት ዘር ማጥፋት፣
8ኛ፣ የህወሓት መሪዎች እንደትልቅ ፖሊሲ አድርገው የያዙት ድርጊት፣ ወጣት ሴቶችና ወንዶች ሃገር ጥለው እንዲሰደዱ በማድረግ ሃገሪቱን የወደፊት ተረካቢ በማሳጣት የሥልጣን ጊዜአቸው እንዲራዘም ማድረግ፣
9ኛ፣ መሬት ነጠቃ፣ ህወሓት (ወያነ) ስልጣን ከያዘበት ጊዜ ጀምሮ፣ በእድገትና ሰላም ስም ሕዝቡን በግዴታ ከተወለደበትና ከሚኖርበት ቀየው እያፈናቀለ ለባእድ ሃገሮች ለምና ሰፋፊ መሬቶችን በርካሽ በሊዝ በመስጠት ኗሪውን
ህዝብ፣ ለረሃብ፣ ለችግርና ለስደት መዳረግ። ይህ ግፈኛና ፋሽስት መንግሥት በኢትዮጵያ ህዝብ ላይ የፈጸመውና በመፈጸም ላይ የሚገኘው ግፍ ተቆጥሮ የሚያልቅ አይደለም።

የኦሮሞ ህዝብ በፋሸስቱ ገዢ ህወሓት የደረሰበት ግፍና ሰቆቃ
የኦሮም ህዝብ ትልቁ የኢርዮጵያ ነገድ ነው። የኦሮሞ ህዝብ በኢትዮጵያዊነቱ በሙሉ ልቡ የሚያምን እና የሚኮራ ዜጋ ነው። እናት ሃገሩን ኢትዮጵያን ከተለያዩ የጠላት ወራሪዎች በመከላከል ለብዙ ዘመናት ከኢትዮጵያዊ ወገኖቹ ጋር በመሰለፍ ደሙን ያፈሰሰና አጥንቱን የከሰከሰ ጀግና ህዝብ ነው። የኦሮሞ ህዝብ የኢትዮጵያን ሉአላዊነት ጠብቆ ለትውልድ ያስተለለፈ ህዝብ ነው። ልጆቹም በኢትዮጵያ በተለያዩ ወታደራዊ ክፍሎች ውስጥ፣ በውጭ ሃገር ከፍተኛ ትምህርት ተምረው፣ በአየር ሃይል፣ በምድር ጦር፣ በባህር ሃይል፣ በፖሊስ ወስጥ ተሰማርተው ሃገራቸውን ያገለገሉና የወገን ኩራትና አለኝታ የሆኑ ናቸው። ለአብነት ጥቂቶቹን ብንጠቅስ፣ ጄነራል ጃገማ ኬሎ፣ ጄነራል ሙሉጌታ ቡሊ፣ ጄነራል ደምሴ ቡልቶ፣ ጄነራል ዋቅጅራ ሳርዳ፣ ጄነራል ገብረክርስቶስ ቡሊ፣ ጄነራል አስራት ብሩ፣ ጄነራል ቀልቤሳ ቤካ፣ ጄነራል አበበ ገመዳ የመሳሰሉትን ማንሳት ይበቃል። የኦሮሞ ህዝብ በተለያዩ የትመህርት መስክ ተሰማርተው በቀሰሙት እውቀትና ብቃት እናት ሃገራቸው ኢትዮጵያን ያገለገሉና በማገለጋል ላይ የሚገኙ ዜጎች ናቸው። የህወሓት መሪዎች ዛሬ የኦሮሞን ህዝብ ሽብርተኛ ብሎታል። ሽብርተኛው ግን ራሱ ህወሓት ነው። ህወሓት ኢትዮጵያን ወሮ ከተቆጣጠር ከ1984 መጀመሪያ አንስቶ በኦሮሞ ህዝብ ላይ ይህ ነው የማይባል በርካታ ጥቃት ፈጽሞበታል። ግድያ ፈጽሞበታል፣ ሰቆቃ በመፈጸም አፍኖ አጥፍቶታል፣ ከየሥራው አፈናቅሎታል፣ ወንድ ሴት ሳይለይ ከአንደኛ ደረጃ እስከ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የሚማሩትን ወጣት ተማሪዎች ከትምህርት ገበታቸው አባርሯል፣ በወታደርነት፣ በፖሊስ ወዘተ ተሰማርተው የሚያገለግሉትን የኦሮሞ ተወላጆች ከሥራ በማባረር ለችግር ዳርጓቸዋል፣ ከመሬቱ ተፈናቅሎ መሬቱን በእድገትና በልማት ስም ለውጭ ባእዳን አገሮች ሸጦበታል። ኢትዮጵያዊው የኦሮሞ ህዝብ አሁንም በህወሓት እየተሰቃየና እየተገደለ ነው። ህወሓት የኦሮሞ ህዝብ በሙሉ የኦነግ ደጋፊና አፍቃሪ ነው በማለት በተለያዩ ቦታዎች በሺህ የሚቆጠሩ የኦሮሞና የሌሎች ነገድ ሰዎች የወያኔን እስር ቤቶች አጨናንቀውታል። እንዲሁም ማንም በማያውቃቸው ድብቅ ወህኒ ቤቶች፣ ማለትም፣ ገሃንነብ (ቃሌማ)፣ ፍየል ውሃ የመሳሰሉ፣ በወልቃይት ፀገዴ የሚገኙና ከመሬት በታች ሁለት ሜትር ጥልቀት ባላቸው እስር ቤቶች በማጎር ያሰቃያቸዋል። በአጠቃላይ እስር ቤቶች በሞላ በኦሮሞ ተናጋሪ ኢትዮጵያውያን ተጣበዋል። በወህኒ ቤቶች ካለፍርድና ፍትህ የሚማቅቀው የኦሮሞ ህዝብ ቁጥሩ ለማወቅ አስቸጋሪ ቢሆንም፣ እስር ቤት ያልገባውም ኦሮሞም የህወሓት እስራኛ ነው። አማራው ወያኔ ተሓህት/ህወሓት ሲፈጠር ጀምሮ ኢትዮጵያዊውን የአማራ ህዝብ ለማጥፋት ያቀደ ነው። ይህንንም በፕሮግራሙ ላይ በግልጽ አስቀምጦታል። ተሓህት/ህወሓት ለውጭ ጠላት የሚውለውን ‘ጠላት’ የሚል ቋንቋ በአማራው ኢትዮጵያዊ ላይ መጠቀሙ የሃገርና የወገን ከሃዲዎች መሆናቸውን በግልጽ ያመለክታል። ወያኔ ተሓህት/ህወሓት አማራው ጠላቴ ነው በማለት ዘሩን ለማጥፋት የተነሳው ከ1969 ጀምሮ ሲሆን፣ አሁንም በአማራው ላይ መጠነ ሰፊ የሆነ ጥቃት እየፈጸመበት ይገኛል።
1. ተስፋፊው ህወሓት በ1967 ይዞት ወደ ደደቢት በረሃ በወረደው ፕሮግራሙ ላይ፣ ሰሜን በጌምድርን በሙሉ፣ ወልቃይት ፀገዴን፣ ሁመራን፣ ፀለምትን ወደ ትግራይ ለማቀላቀል መሬቱ ከአማራ መጽዳት አለበት በማለት በታህሳስ 1972 ገልጾታል። ቀደም ብዬ እንደገለጽኩት፣ በሰሜን በጌምድር ጾታን ሳይለይ፣ ከህጻናት እስከ ሽማግሌ ሰቆቃ ተፈጽሞባቸዋል። እቤት ወስጥ እየታጎሩ በእሳት ጋይተዋል። ወያኔ ህወሓት በተለያየ ዘዴ አማራ የተባለውን እያደነ የዘር ማጥፋት ድርጊት ፈጽሞበታል። ነፍሳቸውን ያተረፉት ለስደት ሲዳረጉ፣ የቀሩት ጥቂቶቹ ደግሞ ከቤት ንብርታቸው እንዳይፈናቀሉ በመፍራት የሚደርስባቸውን ስቃይ እየተቀበሉ እየኖሩ ነው።
2. ወያኔ ህወሓት ኢትዮጵያን ወሮ ከተቆጣጠረ ‘ለ’ ተብሎ እንደተምለከው ካርታ አይነት በማዘጋጀት ሆን ብሎ አማራውን በዘዴ ለማጥፋት ያቀደ ክልል የሚል ስምና ካርታ አዘጋጅቶ አማራውን በዚሁ አጠፋዋለሁ በማለት። ይህንንም ለማሳካት ከበጌምድር፣ ከወሎ፣ ከጎጃም ለም መሬቶችን እየመረጠ ወደ ትግራይ አካሏል። በነዚህ ለም መረቶች ላይ ሲኖር የነበረው የአማራው ህዝብ አብዛኛው ተገድሏል፤ ቀሪውም ተሰዷል። ያማራው ሕዝብ በቀጥታና ዘዴ በተላበሰ መንገድ በወያኔ ህወሓት የግፍ እልቂት ተፈጽሞበታል። አለመታደል ሆነ እንጂ አማራ እኮ የኢትዮጵያ ጋሻ መታ ነው። ከ7ኛው ክፍለ ዘመን ጀምሮ የእናት ሀገሩ ኢትዮጵያ ዳር ድንበር ከወራሪ ጠላት እየተከላከል የመጣ ባለታሪክ ህዝብ
ነው። ወደ ሌላ ሃሳብ ከመግባታችን በፊት፣ ኢትዮጵያውያን በብሄር ብሄረሰቦች በመተባበር ለረጅም ዘመናት አብሮ የኖረና በዳበረ ማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ባህላዊ ትስስር የቆየ ህዝብ ነው። አሁንም ወያኔ የሚፈልገውን መንገድ አንከተልም በማለት የተጠናከረ ህብረት ፈጥሮ በሙሉ ልቦና እና ኢትዮጵያዊነት ተሰባስበው እየተራመዱ ነው። እምቢ ለወያኔ አልገዛም እምቢ ለወያኔ የእድሜ መግዣ አልሆንም አማራ ነኝ አማራነቴም የሚነጥቀኝ ሀይል የለም ።የመብት ገዴታየም በህዝባዊ አመፅ አከብራሉ የኦሮሞ ህዝብም እንደዚሁ ፡ሌላው ኢትዮጵያዊ ህዝብም እንደዚሁ ተነስተዋ ግለቱ እየጨመረ ።የወያኔ ህ.ወ.ሓ.ት ስርአት በዚች አመት ከርሰ መቃብሩ መግባቱ እይቀሬ ነው።ህዝብ ሀያል ነው፤ህዝብ ከተነሳ የሚመልሰው ሀይል በዚች አለም የለም።የኢትዮጵያ ህዝብ አሁን የትቀጣጠለው ህዝባዊ አመፅ ሀገር አቀፍ ሆኖ ዳሩን እናድርስው ነፃነታች እናስመልስ ። ህ.ወ.ሓ.ት የመሰለ ክፉ ጠለት የለም።

ጋሜቤላ

የጋምቤላ ኢትዮጵያዊ ዜጋም ልክ በአማራውና በኦሮሞው ህዝብ ላይ የሚደርሰው ዓይነት ሰቆቃ፣ እስራት፣ ግድያ፣ አፈና በወያኔ ህወሓት እየተፈጸመበት ዘሩ እንዲጠፋ እየተደረገ ነው። በአማራው ላይ የተፈጸመው በመድሃኒት ስም በግድ ለወንዶችና ለሴቶች የሚሰጠው የማምከኛ መድሃኒትም ለጋምምቤላ ሕዝብ እየተሰጠ ዘሩ እየጠፋ ነው። በህወሓት የሚመራው ሽብርተኛ ስርዓት በጋምቤላው አኝዋክ ህዝብ ላይ በጄነራል ጸጋዬ የሚመራው 43ኛው ክፍለ ጦር በቀን ከ425 በላይ ገበሬዎችን፣ ሴቶችን እና ህጻናትን ገድሏል፣ ቤታቸው ተቃጥሏል፣ የተረፈውም ተሰዷል። ይህ ሳይበቃው፣ የህወሓት ሽበርተኛ ስርዓት የጋምቤላ ህዝብ በእርሻ ላይ ተሰማርቶ የሚኖረውን ገበሬ የሚጠቀምበትን መሬት
ለባእዳን ባለሃብቶች በመስጠት ለችግርና መከራ ዳርጓቸዋል። ዛሬ፣ የጋምቤላ ህዝብ በደረሰበት የዘር ማጥፋት ምክንያት ህልውናው የተመናመነ ሆኗል።

ኦጋዴን

ወያኔው የህወሃት ፋሽስት መሪዎች በኦጋዴን ህዝብ ላይም ሰፊ የዘር ማጥፋት ወንጄል ፈጽመዋል። ይህ ኢትዮጵያዊው ህዝብ የኦነግ አባል ነህ በሚል ሰንካላ ምክንያት በቀን እና በሌሊት እያደነ መጠን የሌለው ግድያ በመፈጸም ዘሩን አጥፍቷል። እቤት ውስጥ አሰባስቦ ቤቱን በመቆለፍ በህይወት እያሉ በላያቸው ላይ እሳት በመለኮስ በእሳት ጋይተው እንዲሞቱ አድርጓል። በሌላው ዘር ላይ እንደተፈጸመው አይነትም ከመሬታቸው እንዲፈናቀሉና እንዲሰደዱ አስገድዷቸዋል። አስገድዶ የማምከኛ መርፌና ኪኒን በመስጠት ዘሩ እንዲጠፋ አድርጓል። በየቦታው በማይታወቁና በሚታወቁ የወያኔ ህወሓት ወህኒ ቤቶች በበሽታ፣ በረሃብ ቤተሰባቸው በማያውቀበት ሁኔታ ታስሮ ዘሩ እያለቀ ነው። አፋር የአፋር ኢትዮጵያዊው ዜጋም ከላይ በተጠቀሰው ዓይነት በህወሓት የዘር ማጥፋት ደርሶባታል። ከመሬቱ ተፈናቅሎ በገዛ ሃገረ ሰደታኛና ባይተዋር ተደርጓል። ትግራይ የትግራይ ህዝብ ገና ወያኔ ሲፈጠር ይዞት የመጣውን ፕሮግራም አልቀበልም በማለት፣ አማራው ደመኛ ጠላትህ ነው ሲባል፣ አማራው ወንድሜና እህቴ፣ ደሜና ስጋዬ ነው፣ አማራው ለትግራይ ህዝብ ጠላት አይደለም፣ እናንተ የወያኔ መሪዎች የምታወሩትና ከወገናችን ለማቃረን የሸረባችሁት ዘዴ ነው እንጂ፣ ሁለቱ ህዝቦች ለብዙ ዘመን በፍቅር፣ በሰላም ተጋብቶና በደም ተቆራኝቶ የኖረ ህዝብ ነው። አማራ የትግራይ ህዝብ ጠላት ሳይሆን ወንድምና እህት እንዲሁም ወገንና መመኪያ ነው። ትግራይ የኢትዮጵያ አካል እንጂ ነፃ ሃገር ነበረች የምትሉትን ተረታችሁን አንቀበለውም በማለቱ ከባድ መሰዋእትነት የከፈለ፣ ወገኔን አትንኩ በማለቱ “የትግራይ ሸዋ” የተባለ ህዝብ ነው። በዚህም ምክንያት በወያኔ ተሓህት/ህወሓት ከፍተኛ ጥቃት ደርሶባታል፣ ተገድሏል፣ ንበርቱ ተወርሶ ለከፋ ችግር ተዳርጓል። በኢትዮጵያ ህዝብ ላይ ለደረሰው ለዚህ ሁሉ ጥቃት ተጠያቂዎቹ እነማን ናቸው? በኢትዮጵያ የዘር ማጥፋት ወንጄል በአማራው፣ በኦሮሞው፣ በጋምቤላው፣ በኦጋዴኑ፣ በአፋሩ፣ ወዘተ ላይ ተፈጽሟል። ከተወለደበት ካደገበት መሬት ተፈናቅሏል፤ በመድሃኒት አንዳይዋለዱና እንዳይባዙ ተደርገዋል፣ ንጹሃን ወገኖች በጅምላ ተገድለዋል፤ እንዚህ ሁሉ ከዘር ማጥፋት ድርጊት ያላነሱ ተግባሮች ናቸው። እስከ አሁን በወያኔ ህወሓት አመራር የተገደለው ኢትዮጵያዊ ቁጥር ከ9 ሚሊዮን በላይ እንደደረሰና ቁጥሩ በማደግ ላይ እንድሆነ ጥቆምዎች ያመለክታሉ። ከ34 ሚሊዮን በላይ ደግሞ ከመሬታቸውና ከትውልድ ቦታቸው ተፈናቅለው መኖሪያ አልባ በመሆን ለስደት፣ ለረሃብ፣ ለበሽታና ለሞት፣ ተዳርገዋል። ለዚህ ሁሉ ተጠያቂው ህዝባዊ ወያነ ሓርነት ትግራይ (ህወሓት) ነው። በእኩይ ታግባራቸው ታሪክ ሊረሳቸውና ሊፋረዳቸው የሚገባቸውን እንደሚከተለው አስቀምጣለሁ፤መለስ ዜናዊ፣ ቢሞትም የሰራው የወንጄል ድርጊት ተጠያቂ ያደርገዋል፣ አዜብ መስፈን፣ ስብሃት ነጋ፣ ሥዩም መስፈን፣ አባይ ፀሃየ፣ ስየ አብርሃ፣ አውአሎም ወልዱ፣ ገብሩ አስራት፣ ፃድቃን ገብረተንሳይ፣ አበበ ተ/ሃይማኖት፣ ሳሞራ የኑስ፣ ሃየሎም አርአያ፣ ብስራት አማረ፣ አርከበ እቁባይ፣ ፀጋይ በርሄ፣ ደብረጽዮን ገ/ሚካኤል፣ ቴዎድሮስ ሃጎስ፣ ቴዎድሮስ አድሃኖም፣ አባዲ ዘሞ፣ አረጋሽ አዳነ፣ ተወልደ ወ/ማርያን፣ ጌታቸው አሰፋ፣ ክንፈ ገብረመድህን፣ ገብረአብ ባርኖባስ፣ ዘርአይ አስገዶም፣ የማነ ኪዳነ ጃማይካ፣ ብርሃን ገብረክርስቶስ፣ ሙሉጌታ አለምሰገድ፣ ቢተው በላይ፣ አባይ ወልዱ፣ በየነ ምክሩ፣ አዲስዓለም ባሌማ፣ ኢሳያስ ወ/ጊዮርጊስ፣ ታደሰ መሰረት በዋናነት ተጠያቂዎች ናቸው። በተገኘው አጋጣሚ ሁሉ በነዚህ ግለሰቦች ላይ እርምጃ መወሰድ አለበት። በተጨማሪ የኢትዮጵያ ህዝብ ሊፋረዳቸው የሚገቡ፤
– ከ1967 ጀምሮ እስከ ዛሬ ያለው የማ/ኪሚቴ አባላት በሙሉ፣
– ከላይ እስከታች ያሉት የደህንነት አባላት፣
– በማእካላዊ ወህኒ ቤት ያገለገሉና የሚያገለግሉ በሙሉ፣
– የህዝብ ግንኙነት ካድሬዎች በሙሉ፣
– በዘራቸው ምክንያት የተሾሙት የህወሓት ጄነራሎች በሙሉ።
-የብአዴን ሥራ አስፈጻሚ የነበሩና የሆኑ፣
ደመቀ መኮንን፣ ገዱ አንዳርጋቸው፣ በረከት ስምኦን፣ አየለ ጎበዜ፣ ዓለምነው መኮንን፣ ብናልፍ አንዱዓለም፣ አህመድ አብተው፣ ተፈራ ደርቤው፣ አምባቸው መኮንን፣ በተጨማሪም የማ/ኮሚቴው አባላት በሙሉ። የኦህዴድ ሥራ አስፈጻሚ የነበሩና የሆኑ፣ አባዱላ ገመዳ፣ ሶፍያን መሃመድ፣ በዙ ዋቅቢያካ፣ አስቴር ማሞ፣ ወርቅነህ ገበየሁ፣ ሙክታር ከዲር፣ ዲሪባ ኩማ፣ አከይል አዚዝ መሃመድ፣ ኡመር ሁሴን፣ አለማየሁ ቶምሳ፣ ኩማ ደመቅሳ፣ ግርማ ብሩ፣ እነዚህና ጠቅላላው የማ/ኮሚቴው።

የደቡብ ህዝብ ሥራ አስፈጻሚ የነበሩና የሆኑ፣
ሃይለማርያም ደሳለኝ፣ ሽፈራው ሽጉጤ፣ ሬድዋን ሁሴን፣ መኩሪያ ሃይሉ፣ ሲራጅ ፈጌሳ፣ ሽፈራው ተ/ሃይማኖት፣ አለመየሁ አሰፋ፣ ደሴ ዳልከ፣ እነዚህና ጠቅላላው የማ/ኮሚቴው። ከላይ ከተጠቀሱት ባልተናነሰ ሁኔታ በዘር ማጥፋት መጠየቅ ያለባቸው፤ የትግራይ ክልል፣ የአማራ ክልል፣ የአፋር ክልል፣ የሶማሊ ክልል፣ የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል፣ የጋምቤላ ክልል፣ የደቡብ ክልል፣ የሃረሪ ክልል፣ የኦሮሚያ ክልል፣ የአዲስ አባባ አስተዳደር፣ የድሬደዋ አስተዳደርም ተጠያቂዎች ናቸው። እነዚህ ከላይ የተጠቀሱት የቅጥረኛ ቅጥረኛ ሆነው በማገልገል፤ የህወሓት ተባባሪ በመሆን የኢትዮጵያን ሉአላዊንት አፍርሰዋል፤ በዘር ማጥፋት ድርጊት ተካፋይ ሆነዋል፣ ኢትዮጵያውያንን ከመሬታቸው በማፈናቀልና በመግደል እንዲሁም ንብረታቸውን
በመንጠቅ ከፍተኛ ግፍ ፈጽመዋል፤ ከወያኔ በመተባባር የማምከኛ መድሃኒት እየወጉ ዘር በማጥፋት ድርጊት ተሰማርተዋል፤ የኢትዮጵያን መሬት ለሱዳን መንግሥት እንዲሸጥ በማድረግ ተባብረዋል፤ በየክልላቸው ድብቅ እስርቤቶችን በመሥራት ተቃዋሚዎችን እና ንጹሃን ዜጎችን ያለፍርድ አስረዋል፤ የኢትዮጵያን ህዝብ ስብአዊ መብቱን በመንፈግ ለግፍና መከራ ዳርገውታል። ውድ የኢትዮጵያ ህዝብ ሆይ!!! ከትግራይ የመጣውና አሁን በሥልጣን ላይ ያለው ፋሺስቱ ህወሓት ሃገራችንን ተቆጣጥሮ በቅኝ ግዛት መዳፍ ውስጥ ካደረጋት እነሆ ዛሬ 24 ዓመታት አልፈዋል። በነዚህ ዓምታት ውስጥ ኢትዮጵያ የባህር በር አልባ ሃገር ሆናለች፣ ለም መሬቷ ከሁመራ እስከ ሞያሌ ያለው የድንበር ሃገራችን ለሱዳን በምልጃ ለወያኔ ጥቅም እየተሰጠ ነው፣ ህዝብ ሊፈናቀል ነው፣ ከሃገሩ ከተወለደበት ካደገበት ተፈናቅሎ የት ሊገባ ነው? ይህ የአማራ ጉዳይ ብቻ አይደለም፣ ሁሉንም የኢትዮጵያ ዜጋ የሚመለከት ነው፣ የኢትዮጵያ ዜጋ በሙሉ ካለአንዳች ልዩነት በአንድነት በመነሳት የሚፈለገውን የህይወት መስዋእትነት ከፍሎ፣ ኢትዮጵያ ሃገራችንን የመሬት ወረራ እናድን። ታሪካዊ መሬት፣ ለም መሬት አሳልፈን ለሱዳን ወራሪ መንግስት በወያኔ የባንዳ ስርአት ኢትዮጵያ በሱዳን አትወረርም። በየቦታው ያሉት ለም መሬቶች ለባእዳን ሃገሮች እየተቸበቸቡ ነው፣ በዚህም ምክንያት የሃገራችን ህዝብ መሬትና ሃገር አልባ በመሆን፣ ለረሃብ፣ ለእርዛት፣ ለበሽታና ለሞት ተዳርጓል፣ ግፉና በደሉ አሁንም ተጠናክሮ ቀጥሏል። ስለዚህ፣ ረሃብና በሽታ በየጊዜው እየተፈራረቁብህ እስከመቼ በባርነት ትኖራልህ? ነፃነትህ ያለችው በእጅህ ላይ ስለሆች እምቢ ለወያኔ፣ አሁንስ በቃኝ ብለህ ተነሳ፣ አሁን የተጀመረውን ህዝባዊ አመጽ በሀይልና በግለት አጠናክር። የህዝብን ቁጣ ምንም ዓይነት ሃይል ስለማይቋቋመው ሆ ብለህ በመነሳት ሃይልህን በማሳየት ሃገራችን ኢትዮጵያን ነፃ አውጣ። የወያኔ ባርነት፣ ግድያ፣ ረሃብ፤ ስደትና ተመጽዋችነት ይብቃህ። ከኢትዮጵያዊ ዜግነትህ አልባ ሆነህ የባንዳ ልጆችና ባንዳዎች አገርህን እየዘረፉ፣ የኢትዮጵያን ሉእላዊነት እያፈረሱና እየሸጡ እያየህ እስከመቸ ነው ዝምታው? አሁንስ በቃ። ፋⶥሽቱን ወያኔ የተዘረጋውን ክንዳችንን አናሳርፍበት።

ድል የኢትዮጵያ ህዝብ ነው
ፐርዝ፣ አውስትራሊያ
ታህሳስ 2008 (ዲሴምበር 2015)

Articles

በኦስሎ ዳይመንድ ሊግ የ5000ሜ ፉክክር ኢትዮጵያውያን አትሌቶች በሁለቱም ፆታዎች በአሸናፊነት አጠናቀዋል

Published

on

Dawit-Seyaum-1
ትላንት ምሽት በኖርዌይ ኦስሎ በተከናወነው የዳይመንድ ሊግ 5000 ሜ. ውድድር ኢትዮጵያውያን አትሌቶች በወንዶችም በሴቶችም ከአንደኛ እስከ ሶስተኛ ያሉትን ደረጃዎች በመቆጣጠር አሸንፈዋል፡፡ 

በዝናባማ የአየር ሁኔታ ውስጥ በተካሄደው የሴቶች 5000 ሜትር ፉክክር ዳዊት ስዩም በመጨረሻዎቹ መቶ ሜትሮች ውስጥ ፍጥነቷን በመጨመር ጉዳፍ እና ለተሰንበትን ቀድማ አንደኛ ወጥታለች፡፡ የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ለኦሪገን 2022 የአለም ሻምፒዮና ከመረጣቸው ዕጩ አትሌቶች ዝርዝር ውስጥ ያልተካተተችው ዳዊት በኦስሎ ያሸነፈችበት 14፡25.84 የሆነ ሰአት የራሷ ምርጥ ሲሆን እጅጋየሁ ታዬ (14.12.98) እና ለተሰንበት (14፡24.59) ባለፈው ወር በዩጂን ካስመዘገቧቸው በመቀጠልም የዘንድሮ የአለም ሶስተኛው ፈጣን ነው፡፡ በውድድሩ ላይ ከነበሩት ሌሎች ኢትዮጵያውያን መካከል በዘንድሮው የውድድር ዓመት በርቀቱ የመጀመሪያ ተሳትፎዋን ያደረገችው አልማዝ አያና በ14:32.17 ስድስተኛ ሆና አጠናቃለች፡፡ ሀዊ ፈይሳ በ14:33.66፣ ፅጌ ገብረሰላማ በ14:43.90፣ እና አበራሽ ምንሴዎ በ14:47.98 በቅደም ተከተል ሰባተኛ፣ አስረኛ እና አስራ አንደኛ ሆነው ሲያጠናቅቁ ሶስቱም ያስመዘገቡት ሰዓት የራሳቸውን ምርጥ ያሻሻሉበት ሆኗል፡፡ ጥሩነሽ ዲባባ እ.ኤ.አ. በጁን 2008 ዓ.ም. ያስመዘገበችውና 14:11.15 የሆነው የኦስሎ ዳይመንድ ሊግ የሴቶች 5000 ሜትር የውድድር ስፍራ ሪከርድ ይሰበራል ተብሎ ተጠብቆ የነበረ ቢሆንም ሳይሳካ ቀርቷል፡፡  
ዳዊት ስዩም ውድድሩን በድል ካጠናቀቀች በኋላ ለውድድሩ አዘጋጆች በሰጠችው አስተያየት ‹‹ዛሬ ለእኔ ደስታን ስላመጣልኝ በውድድሩ ሰዓት የነበረውን ዝናብ ወድጄዋለሁ ማለት እችላለሁ፡፡ ጠንካራ ተፎካካሪዎች የነበሩበት ከባድ ውድድር ነበር እናም ሁሉንም ለማሸነፍ በቅቻለሁ። በርቀቱ የራሴን ምርጥ ሰዓት ማሻሻል መቻሌም አስፈላጊ ነበር፡፡ በስታድየሙ ውስጥ በከፍተኛ ስሜት ድጋፍ ይሰጡን የነበሩ ወገኖቻችን ነበሩ። ለሰጡን ድጋፍ እናመሰግናለን።›› ብላለች፡፡
 
በኦስሎ የወንዶች 5000 ሜትር የመጨረሻ ፉክክሩ በኢትዮጵያውያኑ ጥላሁን ሀይሌ እና ሳሙኤል ተፈራ መካከል የነበረ ሲሆን ጥላሁን የ1500 ሜትር ስፔሻሊስቱ ሳሙኤልን በአጨራረስ ፍጥነት ቀድሞ በ13:03.51 በአንደኛነት አጠናቋል፡፡ ሳሙኤል ተፈራ የራሱ ምርጥ በሆነ 13:04.35 ሁለተኛ ሲወጣ ጌትነት ዋለ የግሉ የዓመቱ ምርጥ በሆነ 13:04.48 ሶስተኛ ደረጃን ይዞ ጨርሷል። በውድድሩ ላይ የነበሩት ሌሎች ኢትዮጵያውያን ሚልኬሳ መንገሻ በ13:05.94 አምስተኛ እንዲሁም አሊ አብዱልመናን የራሱ ምርጥ በሆነ 13:16.97 አስረኛ ወጥተዋል፡፡
ጥላሁን ሀይሌ ውድድሩን በአሸናፊነት ካጠናቀቀ በኋላ ለውድድሩ አዘጋጆች በሰጠው አስተያየት ‹‹ሶስት ኢትዮጵያውያን የመጀመሪያዎቹን ሶስት ደረጃዎች ይዘን መጨረስ መቻላችን ጥሩ አፈጻጸም ነበር። እየጠነከርኩ እንደሆነ የተሰማኝ ሲሆን በውድድሩ እና ባስመዘገብኩት ሰዓትም ተደስቻለሁ። ለረጅም ጊዜ ጉዳት ላይ ስለነበኩ ወደ አሸናፊነቱ መመለስ መቻሌ በጣም ጥሩ ነው።›› ብሏል፡፡

በኦስሎ የሴቶች 800ሜ. ውድድር ላይ ተፎካካሪ የነበረችው ኢትዮጵያዊቷ ድሪቤ ወልቴጂ በ1፡58.69 አምስተኛ ሆና አጠናቃለች።
Continue Reading

Articles

የዘንድሮው የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ብሄራዊ ሻምፒዮና በእኔ እይታ

Published

on

IMG_0110
ከመጋቢት19-24/2014 ዓ.ም በሐዋሳ አለም አቀፍ ስቴድዮም የተደረገው 51ኛዉ የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ሻምፒዮና ከሞላ ጎደል ስኬታማ በሚባል ሁኔታ ተጠናቋል፡፡ ከአምስት አመት በኋላ በድጋሚ በአካል በመገኘት ስለተከታተልኩት የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ሀገር አቀፍ ሻምፒዮና የግል ምልከታዬን እንደሚከተለው አጠናቅሬዋለሁ፡፡

የበለጠ ትኩረትን በሳቡት ውድድሮች ዙሪያ የተመዘገቡ ውጤቶችን በወፍ በረር በመዳሰስ ስጀምር ከፍተኛ ፉክክር በታየበት የመጨረሻ ቀን የወንዶች 5000ሜ. የአለም ከ20 አመት በታች ሻምፒዮና የ3000ሜ የብር ሜዳልያ አሸናፊው አሊ አብዱልመና 13፡45.0 በሆነ ሰዓት ከጥላሁን ሀይሌ፣ ጌትነት ዋለ እና ዮሚፍ ቀጄልቻ ቀድሞ አሸናፊ ሆኗል፡፡ የፉክክሩ አካል የነበረው እና የርቀቱ የወቅቱ የአለም ሻምፒዮን ሙክታር እድሪስ ስድስተኛ ወጥቷል። 

ከ20 ዓመት በታች የ3000ሜ የአለም ሻምፒዮኑ ታደሰ ወርቁ በ28፡12.0 የወንዶች 10,000ሜ. ሻምፒዮን ሲሆን በ1996 ዓ.ም. በአትሌት ስለሺ ስህን ተመዝግቦ የነበረውን 28፡16.23 የሆነ የሻምፒዮናው ሪኮርድ ለማሻሻልም በቅቷል፡፡ በ10 ሺህ ሜትር የሴቶች ፉክክር ግርማዊት ገብረእግዚአብሔር በቀዳሚነት የጨረሰችበት 31፡21.5 የሆነ ሰዓት አዲስ የሻምፒዮንሺፕ ሪኮርድ ሆኖ ተመዝግቧል፡፡ በርቀቱ የከዚህ ቀደሙ ሪኮርድ  ለተሰንበት ግደይ ከሶስት ዓመት በፊት ያስመዘገበችው 32፡10.13 የሆነ ሰዓት ነበር፡፡

ሳሙኤል ፍሬው በዘንድሮ የወንዶች 3000ሜ. መሰናክል አፈፃፀም ከአለም ሁለተኛው ፈጣን በሆነ 8፡22.5 ሰዓት አሸናፊ ሲሆን ጌትነት ዋለ ከአራት ዓመት በፊት አስመዝግቦት የነበረውን 8፡28.98 የነበረ የሻምፒዮናው ሪኮርድም አሻሽሏል፡፡ በሴቶች 3000ሜ. መሰናክል ከ800ሜ ወደ ረጅም ርቀት የተሸጋገረችው ወርቅውሃ ጌታቸው በ9፡41.8 ሰዓት መቅደስ አበበን (9:43.8) በማስከትል በአሸናፊነት አጠናቃለች። 

አድሃና ካህሳይ (3:51.0) የወንዶች 1500ሜ ፉክክሩን በበላይት ሲያጠናቅቅ በሴቶች 1500 ሜ አያል ዳኛቸው (4:10.0) ተጠባቂዋ ዳዊት ስዩምን (4:11.1) በመቅደም በአንደኛነት አጠናቃለች። በ800ሜ. ወንዶች ቶሌሳ ቦደና (1:47.1) በሴቶች ወርቅነሽ መሰለ (2:02.1) አሸናፊ ሆነዋል።
ዮብሰን ብሩ በ400ሜ/400ሜ መሰናክል (45.9/50.5) ድርብ ድል ሲቀዳጅ፣ በወንዶች ጦር ውርወራ ኡታጌ ኡባንግ ብሔራዊ ሪኮርድ በሆነ 73.28ሜ. አሸንፏል፡፡ የኋልዬ በለጠው እና ዮሃንስ አልጋው በእርምጃ ሩጫ የሻምፒዮንነት ክብርን ተቀዳጅተዋል።

ጥቂት አስተያየቶች፡-
የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ስፖርት አፍቃሪ እንደሆነ እና ለዕድገቱ እንደሚቆረቆር ሰው በብሔራዊ ሻምፒዮናው ላይ ስለተመለከትኳቸው አዎንታዊ እና አሉታዊ ጎኖች ጥቂት አስተያየቶቼን እንደሚከተለው አስቀምጣለሁ፡-

አዎንታዊ ጎኖች
• ባለው ነባራዊ ሁኔታ ውስጥ ሊገጥሙ የሚችሉትን ተግዳሮቶች በሙሉ በመቋቋም ፌዴሬሽኑ ውድድሩን ከአዲስ አበባ ውጭ አካሂዶ በሰላም ማጠናቀቅ መቻሉ አንደኛው ስኬቱ ነው፡፡

• በሻምፒዮናው ላይ ጥቂት የማይባሉ ታዋቂ አትሌቶች በሀገሪቱ ትልቁ የአትሌቲክስ ፉክክር ላይ ተሳታፊ ሆነው ሲወዳደሩ መመልከት የተቻለ ሲሆን በተለይም በወንዶች 5000 ሜትር ፍፃሜ ላይ የታየው የኮከብ አትሌቶች ፉክክር ልዩ ነበር፡፡

• በውድድሩ ወቅት ለአትሌቲክስ ዳኞች የብቃት ማሻሻያ ስልጠና መሰጠቱም የውድድሩን ጥራት ለማሳደግ የሚረዳ እንደመሆኑ እሰየው የሚባል ነው፡፡
 
• እንደ ኢትዮ ኤሌክትሪክ ያሉት ክለቦች ለአትሌቲክስ ስፖርት የበለጠ ትኩረት በመስጠትና ተጠናክሮ በመቅረብ ከዚህ ቀደም በጠንካራነታቸው ከሚታወቁት መከላከያ እና ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ጋር የቅርብ ተፎካካሪ ሆነው መታየት፤ የኦሮሚያ ክልል፣ ደቡብ ፖሊስ እና ሲዳማ ቡና ክለብ አትሌቶችም ጠንካራ ተሳትፎ ሳይዘነጋ የሻምፒዮናው ፉክክር ድምቀት ነበሩ፡፡  
• የአንዳንዶቹ ተገቢነት አጠያያቂ ቢሆንም ብዛት ያላቸው የሻምፒዮናው ሪኮርዶች የተሻሻሉበት ውድድርም ነበር፡፡ 

አሉታዊ ጎኖች
• የሀገሪቱ ትልቁ የአትሌቲክስ ውድድር ውጤት አሁንም በኤሌክትሮኒክስ የሰዓት መቆጣጠሪያ የማይደገፍ መሆኑ በተለይም በአጭር ርቀት እና በሜዳ ላይ ተግባራት ውድድሮች ላይ የሚሳተፉ አትሌቶች ልፋት ተገቢውን እውቅና እንዳያገኝ እያደረገ ይገኛል፡፡ የሻምፒዮናውን ውጤቶች በዘመናዊ እና ዓለም አቀፉን መለኪያ በሚያሟላ መልኩ አለመያዝ በአህጉራዊ እና አለም አቀፋዊ ውድድሮች ላይ ለተሳትፎ የሚያበቁ ውጤቶችን በማስመዝገቡ ረገድ የሚኖረው አሉታዊ ተፅዕኖ ከፍተኛ መሆኑ ከግምት ውስጥ ገብቶ አሁንም መፍትሄ ያልተበጀለት ጉዳይ ነው፡፡ 
 
• የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ወደ ሚዲያ/ለአጠቃላዩ ሕዝብ የሚያስተላልፈው የመጀመሪያዎቹን ሶስት ደረጃዎች ይዘው የሚያጠናቅቁ አትሌቶችን ውጤት ብቻ መሆኑ አወዳዳሪው አካል የሚያደርገውን የራሱን ውድድርም ሆነ አትሌቶቹ የለፉበትን ውጤት ከማስተዋወቅ አኳያ በቂ አይደለም፡፡
  
• በወንዶች የጦር ውርወራ እና የሴቶች ምርኩዝ ዝላይ ብሔራዊ ሪኮርዶች እንደተመዘገቡ ይታመናል፤ በሴቶች 100ሜ መሰናክል እና የወንዶች 400ሜ መሰናክል የተመዘገቡት ሰዓቶችም የምንግዜውም ፈጣን ሊሆኑ ይችላሉ፡፡ ነገር ግን ውድድሩ በኤሌክትሮኒክስ ታይሚንግ ያልተደገፈ እና የንፋስ ንባብ ያልነበረው መሆኑ ውጤቶቹ በዓለም አቀፍ ደረጃ ተቀባይነት እንዳይኖራቸው የሚያደርግ ነው።

• በ20 ኪ.ሜ የእርምጃ ውድድር ላይ በሁለቱም ፆታዎች የተመዘገቡት ሰዓቶች ከሚጠበቀው በላይ እጅግ በጣም ፈጣን እና እውነታዊ አለመምሰላቸው በውድድሩ ላይ የተፈጠረ አንዳች ስህተት መኖሩን የሚያመላክቱ መሆኑ፡፡ እንዲህ አይነት ለማመን የሚከብዱ እና ጥርጣሬን የሚፈጥሩ አይነት ውጤቶች ሲመዘገቡም የተፈጠረ ስህተት መኖር አለመኖሩን ለማጣራት አለመሞከሩ፡፡
     
• የሴቶች 10 ኪሎ ሜትር ውድድር ላይ ለውድድር የማይፈቀድ የጎዳና ላይ መሮጫ ጫማን በመጠቀም የተመዘገበ ውጤት በሪኮርድነት ጭምር ተይዞ መፅደቁ። ብሔራዊ ፌዴሬሽኑ ከተከለከሉ ጫማዎች ጋር የተያያዙ ዓለም አቀፍ ሕገ ደንቦችን ማወቅና መተግበር ቢገባውም በሴቶች 10 ሺህ ሜትር ውድድር ላይ የተከሰተው ነገር የውድድር ሕገ ደንቦቹ መረጃ በፌዴሬሽኑ ውስጥ በትክክል የተሰራጩ እንዳልሆነ የሚያመላከት ነው፡፡  

• በሴቶች 1500 ሜትር የግማሽ ፍፃሜ ውድድር ላይ አትሌት ዳዊት ስዩም የሻምፒዮናውን ሪኮርድ ያሻሻለችበት ውጤት እንደተመዘገበ በውድድሩ ወቅት በተደጋጋሚ ሲነገር ከተደመጠ በኋላ ግልፅ ባልተደረገ ምክንያት ውጤቱ በሐዋሳው ውድድር ላይ ተሻሻሉ ከተባሉት የሻምፒዮናው አዲስ ሪኮርዶች ዝርዝር ውስጥ ሳይካተት መቅረቱም የፌዴሬሽኑን ግልፀኝነት ጥያቄ ምልክት ውስጥ የሚከት ነው፡፡

ከላይ የተዘረዘሩት አዎንታዊ እና አሉታዊ ጎኖች ለረጅም ግዜ የኢትዮጵያን አትሌቲክስ ስፖርት እንቅስቃሴዎች በቅርበት ከመከታተሌ አንፃር በራሴ እይታ ያስቀመጥኳቸው እንደመሆናቸው አንዳንዶቹ ሀሳቦች አከራካሪ ሊሆኑ ይችላሉ፡፡ ሆኖም የውድድር ደንቦችን በአግባቡ ከማስፈፀም አኳያ በታዩት ክፍተቶች ዙሪያ ምንም የሚያከራክር ጉዳይ ስለሌለ በወቅታዊ የውድድር ደንቦች ዙሪያ የግንዛቤ እጥረት ላለባቸው የስፖርቱ ባለድርሻ አካላት በሙሉ አስፈላጊውን ገለፃ እና ትምህርት መስጠት የፌዴሬሽኑ ኃላፊነት ነው፡፡ ከውድድር ጋር የተያያዙ ደንቦችን ከመጣስ አኳያ በሀገር ውስጥ በሚደረጉ ውድድሮች እንደቀላል ነገር የሚታለፉ ጉዳዮች በዓለም አቀፍ ውድድሮች ላይም ተደግመው እንደግል አትሌቶችን እንደቡድን ሀገርን ትልቅ ዋጋ ሊያስከፍሉ ይችላሉና አስፈላጊው ጥንቃቄ ቢደረግ መልካም ነው፡፡ ባለፈው መስከረም ወር በቪየና ሲቲ ማራቶን ውድድሩን በአሸናፊነት ጨርሶ የነበረው ኢትዮጵያዊው ደራራ ሁሪሳ የገጠመውን አንዘንጋው! 

ሀገራችን ኢትዮጵያን በመልካም ጎኑ ስሟ እንዲነሳ በሚያደርገው እና በትልልቅ ዓለም አቀፍ የውድድር መድረኮች ላይ የኩራታችን ምንጭ በሆነው የአትሌቲክስ ስፖርት እንደጎረቤታችን ኬንያ ዓለም አቀፍ ውድድሮችን የማስተናገድ የብቃት ደረጃ ላይ ደርሰን ማየት የዘወትር ምኞቴ ነው፡፡ የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌደሬሽንም የውድድሮቹን ጥራት ለማሻሻል በትኩረት እንደሚሰራ ተስፋ አደርጋለሁ።      
      
የ10,000ሜ. አሸናፊ የሆነችው ግርማዊት ገብረእግዚአብሔር (Photo by EAF)

በመጨረሻም በሀዋሳ በተካሄደው 51ኛዉ የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ሻምፒዮና ከመሮጫ ጫማ ጋር የተያያዙ ደንቦችን በማስከበሩ ረገድ የተፈጠረውን ክፍተት እንደማስተማሪያ ብንጠቀምበት በሚል የሚከተለውን ለማለት ወደድኩ፡-

የመሮጫ ጫማ ደንቦች ለትራክ ውድድር

64 ደቂቃ ከ14 ሰከንድ በሆነ ሰዓት የዘንድሮ የራስ አል ካይማህ የግማሽ ማራቶን ውድድር አሸናፊ የሆነችው ግርማዊት ገብረእግዚአብሔር በሐዋሳ በተከናወነው 51ኛው የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ሻምፒዮና ላይ 31 ደቂቃ ከ21.5 ሰከንድ  በመግባት የ10,000ሜ. አሸናፊ ሆናለች፡፡ የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽንም ዓለም አቀፉን ደንብ ከግምት ባላስገባ ሁኔታ ውጤቱን በአዲስ የሻምፒዮንሺፕ ሪኮርድነት ጭምር አፅድቆት አልፏል፡፡ ይሁን እንጂ መጋቢት 20/2014 በተደረገው የሴቶች የፍፃሜ ፉክክር ላይ በኢትዮጵያ ምድር የተመዘገበ የምንግዜውም ፈጣን የሴቶች 10 ሺህ ሜትር ሰዓት የሆነው ውጤት በአለም አትሌቲክስ ዘንድ እውቅና ሊሰጠው የማይችል ነው።

ለምን?

አትሌቷ የሶል ውፍረቱ 40ሚሜ የሆነ ዙምኤክስ ቬፐርፍላይ (ZoomX Vaporfly) ጫማ አድርጋ በመወዳደሯ ምክንያት።

ደንቡ ምን ይላል?

በትራክ ውድድሮች ላይ የሚፈቀደው ከፍተኛው የሶል ውፍረት ፡-
– 20ሚሜ ከ 800ሜ በታች ለሆኑ ውድድሮች እና ለሁሉም የሜዳ ላይ ተግባራት (ከስሉስ ዝላይ በስተቀር)

– 25ሚሜ ለ800ሜ እና ከዛ በላይ ለሆኑ ውድድሮች እንዲሁም ለስሉስ ዝላይ

– 40ሚሜ ለትራክ ላይ የእርምጃ ውድድሮች

እነዚህ ደንቦች እ.ኤ.አ. እስከ ኦክቶበር 31, 2024 ድረስ በሥራ ላይ ይውላሉ። ከኖቬምበር 1 ቀን 2024 ጀምሮ ለ800ሜ እና ከዚያ በላይ ለሆኑ ውድድሮች እንዲሁም ለስሉስ ዝላይ የሚፈቀደው ከፍተኛ የሶል ውፍረትም ወደ 20 ሚሜ ዝቅ የሚል ይሆናል።

የትራክ ላይ መወዳደሪያ ስፓይክ ጫማ ከሌለኝስ?  

ደንቡ የጎዳና ላይ የመሮጫ ጫማዎች በትራክ ላይ እንዳይደረጉ አይከለክልም ነገር ግን በ25 ሚሊ ሜትሩ ገደብ ምክንያት 30 ሚሜ ወይም 40 ሚሜ የሆኑ የጎዳና ላይ መሮጫ ጫማዎች በትራክ ውድድሮች ላይ እንዲደረጉ አይፈቅድም፡፡

ለበለጠ መረጃ :-
https://www.worldathletics.org/news/press-releases/new-athletic-shoe-regulations-approved-2022

Continue Reading

Opinions

On the TPLF’s Love Affair With ‘Genocide’

Published

on

WhatsApp-Image-2021-11-04-at-12.41.51-AM
Ethiopia's Lalibela, a UN World Heritage Site, now under Tigrayan forces control

Today, the joint investigation report by the Ethiopian Human Rights Council and the UNHR
on human rights violations committed in Tigray concluded that there is no evidence that genocide has taken place so far. While this is a bit of a setback for the TPLF, which has wanted the world to believe—since the 1990s, even as the TPLF was dominating power in Addis—that a genocide has been perpetrated against the people of Tigray, unfortunately the group still appears to be determined to make genocide a reality. This is confusing for people who don’t understand why the TPLF is obsessed with genocide, why its internet cadres began using #TigrayGenocide in April 2020, months before the war began. So many weapons have been deployed in this war, and among them: confusion and obfuscation.


In the past several months and more so in the past few weeks, we have been getting
testimony after testimony from allied Amhara forces fighting the TPLF that Tigrayan residents of cities in Wollo have been collaborating with the TPLF by a) attacking ENDF and allied forces from behind; b) forcing ENDF and allied forces to withdraw from towns and cities afraid of committing large scale massacres by firing back at the civilians (Tigrayans) firing at them; c) helping the TPLF locate and execute young Amharas believed to be a threat; and d) in at least one horrifying account by an IDP who managed to escape occupied territories, handing TPLF soldiers a list of women to rape. Another shocking development in the past several months has been the widespread use of child soldiers by the TPLF, which, according to experts who have studied the practice, is an “alarm bell” calling attention to possible plans to commit mass atrocities. The use of child soldiers by the TPLF and its attendant implications, along with the widespread deployment of civilian sleeper agents in Amhara cities the TPLF has taken over, serves to create an overall perception of every Tigrayan as a potential enemy, sowing fear and mistrust.

Many Ethiopians are looking at this and wondering: why are Tigrayan elites on the internet
either celebrating the TPLF’s advance via these toxic methods or silent about all this? How can they not see how dangerous this is for everyone, especially for Tigrayans who live outside Tigray? How can they not see that there is no “winning” after stoking all this lasting animosity? Do Tigrayan elites not understand that there can be no justice for Tigray—whether Tigray secedes or not—unless there is justice for her neighbors, for Tigray does not exist in a vacuum? The questions are being asked but nobody is answering them. Our academic class has largely failed to offer viable analyses of the ideas driving this war, as they failed over the past fifty years in regards to coming up with a fitting paradigm for understanding Ethiopia’s unique situation.


Here is my humble attempt to explain what I think is happening with the TPLF’s obsession
with—and with its active attempt to inspire—genocide:


The most successful psychopaths in any field understand that, in order to win anything, one
must risk everything, including the very thing one is supposedly fighting for. In the case of the
TPLF (and associated Tigrayan political elites), whose motto appears to be “give me supremacy or give me death,” that “everything” they are risking is the lives of ordinary Tigrayans in whose names they are fighting. We have seen over the past several months the extent to which the TPLF is willing to go to sacrifice ordinary Tigrayans in order to get what it wants: wave after wave after wave of young poorly armed and inexperienced Tigrayans were unleashed upon ENDF and Amhara and Afar forces in order to force the latter to waste ammunition and energy before the more experienced soldiers are sent.


So, for a political group who sends tens of thousands, if not hundreds of thousands, of
young Tigrayans towards open fire, violence against hundreds of thousands of Tigrayans is nothing if it means the TPLF will in the end win the “prize” it has been obsessed with for decades: genocide. You see, merely attaining power in Addis Ababa is not enough for the TPLF, whose core driving ideology is Tigrayan supremacy. Power is temporary; anybody can take it away from you, and the 2018 uprisings demonstrated that. Genocide is forever. Nobody can take away from you the story of genocide committed against your people.


The TPLF looked at countries like Israel and Rwanda and realized what a potent instrument
genocide is for establishing perpetual minority rule. We have some indications suggesting that the TPLF views Israel as a model. When the war between Ethiopia and the TPLF began in November 2020, Sekoutoure Getachew, a TPLF official, went on TV to tell us that the TPLF’s decision to launch a preemptive attack on the Northern Command was inspired by how the young state of Israel, feeling threatened by her neighbors, launched preemptive attacks against them in the “six-day war” of 1967. Another indication is the manner in which the TPLF, during its 27 years in power, invested heavily in creating a wealthy and strongly networked Tigrayan diaspora which has been used to lobby and influence western governments and organizations much in the same way as the Jewish diaspora aids the state of Israel. The TPLF has figured out that truth does not matter in politics, especially in international politics. If you have the wealth and the personnel to peddle your preferred narrative, if you have the military power to subdue the people you want to subdue, if you are willing to make concessions to external forces (US, Egypt, etc), you can do unspeakable things to others (much like the state of Israel does to Palestinians) and still manage to portray yourself as the victim.
This calculation is so far working for the TPLF, but nothing would seal the deal like the actual
commission of genocide—or something that looks like it—against Tigrayans. As we have seen over the past twelve months, western governments and organizations have shown their willingness to adopt TPLF’s narratives without scrutiny and can easily reward the TPLF with its much pursued prize, genocide, even if actual genocide doesn’t take place.


But why does the TPLF need genocide to establish minority rule? Because, as we saw in their
first tenure in power, you can only rule with an iron fist for a limited period of time. Leaders of the TPLF are adherents of Tigrayan supremacy: the idea that Tigrayans, as the “only” heirs of the Axumite empire, are the natural rulers of the Ethiopian state, and cannot be ruled by “barbarians” south of them. The only acceptable power arrangement for the TPLF is one in which Tigrayans are either directly dominating political power or are the perpetual kingmakers pulling all the major strings. Anything outside that, any system that forces Tigrayans to live on equal footing with everyone else, is unacceptable. And this kind of domination by a minority cannot coexist with a democratic system that the majority of Ethiopians clearly prefer. So, the TPLF needs something more potent than pure political/economic/military power to justify bypassing democracy to establish itself as the permanent ruler/kingmaker of Ethiopia. It needs a new and powerful raison d’être to justify its domination not just to Tigrayans and the rest of Ethiopians but, and most importantly, to the rest of the world. If a genocide were to be committed against Tigrayans (or if the U.S. decides to reward the TPLF with the genocide label even in the absence of it), then the TPLF can license itself to impose all manner of drastic measures aimed at “protecting Tigray and
Tigrayans.” This could be anything from redrawing internal borders (and taking debilitating
measures against the peoples whose lands are being robbed—most likely Amharas and Afaris—so that they will never be in a position to assert themselves) to ethnic cleansing and genocide against populations considered to be a threat. And when you oppose it, the TPLF will say “you committed a genocide against Tigrayans” over and over and over, and its western backers will repeat the same chorus. If they have been this loud over a non-existent genocide over the past twelve months, just imagine what it would be like if the U.S. or UN rewards them with that label.


And this is where the Ethiopian government’s major dilemma comes from: if ENDF and
Amhara forces fight to regain their cities and towns, they risk committing large scale massacres. The TPLF networks reported to be operating within these cities wear civilian clothing and fire at the armies from inside civilian establishments, in an apparent attempt to set up pro-Ethiopia forces. Pro-Ethiopia forces are essentially being dared to commit large scale massacres in order to win back their own cities. So far, they are choosing to withdraw from these towns and cities. But that is another problem: not only is the TPLF committing unspeakable violence against civilians and destroying infrastructure in those cities, the takeovers are emboldening it to continue pressing, giving young people back in Tigray false hope that they are winning and—this is very important—the false idea that they are being “welcomed” by locals in those cities. Then more and more and more young Tigrayans are sent to their deaths.


So the Ethiopian government is stuck between a rock and a hard place. One option is
allowing its forces to do whatever it takes to take back territory, thereby offering protection to its citizens in Wollo and elsewhere, but also risking the “genocide” label by western governments who have been eagerly waiting for such an opportunity so that they can blackmail the government into submitting itself to their wishes on GERD and other issues. Option two is avoiding large scale violence and allowing the TPLF to take power in Addis Ababa and do to Ethiopia what it wishes. One of the things it might do to Ethiopia, according to its leaked strategy document, is force a confederation that will no doubt privilege some states, i.e. Tigray, more than others, and that will no doubt be designed to subdue some populations—mainly Amharas and Afaris—who are considered obstacles to Tigray’s aspirations of domination and expansion (in the TPLF’s original manifesto, Afar is claimed as Tigray land).


And there is absolutely no doubt that the TPLF will make big concessions on the GERD in
order to compensate its western and Egyptian backers, if not redraw borders to make Benishangul Gumuz Tigrayan territory. If you think this is wild, read about the history of the state of Israel, the TPLF’s model state. The redrawing of borders that the TPLF undertook in 1991 was also wild at the time; people don’t think of it as outrageous anymore because the fact that they held onto the territory for 30 years has normalized the event in our minds. And that’s all the TPLF needs: another thirty years to normalize all the outrageous things they will do next.

One may argue that this is a false dichotomy, that there is a third or even maybe fourth option: winning these cities back without mass violence much in the same way the ENDF managed to do during its first campaign in Tigray. We all should pray for such a miracle, of course. However, one can also say that in the early days of the war, the TPLF was mostly withdrawing from Tigrayan cities to avoid urban warfare. And even when they engaged in urban warfare, it was not at the same scale and intensity as has been the case over the past four and half months or so. Starting in mid June, the TPLF’s use of civilians as human shields and fighters stopped being just another weapon in its arsenal and became a center of its operations. The near collapse of the ENDF inside Tigray right before its withdrawal was precipitated by the TPLF’s intensified use of “civilians” to trap the ENDF. Many ENDF soldiers chose to surrender rather than fire at those “civilians.” It is still possible to avoid large scale violence in the attempt to retake towns in Wollo, but the risk for it is very high, and is possibly behind the federal government’s reluctance to take decisive actions.


The point is: barring miracles, the Ethiopian government is positioned to lose something
one way or another. All that is left is choosing its preferred poison. Perhaps one thing to consider for the federal government is: the rights of Amharas and Afaris to defend themselves against the existential threats posed against them by the TPLF is much bigger than the national government’s concerns about its place and relationships with the rest of the world. If the federal government decides to risk the disintegration of Ethiopia, like it has done so far either due to incompetence or severe fear of committing large scale violence, that is fine for the federal government. But when you allow that disintegration to happen, please don’t leave the people of Amhara and Afar in a vulnerable position, unable to defend themselves and their lands. If we must return to the State of Nature, at least give these two peoples, who have so far shed more blood than anyone else in defense of their country, a chance to preserve their lives and their lands. Give them the resources they need to defend themselves before it is too late for them even if you feel it is too late for Ethiopia. Anything less is just a continuation of the gross criminal negligence that the federal government has been guilty of so far.

Continue Reading

Trending