Articles
‹‹በስራዬ እቀጥላለሁ›› ማሪያኖ ባሬቶ

‹‹በስራዬ እቀጥላለሁ›› ማሪያኖ ባሬቶ
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን በአዲስ አበባ ስታዲየም ከማሊ አቻው ጋር ያደረገውን የ2015 አፍሪካ ዋንጫ ማጣሪያ ሶስተኛ ጨዋታ ተሸንፎ የማለፍ እድሉን አመንምኗል፡፡ የቡድኖቹን የሜዳ ላይ እንቅስቃሴ፣ በአዲስ አበባ ስታዲየም የነበረውን ድባብ እና የተፈጠሩ ሁነቶች እንዲሁም ከጨዋታው በኋላ የዋልያዎቹ አለቃ ማሪያኖ ባሬቶ ከጋዜጠኞች ለቀረቡላቸው ጥያቄዎች የሰጧቸው ምላሾች በቀጣዩ ዘገባ ተዳስሰዋል፡፡
ከ31 ዓመታት ረዥም ጥበቃ በኋላ በአህጉራዊው መድረክ መሳተፍ የቻሉት ዋልያዎቹ ለተከታታይ ዓመት በውድድሩ ላይ ለመገኘት የነበራቸው ተስፋ ጥያቄ ውስጥ የገባው የምድብ ድልድሉ ሲወጣ ከወቅቱ የአፍሪካ ቁጥር አንድ አልጄሪያ እና ካለፉት ሁለት ውድድሮች የግማሽ ፍፃሜ ተፋላሚ ማሊ ጋር ሲመደቡ ነበር፡፡ ነገር ግን በሜዳቸው ያላቸው ጥሩ ሬኮርድ እና አንድ ምርጥ ሶስተኛ ቡድን ማለፍ መቻሉ የተስፋ ጭላንጭል ሰጥቷቸው ማጣሪያውን ጀምረዋል፡፡ የመጀመሪያ ሁለት ጨዋታቸውን በአልጄሪያ እና በማላዊ መረታታቸው ግን የማሊውን ጨዋታ በማሸነፍ ግዴታ ውስጥ ገብተው እንዲጀምሩ አድርጓቸዋል፡፡ እንደ ሌሎቹ ያለፉ የአዲስ አበባ ጨዋታዎች የስታዲየሙን ዙሪያ ገባ ያጣበበ የተመልካቾች ሰልፍ እና ወረፋ ባይታይም ስታዲየሙ ሙሉ ነበር፡፡ በቀድሞው ቡድን ወሳኝ ተጨዋቾች ቅነሳ፣ በሚከተሉት የአጨዋወት ሲስተም እና በመሳሰሉ ጉዳዮች አነጋጋሪ ሆነው የሰነበቱት አሰልጣኝ ማሪያኖ ባሬቶ ጨዋታውን የጀመሩት በሚወዱት 4-3-3 ፎርሜሽን የሚከተሉትን ተጨዋቾች ይዘው ነበር፡-
ሲሳይ ባንጫ (ግብ ጠባቂ)፣ አበባው ቡታቆ (ግራ ተከላካይ)፣ ሳላህዲን ባርጌቾ (መሀል ተከላካይ)፣ ዋሊድ አታ (መሀል ተከላካይ)፣ ቢያድግልኝ ኤልያስ (ቀኝ ተከላካይ)፤ በአማካይ ስፍራ ናትናኤል ዘለቀ፣ አንዳርጋቸው ይላቅ እና ሽመልስ በቀለ እንዲሁም በአጥቂ ስፍራ ዩሱፍ ሳላህ፣ ጌታነህ ከበደ እና ኡመድ ኡኩሪ፡፡
የማሊ ብሔራዊ ቡድን በበኩሉ በመጀመሪያ አሰላለፉ ማማዱ ሳማሳን በግብ ጠባቂነት፤ ኦስማኔ ኩሊባሊ፣ ፎውሴይኒ ዲያዋራ፣ ሳሊፍ ኩሊባሊ፣ እና አዳማ ታምቡራን በተከላካይ ስፍራ፤ ያኩባ ሲይላ፣ ቶንጎ አህመድ ዱምቢያ፣ ባካሪ ሳኮ እና ሴይዱ ኬይታን በአማካይ ስፍራ እንዲሁም ሙስታፋ ያታባሬ እና አብዱላዬ ዲያቢን በአጥቂነት በማሰለፍ በ4-4-2 ፎርሜሽን ጨዋታውን ጀምሯል፡፡ ጨዋታውን የመሩት አርቢትሮች ከቱኒዚያ ነበሩ፡፡
ወደ ጨዋታው ስናመራ በስታዲየሙ የሞላው ደጋፊ የተደራጀ የማጥቃት እንቅስቃሴ፣ ተነሳሽነት እና ጎሎችን ከብሔራዊ ቡድናችን ቢጠብቅም ከጨዋታው መጀመሪያ ፊሽካ መነፋት ጀምሮ ይህን ያሳዩት እንግዶቹ ማሊዎች ነበሩ፡፡ ንስሮቹ በታላቁ አምበላቸው ሴይዱ ኬይታ እየተመሩ በዘመናዊው አፍኖ የመጫወት (pressing) እንቅስቃሴ ጨዋታውን በበላይነት ከመቆጣጠራቸው ባሻገር የቡድናችን ተጨዋቾች ተረጋግተው የራሳቸውን ጨዋታ እንዳይጫወቱ አግደዋቸው ውለዋል፡፡ በዚህም ተከላካዮቻችን ኳሶችን በሚገባ ለአማካዮች ማድረስ፣ አማካዮቻችንም ጨዋታውን መቆጣጠር እና ችግር ፈጣሪ ኳሶችን ለአጥቂዎቹ ማቀበል፣ አጥቂዎቻችንም የተጋጣሚን ተከላካዮች መረበሽ እና የጎል ሙከራዎችን ማድረግ እጅጉን ተቸግረው ነበር፡፡ የሄንሪ ካስፔርዣክ በሁሉ ረገድ የተዋጣለት ቡድን ሲያደርግ የነበረው ምሉዕ እንቅስቃሴ ሁሌም የሚወራለትን የአልቲቲዩድ ተጠቃሚነታችንን ጉዳይ ያስረሳም ነበር፡፡
ቡድኑ በ29ኛው ደቂቃ ገደማ ተፅዕኖ ፈጣሪ አምበሉ ኬይታን በጉዳት ቢያጣም በድንቅ አቋሙ ቀጥሎ በ34ኛው ደቂቃ ለሀገሩ የመጀመሪያውን ጨዋታ ባደረገው አብዱላዬ ዲያቢ ጎል መሪ መሆን ችሏል፡፡ ጎሉ የተቆጠረው ከግራ በኩል (ከኢትዮጲያ ቀኝ መስመር) ከተገኘ የቅጣት ምት ሲሆን ባካሪ ሳኮ ያሻገረውን ከባድ የማይባል ኳስ ነበር ብዙም ረዥም የማይባለው ዲያቢ በጭንቅላቱ ገጭቶ ያስቆጠረው፡፡ ለዚህ ጎል መቆጠር በግዴለሽነት የተሞላው ደካማ የመከላከል ተግባር ተወቃሽ ይሆናል፡፡ ከዚያም ወዲያው ቡድናችን ያገኘውን የቅጣት ምት አምበሉ አበባው ጥሩ አድርጎ ቢመታም ሳማሳ ያዳነበት ሲሆን በዚሁ እንቅስቃሴ ጌታነህ እንደገና ያደረገውን አስደናቂ የዞረ ምት (curling shot) ሙከራም ግብ ጠባቂው በድንቅ መንገድ ጎል ከመሆን አግዶታል፡፡ ይህ ቅፅበት የብሔራዊ ቡድናችን የጨዋታው ምርጡ ቅፅበት እንደነበር መግለፅ ማጋነን አይሆንም፡፡ በመጀመሪያው ግማሽ መጠናቀቂያ ላይ ጌታነህ ከናትናኤል የተሻገረለትን ኳስ በጭንቅላቱ በመግጨት ቢሞክርም ብዙም ለግብ ጠባቂው ስጋት ሳይሆን በማሊ 1ለ0 መሪነት ለእረፍት ተለያይተዋል፡፡ የመጀመሪያው ግማሽ በአጭሩ ሲገለፅ የማሊ አስደናቂ የበላይነት የታየበት፣ በሁሉ ረገድ ቡድናችን የተበለጠበት፣ እጅግ በርካታ ዓላማ-የለሽ ረዥም ኳሶች ለአጥቂዎቻችን የተላኩበት ነበር፡፡ ከተጋጣሚያችን የበላይነት አንፃርም ለእረፍት መውጣት እፎይ የሚያሰኝ ነበር፡፡
በ15ቱ ደቂቃ የእረፍት ጊዜ በስታዲየምም ሆነ በየቤታቸው ሆነው ጨዋታውን ሲከታተሉ የነበሩ ሰዎች ሁሉ መነጋገሪያ ምን ብናደርግ ጨዋታውን ለውጠን ልናሸንፍ እንችላለን የሚል ነበር፡፡ ሁሉም እንደየአመለካከቱ የየራሱን አስተያየት ቢሰጥም ቡድናችን ተሽሎ ይመለሳል የሚለው ተስፋ ግን ብዙዎችን ያስማማ ነበር፡፡ ሜዳ ላይ የታየው ግን ከመጀመሪያው አጋማሽ ብዙም የተለየ አልነበረም – በቡድናችን ተጨዋቾች መካከል የእንቅስቃሴ ህብረት እና ውህደት አልነበረም፤ ዓላማ-የለሾቹ ረዥም ኳሶች በሶስት ግዙፍ ተከላካዮች የተያዘው ጌታነህን ኢላማ አድርገው መለጋታቸውን ቀጥለዋል፤ ቦታን ጠብቆ የመጫወት እና የመተጋገዝ ችግሮች ነበሩ፡፡ የተለየው ነገር ቢኖር የማሊ ቡድን ከሜዳው ወጥቶ ተጨዋቾቻችንን አፍኖ የመጫወቱን ነገር በመጠኑ መቀነሱ እና ወደ ራሱ ጎል ማፈግፈጉ ነበር፡፡ ግን ይህም ግራ በሚያጋባ ሁኔታ ተጨዋቾቻችን ከቀድሞ አጨዋወታቸው አልመለሳቸውም፡፡ ንስሮቹ በበላይነታቸው ቀጥለው ሳሊፍ ኩሊባሊ በ53ኛው ደቂቃ በጭንቅላቱ ያደረገው ሙከራ አግዳሚውን መቶ የወጣበት ሲሆን ከጥቂት ደቂቃዎች በኋላ ወጣቱ አንዳርጋቸው በታደለ መንገሻ ተቀይሮ ወጥቷል፡፡ ከዚያም በ62ኛው ደቂቃ በእንግሊዝ ሻምፒዮንሺፕ ለዎልቭስ የሚጫወተው ባካሪ ሳኮ በግራ መስመር ቢያድግልኝን በቀላሉ አልፎ ወደኋላ ያቀበለውን ኳስ የተጎዳው ኬይታን ተክቶ የገባው ሳምቦይ ያታባሬ ወደጎልነት ቀይሮታል፡፡ ከቢያድግልኝ በቀላሉ መታለፍ በተጨማሪ የተከላካይ አማካዩ ናትናኤል ተከላካዮቹን ለማገዝ በጊዜ አለመድረሱ ለጎሉ መቆጠር እንደምክንያትነት ሊነሳ ይችላል፡፡ ከዚህ በኋላ ሜዳ ላይ ሊነሱ የሚችሉ ነገሮች ቢኖሩ ዋልያዎቹ እምብዛም ልዩነት የማይፈጥሩ ቅያሬዎች ማድረጋቸው (ዳዋ ሂቴሶ በቢያድግልኝ እና ኤልያስ ማሞ በሽመልስ)፣ የአበባው ሌላ በግብ ጠባቂ የተመለሰ የቅጣት ምት ሙከራ እና የማሊዎች ዘና ብሎ ጨዋታውን መጨረስ ናቸው፡፡ እንዲያውም በዚህ አጋማሽ ትኩረት ስቦ የነበረው በተመልካቾች ላይ የታዩ አላስፈላጊ ድርጊቶች እና ባህርያት ነበሩ፡፡ በመጀመሪያ ሁለተኛው ጎል እንደተቆጠረ የውሀ መያዣ ፕላስቲኮች ወደሜዳ የተወረወሩ ሲሆን፣ በመቀጠል በተለምዶ የኢትዮጲያ ቡና ደጋፊዎች በሚቀመጡበት ቀኝ ሚስማር ተራ አካባቢ የሀገር ጨዋታ መሆኑ ተዘንግቶ ‹‹ኢትዮጲያ ቡና አደገኛ›› የሚለው ዝማሬ እና የአንድ ሰው ውዳሴ በጭፈራ ታጅቦ ሲሰማ ነበር፡፡ ከዚያም በመጨረሻ የማሊ ተጨዋቾችን ለመሳደብ በሚመስል መልኩ የወቅቱ የዓለም መነጋገሪያ ‹‹ኤቦላ›› ጥቂት በማይባሉ ደጋፊዎች በሚሰማ ድምፅ ሲጠራ ነበር፡፡ በተለይ ይህ ብዙዎችን ያስደነገጠ እና ያሸማቀቀ፣ ቀድሞም በሌሎች አፍሪካዊያን ዘንድ ጥያቄ ውስጥ የነበረ የሀገራችንን ምስል ጥላሸት የሚቀባ ፍፁም ከስፖርታዊ ጨዋነት የራቀ ድርጊት ነበር፡፡
ከዚህ በእግር ኳሳዊም ሆኑ እግር ኳሳዊ ባልሆኑ ምክንያቶች (በተለይ በጨዋታው የመጨረሻ 30 ደቂቃዎች) ብዙዎች ኢትዮጲያዊያን በቶሎ እንዲጠናቀቅ ከተመኙለት ጨዋታ በኋላ ብቸኛው የሚጠበቅ ነገር የብሔራዊ ቡድናችን አባላት በተለይም አሰልጣኙ ማሪያኖ ባሬቶ ስለጨዋታው እና ስለሌሎች ጉዳዮች ምን ይላሉ የሚለው ጉዳይ ነበር፡፡ በዚህም መሰረት ከደቂቃዎች በኋላ በስታዲየሙ ውስጥ በሚገኘው የቀድሞው የፌዴሬሽኑ ፅህፈት ቤት ባሬቶ እና ለሀገሩ የመጀመሪያ ጨዋታውን ያደረገው ዋሊድ አታ ከጋዜጠኞች ለቀረቡላቸው ጥያቄዎች ምላሽ ሰጥተዋል፡፡
ባሬቶ ስለጨዋታው
‹‹የተጫወትነው ከጠንካራ ቡድን ጋር ነው፡፡ ተጨዋቾቼ የሚችሉትን አድርገዋል፡፡ የተጎዳነው በተለመደ ችግራችን ከቆሙ ኳሶች ነው፤ የሚያበሳጨው ያገባብን ከሁሉም ትንሹ ልጅ መሆኑ ነው፡፡ በሁለተኛው አጋማሽ ውጤቱን ለመቀየር ብናስብም እንደተለመደው በዚህ ደረጃ ልንሳሳት የማይገባ ስህተት ሰርተን ተቀጣን፡፡ ችግሮቻችንን እናውቃለን፤ በእነሱ ላይ መስራታችንን እንቀጥላለን፡፡ በማሊ ተጨዋቾች እና በእኛ ጥቂት ተጨዋቾች መሀል ሰፊ የደረጃ ልዩነት አለ፡፡ ጥሩ ተጨዋቾች አሉን፤ ልምድ እያገኙ ነው ግን ገና ነው ይቀረናል፡፡ በጨዋታው ላይ ፍፁም የተለያየ ፍጥነት ተመልክተናል፡፡ ተጨዋቾቼ የትልቅ ደረጃ እግር ኳስ ይህ እንደሆነ ሊረዱ ይገባል – ከፍተኛ ፍጥነት፣ ልምድ፣ ለእያንዳንዷ ሴንቲ ሜትር የመፋለም መንፈስ፡፡ አንድ ቀን የእኛም ተጨዋቾች ይህን ያደርጉታል፡፡ ግን ብዙ መስራት አለብን፡፡››
ባሬቶ በቡድኑ ስለተመለከቷቸው በጎ ነገሮች
‹‹ቡድን እየገነባን፣ ወጣቶች እየመጡ፣ ያለፍራቻ እየተጫወቱ ናቸው፡፡ እነአንዳርጋቸው፣ ናትናኤል እና ዳዋ ልምድ እያገኙ ናቸው፡፡ ሲጫወቱ፣ ሲለማመዱ ነው የሚማሩት፡፡ የምታድገው በልምምድ ሳይሆን በፉክክር ጨዋታዎችም ሆነ በወዳጅነት ጨዋታዎች ስትሳተፍ ነው፡፡ ለወጣቶቹ ልምድ የማግኘት እድል ካልተሰጣቸውስ እንዴት ልምድ ያገኛሉ? ከሱቅ ይገዛሉ ወይስ ከመፅሀፍ ያገኙታል? ትልልቆቹ ተጨዋቾች በዚህ ደረጃ መሮጥ አይችሉም፡፡ በወዳጅነት ጨዋታዎች እና በአልጄሪያ እና ማላዊ ጨዋታዎች ተመልክቼያቸው ነው ወጣቶቹን ለመጠቀም የወሰንኩት፡፡ እባካችሁ ለወጣቶቻችሁ እድል ስጡ፡፡ የወደፊት ተስፋዎቻችሁ እነሱ ናቸው፡፡ ስትፈልጉ እኔን ተናገሩ፡፡ እነዚህን ልጆች ካልተንከባከባችኋቸው ከሱዳን ወይ ከሞሮኮ ማምጣት አትችሉም!››
ስለቀኝ ተከላካይ ችግር
‹‹ምን ላድርግ? እንደ ክለብ አሰልጣኝ ከሌላ ቦታ መግዛት አልችልም፡፡ ያሉኝን ልምድ መስጠት እና ማሳደግ ብቻ ነው የምችለው፡፡ ለተሰራ ስህተት ሀላፊነቱን የምወስደው እኔ ነኝ፡፡ ቢያድግልኝን መረዳት ይኖርብናል፡፡ ያስወጣሁት ስላጠፋ ሳይሆን ስለደነገጠ እና ልከላከለው ስለሚገባኝ ነው፡፡››
ስለረዥም ኳሶች
‹‹እኔ ኳሶችን በረዥሙ እንዲመቱ አላዘዝኳቸውም፡፡ ከፈለጋችሁ እነሱን ልትጠይቋቸው ትችላላችሁ፡፡ በዚህ ደረጃ ጫናውን መቋቋም ስላልቻሉ እና ኳሱን ለመያዝ የሚያበቃ በራስ መተማመን ስለሚያጥራቸው ስህተት ላለመስራት ሲሉ በረዥሙ ይለጉታል፡፡ ተጋጣሚያችን በጣም ጠንካራ በመሆኑና ቀላል አማራጮችን ስላሳጣቸው ያደረጉት ተግባር ነው፡፡ ይህ የሚሻሻለው በመጫወት፣ በመስራት እና የራስ መተማመንን በማዳበር ነው፡፡››
ስለአሚን አስካር አለመግባት ምክንያት
‹‹አሚንን በቡድኔ ያላካተትኩት በቢሮክራቲክ ምክንያት ነው፡፡ ቀድሞ ለኖርዌይ ከ19 እና 20 ዓመት በታች ቡድኖች በመጫወቱ አንዳንድ ማጠናቀቅ የነበረበት የአሰራር ጉዳዮች ነበሩ፡፡ ጉዳዮቹን በጊዜ ባለማጠናቀቁ ከፊፋ የመጫወት ፍቃድ አላገኘም፡፡››
ስለቀጣይ እቅዳቸው
‹‹ኮንትራቴ ላይ ለ2015ቱ የሞሮኮ አፍሪካ ዋንጫ ካላሳለፍክ ትለቃለህ የሚል አንቀፅ የለም፡፡ የመጣሁት ለመስራት ነው፡፡ ስራዬ የሚመዘነው በአንድ ጨዋታ ሳይሆን በኮንትራት ጊዜዬ በምሰራው ነው፡፡ እናም መስራቴን እቀጥላለሁ፤ ማሻሻሌን፣ ጥቃቅን ስህተቶች እንዳይሰሩ፣ ቀላል ጎሎችን እንዳያስተናግዱ መርዳቴን እቀጥላለሁ፡፡››
ዋሊድ አታ ‹‹ከደጋፊዎች ያገኘሁት ድጋፍ በጣም አስደስቶኛል››
በኢትዮጲያ እና ማሊ ጨዋታ ከታዩ ጥቂት ተስፋ ሰጪ በጎ ነገሮች አንዱ በስዊድን ቢኬ ሀከን ክለብ የሚጫወተው እና ለኢትዮጲያ ብሔራዊ ቡድን የመጀመሪያ ጨዋታውን ያደረገው የዋሊድ አታ ብቃት ነበር፡፡ በአንዴ የደጋፊው ተወዳጅ ተጨዋች መሆን የቻለው የመሀል ተከላካይ ለጋዜጠኞች አጠር ያለ ቃሉን ሰጥቷል፡፡
‹‹እዚህ በመገኘቴ ደስ ብሎኛል፡፡ ወደ አዲስ አበባም ሆነ ወደ ኢትዮጲያ ስመጣ የመጀመሪያ ጊዜዬ ነው፡፡ እዚህ ለመገኘት ረዥም ጊዜ ጠብቄያለሁ፡፡ እድሉን በማግኘቴም ተደስቻለሁ፡፡ ጨዋታውን ያደረግነው በጣም ጥሩ ከሆነ ቡድን ጋር ነው፡፡ በአካል ብቃት፣ ተጭኖ በመጫወት ጠንካሮች ናቸው፡፡ ከጎሉ በኋላ በአእምሮ ረገድ ወደጨዋታው ለመመለስ ተቸግረናል፡፡ አዲስ እና ወጣት ቡድን እንደመሆኑ የምንችለውን ሁሉ አድርገናል፡፡ ብዙ ኳሊቲ፣ ወጣት ተጨዋቾች አሉ፡፡ አሁን ስላለፈው ትተን ስለወደፊቱ ማሰብ ይኖርብናል፤ ጠንክረን መስራት ይኖርብናል፤ በራሳችን ማመን ይኖርብናል፡፡ ብሩህ ጊዜ እንደሚጠብቀንም ይሰማኛል፡፡ በግሌ ግን ከደጋፊዎች ያገኘሁት ድጋፍ በጣም አስደስቶኛል፡፡››
Articles
በኦስሎ ዳይመንድ ሊግ የ5000ሜ ፉክክር ኢትዮጵያውያን አትሌቶች በሁለቱም ፆታዎች በአሸናፊነት አጠናቀዋል

ትላንት ምሽት በኖርዌይ ኦስሎ በተከናወነው የዳይመንድ ሊግ 5000 ሜ. ውድድር ኢትዮጵያውያን አትሌቶች በወንዶችም በሴቶችም ከአንደኛ እስከ ሶስተኛ ያሉትን ደረጃዎች በመቆጣጠር አሸንፈዋል፡፡ በዝናባማ የአየር ሁኔታ ውስጥ በተካሄደው የሴቶች 5000 ሜትር ፉክክር ዳዊት ስዩም በመጨረሻዎቹ መቶ ሜትሮች ውስጥ ፍጥነቷን በመጨመር ጉዳፍ እና ለተሰንበትን ቀድማ አንደኛ ወጥታለች፡፡ የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ለኦሪገን 2022 የአለም ሻምፒዮና ከመረጣቸው ዕጩ አትሌቶች ዝርዝር ውስጥ ያልተካተተችው ዳዊት በኦስሎ ያሸነፈችበት 14፡25.84 የሆነ ሰአት የራሷ ምርጥ ሲሆን እጅጋየሁ ታዬ (14.12.98) እና ለተሰንበት (14፡24.59) ባለፈው ወር በዩጂን ካስመዘገቧቸው በመቀጠልም የዘንድሮ የአለም ሶስተኛው ፈጣን ነው፡፡ በውድድሩ ላይ ከነበሩት ሌሎች ኢትዮጵያውያን መካከል በዘንድሮው የውድድር ዓመት በርቀቱ የመጀመሪያ ተሳትፎዋን ያደረገችው አልማዝ አያና በ14:32.17 ስድስተኛ ሆና አጠናቃለች፡፡ ሀዊ ፈይሳ በ14:33.66፣ ፅጌ ገብረሰላማ በ14:43.90፣ እና አበራሽ ምንሴዎ በ14:47.98 በቅደም ተከተል ሰባተኛ፣ አስረኛ እና አስራ አንደኛ ሆነው ሲያጠናቅቁ ሶስቱም ያስመዘገቡት ሰዓት የራሳቸውን ምርጥ ያሻሻሉበት ሆኗል፡፡ ጥሩነሽ ዲባባ እ.ኤ.አ. በጁን 2008 ዓ.ም. ያስመዘገበችውና 14:11.15 የሆነው የኦስሎ ዳይመንድ ሊግ የሴቶች 5000 ሜትር የውድድር ስፍራ ሪከርድ ይሰበራል ተብሎ ተጠብቆ የነበረ ቢሆንም ሳይሳካ ቀርቷል፡፡

ዳዊት ስዩም ውድድሩን በድል ካጠናቀቀች በኋላ ለውድድሩ አዘጋጆች በሰጠችው አስተያየት ‹‹ዛሬ ለእኔ ደስታን ስላመጣልኝ በውድድሩ ሰዓት የነበረውን ዝናብ ወድጄዋለሁ ማለት እችላለሁ፡፡ ጠንካራ ተፎካካሪዎች የነበሩበት ከባድ ውድድር ነበር እናም ሁሉንም ለማሸነፍ በቅቻለሁ። በርቀቱ የራሴን ምርጥ ሰዓት ማሻሻል መቻሌም አስፈላጊ ነበር፡፡ በስታድየሙ ውስጥ በከፍተኛ ስሜት ድጋፍ ይሰጡን የነበሩ ወገኖቻችን ነበሩ። ለሰጡን ድጋፍ እናመሰግናለን።›› ብላለች፡፡ በኦስሎ የወንዶች 5000 ሜትር የመጨረሻ ፉክክሩ በኢትዮጵያውያኑ ጥላሁን ሀይሌ እና ሳሙኤል ተፈራ መካከል የነበረ ሲሆን ጥላሁን የ1500 ሜትር ስፔሻሊስቱ ሳሙኤልን በአጨራረስ ፍጥነት ቀድሞ በ13:03.51 በአንደኛነት አጠናቋል፡፡ ሳሙኤል ተፈራ የራሱ ምርጥ በሆነ 13:04.35 ሁለተኛ ሲወጣ ጌትነት ዋለ የግሉ የዓመቱ ምርጥ በሆነ 13:04.48 ሶስተኛ ደረጃን ይዞ ጨርሷል። በውድድሩ ላይ የነበሩት ሌሎች ኢትዮጵያውያን ሚልኬሳ መንገሻ በ13:05.94 አምስተኛ እንዲሁም አሊ አብዱልመናን የራሱ ምርጥ በሆነ 13:16.97 አስረኛ ወጥተዋል፡፡

ጥላሁን ሀይሌ ውድድሩን በአሸናፊነት ካጠናቀቀ በኋላ ለውድድሩ አዘጋጆች በሰጠው አስተያየት ‹‹ሶስት ኢትዮጵያውያን የመጀመሪያዎቹን ሶስት ደረጃዎች ይዘን መጨረስ መቻላችን ጥሩ አፈጻጸም ነበር። እየጠነከርኩ እንደሆነ የተሰማኝ ሲሆን በውድድሩ እና ባስመዘገብኩት ሰዓትም ተደስቻለሁ። ለረጅም ጊዜ ጉዳት ላይ ስለነበኩ ወደ አሸናፊነቱ መመለስ መቻሌ በጣም ጥሩ ነው።›› ብሏል፡፡
በኦስሎ የሴቶች 800ሜ. ውድድር ላይ ተፎካካሪ የነበረችው ኢትዮጵያዊቷ ድሪቤ ወልቴጂ በ1፡58.69 አምስተኛ ሆና አጠናቃለች።
Articles
የዘንድሮው የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ብሄራዊ ሻምፒዮና በእኔ እይታ

ከመጋቢት19-24/2014 ዓ.ም በሐዋሳ አለም አቀፍ ስቴድዮም የተደረገው 51ኛዉ የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ሻምፒዮና ከሞላ ጎደል ስኬታማ በሚባል ሁኔታ ተጠናቋል፡፡ ከአምስት አመት በኋላ በድጋሚ በአካል በመገኘት ስለተከታተልኩት የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ሀገር አቀፍ ሻምፒዮና የግል ምልከታዬን እንደሚከተለው አጠናቅሬዋለሁ፡፡ የበለጠ ትኩረትን በሳቡት ውድድሮች ዙሪያ የተመዘገቡ ውጤቶችን በወፍ በረር በመዳሰስ ስጀምር ከፍተኛ ፉክክር በታየበት የመጨረሻ ቀን የወንዶች 5000ሜ. የአለም ከ20 አመት በታች ሻምፒዮና የ3000ሜ የብር ሜዳልያ አሸናፊው አሊ አብዱልመና 13፡45.0 በሆነ ሰዓት ከጥላሁን ሀይሌ፣ ጌትነት ዋለ እና ዮሚፍ ቀጄልቻ ቀድሞ አሸናፊ ሆኗል፡፡ የፉክክሩ አካል የነበረው እና የርቀቱ የወቅቱ የአለም ሻምፒዮን ሙክታር እድሪስ ስድስተኛ ወጥቷል። ከ20 ዓመት በታች የ3000ሜ የአለም ሻምፒዮኑ ታደሰ ወርቁ በ28፡12.0 የወንዶች 10,000ሜ. ሻምፒዮን ሲሆን በ1996 ዓ.ም. በአትሌት ስለሺ ስህን ተመዝግቦ የነበረውን 28፡16.23 የሆነ የሻምፒዮናው ሪኮርድ ለማሻሻልም በቅቷል፡፡ በ10 ሺህ ሜትር የሴቶች ፉክክር ግርማዊት ገብረእግዚአብሔር በቀዳሚነት የጨረሰችበት 31፡21.5 የሆነ ሰዓት አዲስ የሻምፒዮንሺፕ ሪኮርድ ሆኖ ተመዝግቧል፡፡ በርቀቱ የከዚህ ቀደሙ ሪኮርድ ለተሰንበት ግደይ ከሶስት ዓመት በፊት ያስመዘገበችው 32፡10.13 የሆነ ሰዓት ነበር፡፡ ሳሙኤል ፍሬው በዘንድሮ የወንዶች 3000ሜ. መሰናክል አፈፃፀም ከአለም ሁለተኛው ፈጣን በሆነ 8፡22.5 ሰዓት አሸናፊ ሲሆን ጌትነት ዋለ ከአራት ዓመት በፊት አስመዝግቦት የነበረውን 8፡28.98 የነበረ የሻምፒዮናው ሪኮርድም አሻሽሏል፡፡ በሴቶች 3000ሜ. መሰናክል ከ800ሜ ወደ ረጅም ርቀት የተሸጋገረችው ወርቅውሃ ጌታቸው በ9፡41.8 ሰዓት መቅደስ አበበን (9:43.8) በማስከትል በአሸናፊነት አጠናቃለች። አድሃና ካህሳይ (3:51.0) የወንዶች 1500ሜ ፉክክሩን በበላይት ሲያጠናቅቅ በሴቶች 1500 ሜ አያል ዳኛቸው (4:10.0) ተጠባቂዋ ዳዊት ስዩምን (4:11.1) በመቅደም በአንደኛነት አጠናቃለች። በ800ሜ. ወንዶች ቶሌሳ ቦደና (1:47.1) በሴቶች ወርቅነሽ መሰለ (2:02.1) አሸናፊ ሆነዋል። ዮብሰን ብሩ በ400ሜ/400ሜ መሰናክል (45.9/50.5) ድርብ ድል ሲቀዳጅ፣ በወንዶች ጦር ውርወራ ኡታጌ ኡባንግ ብሔራዊ ሪኮርድ በሆነ 73.28ሜ. አሸንፏል፡፡ የኋልዬ በለጠው እና ዮሃንስ አልጋው በእርምጃ ሩጫ የሻምፒዮንነት ክብርን ተቀዳጅተዋል። ጥቂት አስተያየቶች፡- የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ስፖርት አፍቃሪ እንደሆነ እና ለዕድገቱ እንደሚቆረቆር ሰው በብሔራዊ ሻምፒዮናው ላይ ስለተመለከትኳቸው አዎንታዊ እና አሉታዊ ጎኖች ጥቂት አስተያየቶቼን እንደሚከተለው አስቀምጣለሁ፡- አዎንታዊ ጎኖች • ባለው ነባራዊ ሁኔታ ውስጥ ሊገጥሙ የሚችሉትን ተግዳሮቶች በሙሉ በመቋቋም ፌዴሬሽኑ ውድድሩን ከአዲስ አበባ ውጭ አካሂዶ በሰላም ማጠናቀቅ መቻሉ አንደኛው ስኬቱ ነው፡፡ • በሻምፒዮናው ላይ ጥቂት የማይባሉ ታዋቂ አትሌቶች በሀገሪቱ ትልቁ የአትሌቲክስ ፉክክር ላይ ተሳታፊ ሆነው ሲወዳደሩ መመልከት የተቻለ ሲሆን በተለይም በወንዶች 5000 ሜትር ፍፃሜ ላይ የታየው የኮከብ አትሌቶች ፉክክር ልዩ ነበር፡፡ • በውድድሩ ወቅት ለአትሌቲክስ ዳኞች የብቃት ማሻሻያ ስልጠና መሰጠቱም የውድድሩን ጥራት ለማሳደግ የሚረዳ እንደመሆኑ እሰየው የሚባል ነው፡፡ • እንደ ኢትዮ ኤሌክትሪክ ያሉት ክለቦች ለአትሌቲክስ ስፖርት የበለጠ ትኩረት በመስጠትና ተጠናክሮ በመቅረብ ከዚህ ቀደም በጠንካራነታቸው ከሚታወቁት መከላከያ እና ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ጋር የቅርብ ተፎካካሪ ሆነው መታየት፤ የኦሮሚያ ክልል፣ ደቡብ ፖሊስ እና ሲዳማ ቡና ክለብ አትሌቶችም ጠንካራ ተሳትፎ ሳይዘነጋ የሻምፒዮናው ፉክክር ድምቀት ነበሩ፡፡ • የአንዳንዶቹ ተገቢነት አጠያያቂ ቢሆንም ብዛት ያላቸው የሻምፒዮናው ሪኮርዶች የተሻሻሉበት ውድድርም ነበር፡፡ አሉታዊ ጎኖች • የሀገሪቱ ትልቁ የአትሌቲክስ ውድድር ውጤት አሁንም በኤሌክትሮኒክስ የሰዓት መቆጣጠሪያ የማይደገፍ መሆኑ በተለይም በአጭር ርቀት እና በሜዳ ላይ ተግባራት ውድድሮች ላይ የሚሳተፉ አትሌቶች ልፋት ተገቢውን እውቅና እንዳያገኝ እያደረገ ይገኛል፡፡ የሻምፒዮናውን ውጤቶች በዘመናዊ እና ዓለም አቀፉን መለኪያ በሚያሟላ መልኩ አለመያዝ በአህጉራዊ እና አለም አቀፋዊ ውድድሮች ላይ ለተሳትፎ የሚያበቁ ውጤቶችን በማስመዝገቡ ረገድ የሚኖረው አሉታዊ ተፅዕኖ ከፍተኛ መሆኑ ከግምት ውስጥ ገብቶ አሁንም መፍትሄ ያልተበጀለት ጉዳይ ነው፡፡ • የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ወደ ሚዲያ/ለአጠቃላዩ ሕዝብ የሚያስተላልፈው የመጀመሪያዎቹን ሶስት ደረጃዎች ይዘው የሚያጠናቅቁ አትሌቶችን ውጤት ብቻ መሆኑ አወዳዳሪው አካል የሚያደርገውን የራሱን ውድድርም ሆነ አትሌቶቹ የለፉበትን ውጤት ከማስተዋወቅ አኳያ በቂ አይደለም፡፡ • በወንዶች የጦር ውርወራ እና የሴቶች ምርኩዝ ዝላይ ብሔራዊ ሪኮርዶች እንደተመዘገቡ ይታመናል፤ በሴቶች 100ሜ መሰናክል እና የወንዶች 400ሜ መሰናክል የተመዘገቡት ሰዓቶችም የምንግዜውም ፈጣን ሊሆኑ ይችላሉ፡፡ ነገር ግን ውድድሩ በኤሌክትሮኒክስ ታይሚንግ ያልተደገፈ እና የንፋስ ንባብ ያልነበረው መሆኑ ውጤቶቹ በዓለም አቀፍ ደረጃ ተቀባይነት እንዳይኖራቸው የሚያደርግ ነው። • በ20 ኪ.ሜ የእርምጃ ውድድር ላይ በሁለቱም ፆታዎች የተመዘገቡት ሰዓቶች ከሚጠበቀው በላይ እጅግ በጣም ፈጣን እና እውነታዊ አለመምሰላቸው በውድድሩ ላይ የተፈጠረ አንዳች ስህተት መኖሩን የሚያመላክቱ መሆኑ፡፡ እንዲህ አይነት ለማመን የሚከብዱ እና ጥርጣሬን የሚፈጥሩ አይነት ውጤቶች ሲመዘገቡም የተፈጠረ ስህተት መኖር አለመኖሩን ለማጣራት አለመሞከሩ፡፡ • የሴቶች 10 ኪሎ ሜትር ውድድር ላይ ለውድድር የማይፈቀድ የጎዳና ላይ መሮጫ ጫማን በመጠቀም የተመዘገበ ውጤት በሪኮርድነት ጭምር ተይዞ መፅደቁ። ብሔራዊ ፌዴሬሽኑ ከተከለከሉ ጫማዎች ጋር የተያያዙ ዓለም አቀፍ ሕገ ደንቦችን ማወቅና መተግበር ቢገባውም በሴቶች 10 ሺህ ሜትር ውድድር ላይ የተከሰተው ነገር የውድድር ሕገ ደንቦቹ መረጃ በፌዴሬሽኑ ውስጥ በትክክል የተሰራጩ እንዳልሆነ የሚያመላከት ነው፡፡ • በሴቶች 1500 ሜትር የግማሽ ፍፃሜ ውድድር ላይ አትሌት ዳዊት ስዩም የሻምፒዮናውን ሪኮርድ ያሻሻለችበት ውጤት እንደተመዘገበ በውድድሩ ወቅት በተደጋጋሚ ሲነገር ከተደመጠ በኋላ ግልፅ ባልተደረገ ምክንያት ውጤቱ በሐዋሳው ውድድር ላይ ተሻሻሉ ከተባሉት የሻምፒዮናው አዲስ ሪኮርዶች ዝርዝር ውስጥ ሳይካተት መቅረቱም የፌዴሬሽኑን ግልፀኝነት ጥያቄ ምልክት ውስጥ የሚከት ነው፡፡ ከላይ የተዘረዘሩት አዎንታዊ እና አሉታዊ ጎኖች ለረጅም ግዜ የኢትዮጵያን አትሌቲክስ ስፖርት እንቅስቃሴዎች በቅርበት ከመከታተሌ አንፃር በራሴ እይታ ያስቀመጥኳቸው እንደመሆናቸው አንዳንዶቹ ሀሳቦች አከራካሪ ሊሆኑ ይችላሉ፡፡ ሆኖም የውድድር ደንቦችን በአግባቡ ከማስፈፀም አኳያ በታዩት ክፍተቶች ዙሪያ ምንም የሚያከራክር ጉዳይ ስለሌለ በወቅታዊ የውድድር ደንቦች ዙሪያ የግንዛቤ እጥረት ላለባቸው የስፖርቱ ባለድርሻ አካላት በሙሉ አስፈላጊውን ገለፃ እና ትምህርት መስጠት የፌዴሬሽኑ ኃላፊነት ነው፡፡ ከውድድር ጋር የተያያዙ ደንቦችን ከመጣስ አኳያ በሀገር ውስጥ በሚደረጉ ውድድሮች እንደቀላል ነገር የሚታለፉ ጉዳዮች በዓለም አቀፍ ውድድሮች ላይም ተደግመው እንደግል አትሌቶችን እንደቡድን ሀገርን ትልቅ ዋጋ ሊያስከፍሉ ይችላሉና አስፈላጊው ጥንቃቄ ቢደረግ መልካም ነው፡፡ ባለፈው መስከረም ወር በቪየና ሲቲ ማራቶን ውድድሩን በአሸናፊነት ጨርሶ የነበረው ኢትዮጵያዊው ደራራ ሁሪሳ የገጠመውን አንዘንጋው! ሀገራችን ኢትዮጵያን በመልካም ጎኑ ስሟ እንዲነሳ በሚያደርገው እና በትልልቅ ዓለም አቀፍ የውድድር መድረኮች ላይ የኩራታችን ምንጭ በሆነው የአትሌቲክስ ስፖርት እንደጎረቤታችን ኬንያ ዓለም አቀፍ ውድድሮችን የማስተናገድ የብቃት ደረጃ ላይ ደርሰን ማየት የዘወትር ምኞቴ ነው፡፡ የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌደሬሽንም የውድድሮቹን ጥራት ለማሻሻል በትኩረት እንደሚሰራ ተስፋ አደርጋለሁ።
በመጨረሻም በሀዋሳ በተካሄደው 51ኛዉ የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ሻምፒዮና ከመሮጫ ጫማ ጋር የተያያዙ ደንቦችን በማስከበሩ ረገድ የተፈጠረውን ክፍተት እንደማስተማሪያ ብንጠቀምበት በሚል የሚከተለውን ለማለት ወደድኩ፡-
የመሮጫ ጫማ ደንቦች ለትራክ ውድድር
64 ደቂቃ ከ14 ሰከንድ በሆነ ሰዓት የዘንድሮ የራስ አል ካይማህ የግማሽ ማራቶን ውድድር አሸናፊ የሆነችው ግርማዊት ገብረእግዚአብሔር በሐዋሳ በተከናወነው 51ኛው የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ሻምፒዮና ላይ 31 ደቂቃ ከ21.5 ሰከንድ በመግባት የ10,000ሜ. አሸናፊ ሆናለች፡፡ የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽንም ዓለም አቀፉን ደንብ ከግምት ባላስገባ ሁኔታ ውጤቱን በአዲስ የሻምፒዮንሺፕ ሪኮርድነት ጭምር አፅድቆት አልፏል፡፡ ይሁን እንጂ መጋቢት 20/2014 በተደረገው የሴቶች የፍፃሜ ፉክክር ላይ በኢትዮጵያ ምድር የተመዘገበ የምንግዜውም ፈጣን የሴቶች 10 ሺህ ሜትር ሰዓት የሆነው ውጤት በአለም አትሌቲክስ ዘንድ እውቅና ሊሰጠው የማይችል ነው።
● ለምን?
አትሌቷ የሶል ውፍረቱ 40ሚሜ የሆነ ዙምኤክስ ቬፐርፍላይ (ZoomX Vaporfly) ጫማ አድርጋ በመወዳደሯ ምክንያት።
● ደንቡ ምን ይላል?
በትራክ ውድድሮች ላይ የሚፈቀደው ከፍተኛው የሶል ውፍረት ፡-
– 20ሚሜ ከ 800ሜ በታች ለሆኑ ውድድሮች እና ለሁሉም የሜዳ ላይ ተግባራት (ከስሉስ ዝላይ በስተቀር)
– 25ሚሜ ለ800ሜ እና ከዛ በላይ ለሆኑ ውድድሮች እንዲሁም ለስሉስ ዝላይ
– 40ሚሜ ለትራክ ላይ የእርምጃ ውድድሮች
እነዚህ ደንቦች እ.ኤ.አ. እስከ ኦክቶበር 31, 2024 ድረስ በሥራ ላይ ይውላሉ። ከኖቬምበር 1 ቀን 2024 ጀምሮ ለ800ሜ እና ከዚያ በላይ ለሆኑ ውድድሮች እንዲሁም ለስሉስ ዝላይ የሚፈቀደው ከፍተኛ የሶል ውፍረትም ወደ 20 ሚሜ ዝቅ የሚል ይሆናል።
● የትራክ ላይ መወዳደሪያ ስፓይክ ጫማ ከሌለኝስ?
ደንቡ የጎዳና ላይ የመሮጫ ጫማዎች በትራክ ላይ እንዳይደረጉ አይከለክልም ነገር ግን በ25 ሚሊ ሜትሩ ገደብ ምክንያት 30 ሚሜ ወይም 40 ሚሜ የሆኑ የጎዳና ላይ መሮጫ ጫማዎች በትራክ ውድድሮች ላይ እንዲደረጉ አይፈቅድም፡፡
● ለበለጠ መረጃ :-
https://www.worldathletics.org/news/press-releases/new-athletic-shoe-regulations-approved-2022
Opinions
On the TPLF’s Love Affair With ‘Genocide’

Today, the joint investigation report by the Ethiopian Human Rights Council and the UNHR
on human rights violations committed in Tigray concluded that there is no evidence that genocide has taken place so far. While this is a bit of a setback for the TPLF, which has wanted the world to believe—since the 1990s, even as the TPLF was dominating power in Addis—that a genocide has been perpetrated against the people of Tigray, unfortunately the group still appears to be determined to make genocide a reality. This is confusing for people who don’t understand why the TPLF is obsessed with genocide, why its internet cadres began using #TigrayGenocide in April 2020, months before the war began. So many weapons have been deployed in this war, and among them: confusion and obfuscation.
In the past several months and more so in the past few weeks, we have been getting
testimony after testimony from allied Amhara forces fighting the TPLF that Tigrayan residents of cities in Wollo have been collaborating with the TPLF by a) attacking ENDF and allied forces from behind; b) forcing ENDF and allied forces to withdraw from towns and cities afraid of committing large scale massacres by firing back at the civilians (Tigrayans) firing at them; c) helping the TPLF locate and execute young Amharas believed to be a threat; and d) in at least one horrifying account by an IDP who managed to escape occupied territories, handing TPLF soldiers a list of women to rape. Another shocking development in the past several months has been the widespread use of child soldiers by the TPLF, which, according to experts who have studied the practice, is an “alarm bell” calling attention to possible plans to commit mass atrocities. The use of child soldiers by the TPLF and its attendant implications, along with the widespread deployment of civilian sleeper agents in Amhara cities the TPLF has taken over, serves to create an overall perception of every Tigrayan as a potential enemy, sowing fear and mistrust.
Many Ethiopians are looking at this and wondering: why are Tigrayan elites on the internet
either celebrating the TPLF’s advance via these toxic methods or silent about all this? How can they not see how dangerous this is for everyone, especially for Tigrayans who live outside Tigray? How can they not see that there is no “winning” after stoking all this lasting animosity? Do Tigrayan elites not understand that there can be no justice for Tigray—whether Tigray secedes or not—unless there is justice for her neighbors, for Tigray does not exist in a vacuum? The questions are being asked but nobody is answering them. Our academic class has largely failed to offer viable analyses of the ideas driving this war, as they failed over the past fifty years in regards to coming up with a fitting paradigm for understanding Ethiopia’s unique situation.
Here is my humble attempt to explain what I think is happening with the TPLF’s obsession
with—and with its active attempt to inspire—genocide:
The most successful psychopaths in any field understand that, in order to win anything, one
must risk everything, including the very thing one is supposedly fighting for. In the case of the
TPLF (and associated Tigrayan political elites), whose motto appears to be “give me supremacy or give me death,” that “everything” they are risking is the lives of ordinary Tigrayans in whose names they are fighting. We have seen over the past several months the extent to which the TPLF is willing to go to sacrifice ordinary Tigrayans in order to get what it wants: wave after wave after wave of young poorly armed and inexperienced Tigrayans were unleashed upon ENDF and Amhara and Afar forces in order to force the latter to waste ammunition and energy before the more experienced soldiers are sent.
So, for a political group who sends tens of thousands, if not hundreds of thousands, of
young Tigrayans towards open fire, violence against hundreds of thousands of Tigrayans is nothing if it means the TPLF will in the end win the “prize” it has been obsessed with for decades: genocide. You see, merely attaining power in Addis Ababa is not enough for the TPLF, whose core driving ideology is Tigrayan supremacy. Power is temporary; anybody can take it away from you, and the 2018 uprisings demonstrated that. Genocide is forever. Nobody can take away from you the story of genocide committed against your people.
The TPLF looked at countries like Israel and Rwanda and realized what a potent instrument
genocide is for establishing perpetual minority rule. We have some indications suggesting that the TPLF views Israel as a model. When the war between Ethiopia and the TPLF began in November 2020, Sekoutoure Getachew, a TPLF official, went on TV to tell us that the TPLF’s decision to launch a preemptive attack on the Northern Command was inspired by how the young state of Israel, feeling threatened by her neighbors, launched preemptive attacks against them in the “six-day war” of 1967. Another indication is the manner in which the TPLF, during its 27 years in power, invested heavily in creating a wealthy and strongly networked Tigrayan diaspora which has been used to lobby and influence western governments and organizations much in the same way as the Jewish diaspora aids the state of Israel. The TPLF has figured out that truth does not matter in politics, especially in international politics. If you have the wealth and the personnel to peddle your preferred narrative, if you have the military power to subdue the people you want to subdue, if you are willing to make concessions to external forces (US, Egypt, etc), you can do unspeakable things to others (much like the state of Israel does to Palestinians) and still manage to portray yourself as the victim.
This calculation is so far working for the TPLF, but nothing would seal the deal like the actual
commission of genocide—or something that looks like it—against Tigrayans. As we have seen over the past twelve months, western governments and organizations have shown their willingness to adopt TPLF’s narratives without scrutiny and can easily reward the TPLF with its much pursued prize, genocide, even if actual genocide doesn’t take place.
But why does the TPLF need genocide to establish minority rule? Because, as we saw in their
first tenure in power, you can only rule with an iron fist for a limited period of time. Leaders of the TPLF are adherents of Tigrayan supremacy: the idea that Tigrayans, as the “only” heirs of the Axumite empire, are the natural rulers of the Ethiopian state, and cannot be ruled by “barbarians” south of them. The only acceptable power arrangement for the TPLF is one in which Tigrayans are either directly dominating political power or are the perpetual kingmakers pulling all the major strings. Anything outside that, any system that forces Tigrayans to live on equal footing with everyone else, is unacceptable. And this kind of domination by a minority cannot coexist with a democratic system that the majority of Ethiopians clearly prefer. So, the TPLF needs something more potent than pure political/economic/military power to justify bypassing democracy to establish itself as the permanent ruler/kingmaker of Ethiopia. It needs a new and powerful raison d’être to justify its domination not just to Tigrayans and the rest of Ethiopians but, and most importantly, to the rest of the world. If a genocide were to be committed against Tigrayans (or if the U.S. decides to reward the TPLF with the genocide label even in the absence of it), then the TPLF can license itself to impose all manner of drastic measures aimed at “protecting Tigray and
Tigrayans.” This could be anything from redrawing internal borders (and taking debilitating
measures against the peoples whose lands are being robbed—most likely Amharas and Afaris—so that they will never be in a position to assert themselves) to ethnic cleansing and genocide against populations considered to be a threat. And when you oppose it, the TPLF will say “you committed a genocide against Tigrayans” over and over and over, and its western backers will repeat the same chorus. If they have been this loud over a non-existent genocide over the past twelve months, just imagine what it would be like if the U.S. or UN rewards them with that label.
And this is where the Ethiopian government’s major dilemma comes from: if ENDF and
Amhara forces fight to regain their cities and towns, they risk committing large scale massacres. The TPLF networks reported to be operating within these cities wear civilian clothing and fire at the armies from inside civilian establishments, in an apparent attempt to set up pro-Ethiopia forces. Pro-Ethiopia forces are essentially being dared to commit large scale massacres in order to win back their own cities. So far, they are choosing to withdraw from these towns and cities. But that is another problem: not only is the TPLF committing unspeakable violence against civilians and destroying infrastructure in those cities, the takeovers are emboldening it to continue pressing, giving young people back in Tigray false hope that they are winning and—this is very important—the false idea that they are being “welcomed” by locals in those cities. Then more and more and more young Tigrayans are sent to their deaths.
So the Ethiopian government is stuck between a rock and a hard place. One option is
allowing its forces to do whatever it takes to take back territory, thereby offering protection to its citizens in Wollo and elsewhere, but also risking the “genocide” label by western governments who have been eagerly waiting for such an opportunity so that they can blackmail the government into submitting itself to their wishes on GERD and other issues. Option two is avoiding large scale violence and allowing the TPLF to take power in Addis Ababa and do to Ethiopia what it wishes. One of the things it might do to Ethiopia, according to its leaked strategy document, is force a confederation that will no doubt privilege some states, i.e. Tigray, more than others, and that will no doubt be designed to subdue some populations—mainly Amharas and Afaris—who are considered obstacles to Tigray’s aspirations of domination and expansion (in the TPLF’s original manifesto, Afar is claimed as Tigray land).
And there is absolutely no doubt that the TPLF will make big concessions on the GERD in
order to compensate its western and Egyptian backers, if not redraw borders to make Benishangul Gumuz Tigrayan territory. If you think this is wild, read about the history of the state of Israel, the TPLF’s model state. The redrawing of borders that the TPLF undertook in 1991 was also wild at the time; people don’t think of it as outrageous anymore because the fact that they held onto the territory for 30 years has normalized the event in our minds. And that’s all the TPLF needs: another thirty years to normalize all the outrageous things they will do next.
One may argue that this is a false dichotomy, that there is a third or even maybe fourth option: winning these cities back without mass violence much in the same way the ENDF managed to do during its first campaign in Tigray. We all should pray for such a miracle, of course. However, one can also say that in the early days of the war, the TPLF was mostly withdrawing from Tigrayan cities to avoid urban warfare. And even when they engaged in urban warfare, it was not at the same scale and intensity as has been the case over the past four and half months or so. Starting in mid June, the TPLF’s use of civilians as human shields and fighters stopped being just another weapon in its arsenal and became a center of its operations. The near collapse of the ENDF inside Tigray right before its withdrawal was precipitated by the TPLF’s intensified use of “civilians” to trap the ENDF. Many ENDF soldiers chose to surrender rather than fire at those “civilians.” It is still possible to avoid large scale violence in the attempt to retake towns in Wollo, but the risk for it is very high, and is possibly behind the federal government’s reluctance to take decisive actions.
The point is: barring miracles, the Ethiopian government is positioned to lose something
one way or another. All that is left is choosing its preferred poison. Perhaps one thing to consider for the federal government is: the rights of Amharas and Afaris to defend themselves against the existential threats posed against them by the TPLF is much bigger than the national government’s concerns about its place and relationships with the rest of the world. If the federal government decides to risk the disintegration of Ethiopia, like it has done so far either due to incompetence or severe fear of committing large scale violence, that is fine for the federal government. But when you allow that disintegration to happen, please don’t leave the people of Amhara and Afar in a vulnerable position, unable to defend themselves and their lands. If we must return to the State of Nature, at least give these two peoples, who have so far shed more blood than anyone else in defense of their country, a chance to preserve their lives and their lands. Give them the resources they need to defend themselves before it is too late for them even if you feel it is too late for Ethiopia. Anything less is just a continuation of the gross criminal negligence that the federal government has been guilty of so far.
-
EBS Mogachoch9 years ago
[New] EBS Drama Series – Mogachoch : ሞጋቾች | Episode 7
-
Articles9 years ago
Ethiopia’s renewable energy revolution shouldn’t fail to empower its poor
-
News2 years ago
መንግሥት ከሕወሓት ይልቅ ለአገሪቱ ሥጋት የሆኑ ሌሎች ችግሮች አሉብኝ አለ
-
Opinions2 years ago
On the TPLF’s Love Affair With ‘Genocide’
-
Music4 years ago
2019 ESFNA Atlanta: Ethiopian Day – Ethiopia Hagerachin : ኢትዮጵያ ሀገራችን
-
Music4 years ago
2019 #ESFNA Atlanta: Ethiopian Day | Neway Debebe – Hageren Alresam : ሀገሬን አልረሳም
-
Articles8 years ago
ሰበር ዜና፦ ተዋናይት ሰብለ ተፈራ (ትርፌ) በመኪና አደጋ ህይወቷ አለፈ
-
Bahilawi Zefenoch10 years ago
Bahilawi Zefenoch – ባህላዊ ዘፈኖች
Anonymous
October 16, 2014 at 7:35 am
metagese aleben wegen
Anonymous
October 14, 2014 at 8:23 am
pls remove barito from his position and substitute by sewnet.
Anonymous
October 13, 2014 at 12:26 pm
please, be patient, good team would not be created over night. Do not repeat the mistakes made during the previous white coach who enable our young team to take part for the competition of world youth champion in history of Ethiopia. As we started now, we kept shouting and that great man was made to leave the team he was coaching as well the country. We should not act like children. We need to think twice and more before posting the wrong issues
Teferi Demie
October 13, 2014 at 12:01 pm
please Ethiopian foot ball federation think for Ethiopian people; who is the lover of his country I’m sorry for your activity !but I’m happy for Wald Ata He is the only person for Ethiopia with a lot of his class mate more of them are not in the position of Ethiopian people!!!!!!!!!!!!!!!!!
Anonymous
October 13, 2014 at 11:56 am
please Ethiopian foot ball federation think for Ethiopian people; who is the lover of his country I’m sorry for your activity !but I’m happy for Wald Ata He is the only person for Ethiopia with a lot of his class mate more of them are not in the position of Ethiopian people!!!!!!!!!!!!!!!!!
ASHENAFI
October 13, 2014 at 10:37 am
KESUMALE KESUDAN GAR TECHAWTO MALEF ADELEM KUMNEGERU!
DO YOU REMEMBER BURKINAFASO, NIGERIA, … THINK TWICE BEFORE POSTING ANY COMMENTS. IF YOU VIEW HOW OLD THIS GENERATION IS,THIS IS A GENERATION IN PROGRESS,
Ayele G/tsadik
October 13, 2014 at 9:37 am
Mr coach , Please refer previous history of our country foot ball, the history show you beautiful foot ball ,commitment hard working . But your collection show us long pass boring dribbling with out any goal attempt, Ask Sewnet and correct your way as soon as possible .
Ibrahim Abdurehman
October 13, 2014 at 7:40 am
hey mrs. Mariano Baretto , Please you new comers just look ,what the ethiopian football players in the past before 31 yrs ,then we were born as a new child by mrs Sewinet Bishaw who is not that much foot ball expert and not that much famous couch in his history , but he try to get the Ethiopian football secret . just look the match not only as the football fun, as football expert. Because our intention fantastic football and winning. to get it, it needs more time. B/c our coach is new,his football tactics and philosophy is new for our players and we Ethiopians need this those Match b/c they help us for CAF cup of 2015.plz do your best ……?
abenezer
October 12, 2014 at 7:36 pm
All federation mamber is stop they work and re build it
Tek
October 12, 2014 at 3:08 pm
mejemera egiri kasi edigeti tukureti enisixxi belijochi enijemire zemenawi silixena enisixxi wixeti himexali!!!!!!!!!!!!!!!!!!!!!!!!!!!!!!!!!!!!!!!!!!!!!!!!!
Teshe
October 12, 2014 at 12:06 pm
please please coach
Anonymous
October 12, 2014 at 10:01 am
Mr. coach, please be hard working. We don’t want to repeat and/or see the past sport history of our country. we need to be come first just like that of Athletics. Therefore, please refer the methods in which various famous international and/or national coaches are follow. Otherwise, the people of Ethiopia may not allow you to pay your monthly salary.
wasihun abate
October 12, 2014 at 9:46 am
Please you Ethiopian, look the match not only as the football fun, as football expert. Because our intention fantastic football and winning. to get it, it needs more time. B/c our coach is new,his football tactics and philosophy is new for our players.
Anonymous
October 12, 2014 at 9:19 am
sory federation
Anonymous
October 12, 2014 at 9:12 am
ድሮውንም እኛ ኢትዮጲያዎች ስንባል ለውጥ(ማደግ) አንወድም!! ጋሽ ሰውነት ቢሻው ሲናፍቀን የነበረውን የአፍሪካ ዋንጫ አሳይተውን፣ ለአለም ዋንጫ የመጨረሻ ማጣሪያ አድርሰውን ሽልማታቸው መባረር(መሰናበት) ሆነ ግን ለምን¬……….. ለዚህ አሰልጣኝ የሚከፈለው ለዛኛው አሰልጣኝ አልተከፈለውም ስራቸው ግን ተቃራኒ ነው,መቀነስ የሌለባቸውንስ ተጨዋቾችስ ለምንስ ይቀንሳቸዋል,……… ወገኔ ነጭ አያታለን እኛው ራሳችን ለራሳችን አናንስም!!!!!!!!!!!
zelalem
October 12, 2014 at 8:27 am
are sewint yeshalenal endabarerachut leminachute ametute
wubegzier
October 12, 2014 at 7:39 am
የተሻለ ተክለ ሰውነት ያላቸው ተጨዋቾች ቢመጡ ቡድኑ እንደ ማሊዎቹ ጠንካራ ሊሆን ይችላል ያገራችን አሰልጣኝ ባለፉት ጨዋታወች ከእረፍት በኋላ እንዴት የተጨዋች ለውጥ አድርገው የጨዋታ ለውጥ እንደሚያመጡ ማየት ይቻላል።
Assafew tamene
October 12, 2014 at 7:16 am
አሰልጣኝ ሆይ ሁሌ የተጫወትነው ከጠንካራ ቡድን ጋር ነው የምትለን ከሆነ ቀላል ቡድን እንፈልግልህ እንዴ.
ልምድ ለማግኘት ሰዉነት ቢሸዉን ጠይቀዉ እባክህ ወደ ኋላ አትመልሰን