Articles
ሦስት መንግሥታትን በቤተመንግሥት ውስጥ

April 07, 2014 | Written by አበባየሁ ገበያው
አቶ አያሌው ይመር ከቀዳማዊ ኃይለሥላሴ ጀምሮ እስከ ኢህአዴግ ዘመን በሦስት መንግሥታት ቤተመንግሥት ውስጥ ሰርተዋል – በኃላፊነት፡፡
በተለይ ጃንሆይ የቤተመንግስቱ ኃላፊ አድርገዋቸው ነበር፡፡ ከንጉሱም ጋር ቅርበት ነበራቸው፡፡
የ84 ዓመት የዕድሜ ባለፀጋው አቶ አያሌው ስለ ቤተመንግሥት ሥራቸውና ስለንጉሱ ከጋዜጠኛ አበባየሁ ገበያው ጋር በስፋት አውግተዋል፡፡ እነሆ፡-
ከአፄ ኃይለስላሴ ጀምሮ፣ በደርግም ሆነ በኢህአዴግ ቤተመንግስት ውስጥ ነበሩ፡፡ እንዴት ነው ቤተመንግስት የገቡት?
በ1952 ዓ.ም ነው ቤተመንግስት የገባሁኝ፡፡ ጄነራል አበበ ነበሩ ያሳደጉኝ፡፡ አክስቴ 40 ሺ ሄክታር ቦታ ነበራት፡፡ እዚሁ አሁን ስድስት ኪሎ ተብሎ የሚጠራው አካባቢ፡፡ አሁንም የምኖረው እዚሁ አካባቢ ነው፡፡ በጣም ሰፊ ነበር፡፡ እኛ የእቴጌ ጣይቱ ወገኖች ነን፡፡ ጎንደር፣ ጎጃም፣ የጁ… የእኛ ነው፡፡ ጠዋት ማታ ጄነራል አበበን ነበር የማስታምመው፡፡ ጄነራል አበበ የታመሙት ቲቢ ነበር፤ ሳንባ በሽታ፡፡ ጃንሆይ መጥተው ሲያይዋቸው ሁልጊዜ ሰላምታ እሰጣቸው ነበር፡፡ “እንዴት ዋልክ” ይላሉ። ሲወጡ ጥጥ በአልኮል ነክሬ በር ላይ እጠብቃቸዋለሁ፡፡ እጃቸውን አልኮል በነካው ጥጥ ጠረግ ጠረግ ያደርጉትና ፈገግ ብለው ያዩኛል፡፡ ጄነራልም ከህመማቸው አላገገሙ እሳቸውን ቀብሬ አክስቴን ልጠይቅ ወደ ስድስት ኪሎ እያመራሁ እያለ… ቀዳማዊ ኃይለስላሴ ሆስፒታል የሚባለው ጋ… አሁን የካቲት 12 ነው መሰለኝ የምትሉት “ጃንሆይ መጡ መጡ” ተባለ፡፡ እንዳጋጣሚ ነው አየት አድርገው ያወቁኝ፡፡ እናም አስጠሩኝ፡፡
“የት ነው ያለኸው?” አሉኝ፡፡
“አክስቴ ጋ” አልኳቸው፡፡ አንገታቸውን ወዝወዝ አድርገው አለፉ፡፡
ቤት ሄጄ የተባልኩትን የሆነውን ሁሉ ለአክስቴ ነገርኳት፡፡ አክስቴም “ምን ይታወቃል… ሊያሰሩህ ይሆናል” አሉኝ፡፡ አንድ ጠዋት የእቴጌ ዣንጥላ ያዥ (ረጅም ነው) ተልኮ ቤታችን መጣ፡፡ “ኧረ ተካ ገዳ… ከመቼ ወዲህ…” አሉ አክስቴ፡፡
“የድሮው ጠጅ የለም እንዴ… እሜቴ?” እያለ እያጨዋወታቸው ወደ ቤት ዘለቀ፡፡
“የጄነራል አበበ አሽከር የነበረውን አምጣ ተብዬ ነው” አላቸው፡፡ ከቤት ይዞኝ ሄደ፡፡ ስድስት ኪሎ ልደታ አዳራሽ በፊት ለፊት በር ይዞኝ ገባ፡፡ ጃንሆይ እጄን ይዘውኝ፤
“ከዛሬ ጀምሮ ከዚህ እንዳትነቃነቅ” አሉኝ፡፡ በቃ! እዚያው ቀረሁ ቀረሁ፡፡
ቤተመንግስት ውስጥ ምን ነበር የሚሰሩት?
በፊት የመጠጥ ቤት ኃላፊ ነበርኩ፡፡ በኋላ ከመጠጡ ወጥቼ ምክትል የእልፍኝ አስከልካይ ሆንኩ፡፡ ሴት ወይዘሮና መኳንንቱን ከእቴጋ ጋር አገናኝ ነበር፡፡ እቴጌ ቢሮ ነው የሚቀመጡት፡፡ የተበደለውን፣ ፍርድ ጐደለብኝ የሚለውን “ውሰድና ለእገሌ አገጣጥም፣ በቶሎ ፍርዱ ይታይለት” ብለው ያዙኛል፡፡ ጃንሆይም ለብቻቸው ችሎት አላቸው፤ በችሎታቸው ያስችላሉ፡፡ ምሳ ሲደርስ መኳንንቱ ይመጣሉ፤ ጃንሆይ ጋ ምሳ ለመብላት፡፡ ጃንሆይ ያን ምሳ ይጋብዙና ወደ ማረፊያቸው ይገባሉ፡፡ ጠዋት ፆም ከሆነ፣ ፀሎታቸውን ጨርሰው ለባብሰው ነው ቁጭ የሚሉት። ስድስት ሰዓት ሲሆን የህዝብ ችሎት ቀርበው ያሟግታሉ፡፡ ከዛ ቅዳሴ ካለ ተነስተው ይሄዳሉ፡፡
ቀጠሮ ሲኖር ማስታወሻ እንይዛለን፡፡ “በዚህ ሰዓት እንግዳ ይመጣል” ብለን ለጃንሆይ እንነግራለን፡፡ አስተርጓሚው ይገባሉ፤ እኛ እንወጣለን። እኔ ለእቴጌም ለጃንሆይም ቅርብ ነበርኩ፡፡ መንግስቱ ንዋይ ያንን ካደረገ በኋላ እኮ (መፈንቅለ መንግሥቱን ማለታቸው ነው) የታችኛው ቤተመንግስት የቢሮዋቸው ኃላፊ አድርገውኝ ነበር፡፡ አዛዡ፣ ሊጋባው፣ አጋፋሪው… ብዙ ብዙ ደረጃ ነበር፡፡ ጠቅላዩ ግን የቤተመንግስቱ ሚኒስትር ናቸው፡፡ በእኔ ሥር አስራ አምስት ሰራተኞች ነበሩ፡፡ ጃንሆይ ብሔራዊ ቤተመንግስት ነው የሚበሉትም የሚያድሩትም፡፡ ፈረንጆች አንዳንድ ገፀ በረከቶች ሲሰጡዋቸው፤ ያንን አንስቼ አስቀምጣለሁ፡፡ በኋላ ያዩትና… “ምንም የሚረባ ነገር አይደለም… ብቻ ይሁን” ይላሉ፡፡
እስቲ የጃንሆይን የዕለት ዕለት ተግባር ይንገሩኝ…?
ከጠዋቱ በ12 ሰዓት ላይ ወታደሩ ከአንደኛ በር ተነስቶ፤ በሰልፍ ሂዶ ነው ባንዲራ በጥሩንባ የሚሰቅለው፡፡ የባንዲራ መስቀያው ፊት ለፊት የእሳቸው መኝታ ቤት ነው፡፡ በራቸውን ወለል አድርገው አንደኛ በር ድረስ ያያሉ፡፡ የጠዋት የሙቀት ልብሳቸውን ለብሰው፤ በዛውም ወደ ፀሎት ይሄዳሉ፡፡ የፀሎት ስፍራቸው፣ ከእንጦጦ ማርያም ትይዩ ነው፡፡
ወደ ፀሎት ሲያዘግሙ “እንዴት አደራች” የለም፤ ዝም ነው የሚሉ። ሰው አያነጋግሩም፡፡ ፀሎታቸውን ሲያበቁ ነው የሚያነጋግሩት፡፡ ከላም አላቢዎችና ፈረስ ቦራሾች በቀር በዚያች አካባቢ ዝር የሚል የለም፡፡ ዳዊቱን የሚደግሙት በቃላቸው ነው …ግዕዙን እኮ ነው፡፡ በ12 ሰዓት ጠዋት የቆሙ ሁለት ሰዓት ሲሆን የቆሙባትን መሬቷን ሳም አድርገው ነው የሚነሱት። ከዛ የከብቶቹን ኃላፊ ይጠሩታል፡፡
“ተሰማ … ላሟ ጥጃዋን ስትዋጋት አላየህም … ለምንድነው?” ይላሉ፡፡ ወደ ፈረሶቹ ዘወር ይሉና ደግሞ፤ “ክፍ.. ሲነክሰው ዝም ብለህ ታያለህ፤ አላየሁም መሰለህ … ሁለተኛ ተጠንቀቁ” ይላሉ፡፡
እስቲ ስለ1953 ዓ.ም. የታህሳስ ግርግር፤ ይንገሩኝ…?
እዚያው ቤተ መንግስት ውስጥ ነበርን፡፡ መንግስቱ ንዋይ እኮ ነው፡፡… ጃንሆይ ፈረንጅ አገር ሄደዋል፡፡ እቴጌ… መኳንንቱ ሚኒስትሮቹ አሉ፡፡ እኛ አላወቅንም፡፡ ማታ 4፡30 ወደ 5 ሰዓት ገደማ ነው- እኔ ወደ ቤቴ የምገባው፡፡
ለምን?
ቁልፍ ይዣለኋ!
የምን ቁልፍ?
የመጠጡን ነዋ! እቴጌም ቢኖሩ ያው እንደ ጃንሆይ ናቸው፡፡ ጃንሆይ የትም ለመሄድ ሲያስቡ ድብቅ ነው፡፡ ያኔም ለህዝብ አልተነገረም፡፡ የሚያውቅ ግን ያውቃል፡፡ ከዚያ እንግሊዝ አገር ሆነ መቀመጫቸው፡፡ ቆይተው ባለቤታቸውንና ልጆቻቸውን ወሰዱ፡፡ የጃንሆይ አባት ራስ መኮንን፣ እንግሊዝ አገር የሠሩት ቤት አለ – “ፌርፊልድ ቤተመንግስት” ብለዋታል ጃንሆይ፡፡ ከከተማው ወጣ ብሎ ነው የሚገኝ፡፡
እርስዎ የእንግሊዙን ቤተመንግሥት የማየት ዕድል ገጥሞዎታል?
አላየሁትም፡፡ ጃንሆይ ከተመለሱ በኋላ በተራ እንደወስዳችኋለን ብለው ነበር፡፡ እድላችን ሆኖ አልሄድንም፡፡ በፎቶግራፍ ግን አይቼዋለሁ። እና ጃንሆይ እንግሊዝ አባታቸው ቤት ገቡ፤ ልጆቻቸውንም ባለቤታቸውንም ወሰዱ፡፡ ትንሽ የተማሩትን ባለስልጣናትም ወስደዋል፡፡ ሃሳባቸው የጣልያንን ወረራ ለዓለም ከፍተኛው ፍ/ቤት ማቅረብ ነበር፡፡
መንግስቱ ንዋይ መክዳቱን ጃንሆይ አውቀዋል። በስምንተኛው ቀን ቤተመንግስቱ በታንክ ተከቦ… ስራ ልንገባ ስንሄድ አይቻልም አሉለን፡፡ ሚኒስትሮችን ማታ “እቴጌ ታመዋል” ብሎ ጠርቶ አጐራቸው። እቴጌ የራሳቸው ቤት አለ፤ ከአሜሪካ ኤምባሲ ጐን፤ የእናታቸው ቤት ነው፤ እዛ ገቡ፡፡ ሲነጋ ሄድን፤ ሰውም ዙሪያውን ከበበ፡፡
ወዲያው አልጋ ወራሽ በሬዲዮ “እኔም እንደ አንድ ኢትዮጵያዊ ሆኜ ለአገሬ ላገለግል በተቆረጠልኝ ደምወዝ…” የሚል ነገር ሲናገሩ ክው አልን፡፡ “አስገድዷቸዋል…” አልነ፡፡
ጠቅል ይህን ሲሰሙ ባሉበት ሆነው ብድግ አሉ።
“ህዝቤን እኔ አውቀዋለሁ፤ ህዝባችን እኛን ይወደናል፤ ግዴለም እኛ ከአንድ ከሁለት ሰው ጉዳይ የለንም” ብለው ገሠገሡ፡፡ አስመራ ሲገቡ የአስመራ ህዝብ “እኛ እንቅደም እርስዎ ይቆዩ” አለ.. “አይ ግዴለም” ብለው መጡ፡፡ ያኔ አውሮፕላን ማረፊያው ጦር ኃይሎች ነበር፡፡ ያን ጊዜ የቦሌው አውሮፕላን ማረፊያ አልተሠራም፡፡ እዚያ ሄደን ንጉሱን ጠበቅናቸው፡፡ መሬቷ አትታይም፡፡ ህዝቡ ለጉድ ነበር፡፡ ጃንሆይ ፈገግ ፈገግ እያሉ ነበር፡፡ አቡነ ባስሊዎስ ከጐናቸው ነበሩ፡ የጦር ሚኒስትሮቻቸው ጀነራል መርድ መንገሻና ጀነራል ከበደ ገብሬ ነበሩ መንግስቱ ንዋይን ድል ያደረጉት፡፡ ሰራዊቱ ተዋጋ፡፡ ለካ ግማሹ ክቡር ዘበኛም አላወቀም፡፡ “እንግሊዝኛ ቆጠርን!!” የሚሉት ናቸው የከዱት። ጃንሆይ ቀጥታ ልዕልት ተናኘ ቤት ነው የገቡት፡፡ ቆዩና ብሔራዊ ቤተመንግስት ገቡ፡፡ ለሊቱን ሙሉ ተኩስ ነበር፡፡ ጃንሆይ “እባካችሁ ከልክሉ” ይላሉ። አበበ አረጋይም ተው ይላሉ፡፡ ጃንሆይ ቀዳማዊ ኃይለስላሴ ሆስፒታል ሄደው ብዙ ሬሳ ተመለከቱ። ሬሳው ሲታይ “እነ ራስ ስዩም፣ እነ አበበ አረጋዊ… ሚኒስትሮች ሁሉ… ነበሩበት፡፡ መንግሥቱ ንዋይ ኩዴታው መክሸፉን ሲያውቅ ቀጨኔ መድሃኒያለም ተደብቆ፣ ሌሊት ወደ ሶማሊ ሲሄድ ዝቋላ ላይ ተያዘ። ተታኮሰ፤ አንድ አይኑን መቱት፡፡ ወንድምየውን ገደሉት፡፡ እሱን ወደ ጃንሆይ አመጡት፡፡ ብርድ ልብስ ለብሶ ባዶ እግሩን ነበር፡፡
“መንግስቱ” አሉት ጃንሆይ፤ አንድ ዓይኑ አያይም “ያ ሻምፓኝ የምትጠጣበት ቤተመንግስት ነው” “አይታየኝም” አላቸው፡፡ ይኸኔ “ውጡ ውጡ” ተባልንና ወጣን፡፡ እሱና እሳቸው ብቻ ቀሩ፡፡ ህክምና ተደረገለትና ለፍርድ ቀረበ፡፡ ያ ሁሉ ደመኛ ዘመድ መጣልሽ፡፡ ከፍተኛ ፍ/ቤት ሰው ግጥም አለ። የሞት ፍርድ ተበየነበት፡፡
ተክለ ሃይማኖት አደባባይ መሰላል መስቀያ ተዘጋጅቶ ለንጋት አጥቢያ ላይ በ12 ሰዓት ህዝቡ ግጥም ብሏል፡፡ መንግስቱ ገበር ጅንስ ሱሪና ከላይ ሸሚዝ ነበር የለበሰው። የመስቀያውን ደረጃ ጢብ ጢብ ብሎ ወጣ፤ ወዲያው መሰላሉን ሸርተት አደረጉት፡፡ በአደባባይ ተሰቀለ፡፡ ከዛ አብረው የኖሩት መርድ መንገሻ ስቅስቅ ብለው አለቀሱ፡፡
ምክትል እልፍኝ አስከልካይ ሆኜ እሰራ ነበር፤ ለእቴጌ መነን፡፡ ጃንሆይ ወታደሩንም፣ ሹማምንቱንም ሰብስበው “የተወለድኩበትን የአባቴን ቤት ለዩኒቨርስቲ አስረክቤዋለሁ” አሉ፡፡ ያ ሁሉ ሚ/ር የተረሸነው እዛ ውስጥ ነው፡፡ ግብዣቸውን አድርገው ብሔራዊ ፍልውሃ ቤተመንግሥት ገባን። ያን ጊዜ እሳቸው ህዝባቸው እንዲማርላቸው፣ ያን ጊዜ ጨለማ ነው፤ ትምህርት የለም፡፡ በየአገሩ፣ በየወረዳው እየሄዱ እንጨት አጣና እየረበረባችሁ ት/ቤት አቋቁሙ አሉ፡፡ መጽሐፉን ሁሉ በመኪና እየጫኑ እየሄዱ ይሰጡ ነበር፡፡
በቅርቡ የወጣ መጽሐፍ፤ ጃንሆይ ጥፋት የፈፀሙ የቤተመንግሥቱ ባለሟሎችን በአለንጋ ይገርፉ እንደነበረ ይገልፃል፡፡ እርስዎ ይሄን ያውቃሉ?
ጃንሆይ!!? (ራሳቸውን ይዘው እየነቀነቁ) ጠርተው “ተው! እንደዚህ አይነት ብልግናህን ተው!” ብለው ነው የሚመክሩት፡፡ ብለው ብለው ሲያቅታቸው “አለንጋ አምጡ” ብለው…ትንሽ ነካ አድርገው ነው የሚተውት፡፡
ይኼው መጽሐፍ …ስስት አለባቸው ይላል ንጉሡን?
ውሸት ነው፡፡ በልተሸ የጠገብሽ አይመስላቸውም እኮ፡፡ “አንሺ፣ ብይ… ያወጣሽውን ምግብ መጨረስ አለብሽ” ነው የሚሉሽ፡፡ ሴት ወንድ ሳይሉ ይጋብዛሉ፡፡ እሳቸው የሚቆጡት መብራትና ውሃ ያለጥቅም ሲባክን ነው፡፡ “መብራትና ውሃ ማን አባቱ ነው የሚከፍተው? ጥራ ማን ነው የከፈተው ይሄን ውሃ፤ እናንተ አታውቁትም፤ እኛ እናውቀዋለን የውሃን ጡር” ይላሉ፡፡
የጃንሆይ አመጋገብ እንዴት ነበር?
ጃንሆይ የእኛን ሀገር ምግብ ብዙም አይወዱትም ትንሽ አልጫ ነበር የሚወዱት፡፡ በተረፈ ግን የፈረንጅ ምግብ ነው የሚመርጡት ኬክ ከምግብ በኋላ ሳይሆን በ10 ሰዓት ከሻይ፣ ከወተት ጋር ሆኖ ይቀርብላቸዋል፡፡ ራሳቸው የሚፈልጉትን ያህል ቆርጠው ነው የሚበሉት፡፡
እቴጌ ጣይቱ የአፄ ምኒልክ ቀኝ እጅ እንደነበሩ ይነገራል፡፡ የአፄ ኃይለሥላሴ እቴኔ መነንስ እንዴት ያሉ ነበሩ?
እቴጌ እንኳን ፀሎተኛ ናቸው፡፡ እቴጌ ጣይቱማ በጦሩም ጭምር አሉበት፡፡ እኝህ እቴጌ መነን ፀሎት ብቻ ነው፤ ደግ ሰው ነበሩ፡፡ በፀሎት ጥሩ አድርገው አገራቸውን የረዱ ሰው ናቸው፡፡ መንህፍት ማንበብ፣ ዳዊት መድገም እንጂ ሌላ የሚያውቁት ነገር የለም። ብቻ ከፈረንጆቹ ጋር ቀጠሮ ሲኖራቸው በአስተርጓሚ መልስ ይሰጣሉ፡፡ ጃንሆይን ያልሽ እንደሆነ ደግሞ የደግነታቸውና የአስተዋይነታቸውን ብዛት አልነግርሽም። መኳንንቱ እንደመሰለው ሲፈርድ… እሳቸው ችሎት ቀርበው ጉዳዩ ሲነበብ ልብ ብለው ያደምጣሉ፡፡ “እዚች ጋ ምልክት አድርግ” እያሉ ተነቦ ሲያልቅ.. “እስቲ ቅድም ምልክት ያደረክበትን አንብብ” ይላሉ መልሰው፡፡ ያ ሁሉ ተደርጐ ነው እሳቸው የሚፈርዱት፡፡ ከዚያ “ርስቱን ቀማኸው፤ አያቱ አድዋ ዘምቶ፣ አባቱም ማይጨው ሞቶ አንተ ጣሊያን ሰጠኝ ብለህ የያዝከው መሬት አይደለም… ለእሱ ይገባል” ብለው ይፈርዳሉ፡፡ ልጃቸው ቢሆንም እንኳ ለሃቅ ነው የሚፈርዱት፡፡ ልብ እንደ ጐራዴ ተመዞ አይታይ እንዴት ብዬ ልንገርሽ? ለፍርድ በጣም ይጠነቀቃሉ፡፡ እንደሳቸው ጥንቁቅ ማንም የለም። ጠዋት ማታ ፖለቲካውን አስተዳደሩን… ይከውናሉ። በቀኛቸው ዶሴ በግራም ዶሴ ነው፡፡ የሞት ፍርድ እሳቸው ካልፈረሙበት አይፈፀምም፡፡ የፍርድ ሚኒስትሩ አቶ አካልወርቅ “ጃንሆይ ያን ነገር እባክዎ አዘገዩት” ይሏቸዋል፡፡
እሳቸውም “ሰው ለመግደል ምን ያስቸኩልሃል?” ይሉታል፡፡ ይሄኔ ዝም ይላል፡፡ ሁልጊዜ የሞት ፍርድ ላይ ፊታቸውን አዙረው ፀልየው ነው፡፡ ምን ያድርጉ… ፍርድ ነዋ፤ አይቀር!
ቀደም ሲል በጠቀስኩልዎት “የንጉሱ ገመና” መፅሃፍ ላይ “ሴሰኛ” መሆናቸውና ከቤተመንግሥት የፅዳት ሠራተኞች ጋር ሳይቀር ይቀብጡ እንደነበር ተጠቅሷል፡፡ ይሄስ ምን ያህል ሃቅ ነው?
አይ ሰው ከንቱ! ይሄን አለም የተውት ገና ከስደት ሲመጡ ነው፡፡ ግን እሳቸው ምን ቸገራቸው! አየሽ… ባላደረግሽው ነገር ስትታሚ እግዚአብሔር ነው ዋስሽ። እሳቸውን ማንም የሚጠረጥራቸው የለም። ባይሆን እንኳ እነ ልዑል መኮንን… ልጆች ስለሆኑ ጨዋታ ይፈልጉ ይሆናል፡፡ አፄ ኃይለሥላሴ የተማሩ እኮ ናቸው፡፡ የሊቁን ትምህርት በግዝ ሲነግሩሽ… ሌላ ነው፡፡ አባታቸው ራስ መኮንን ጥሩ አድርገው አስተምረዋቸዋል፡፡ ኦሮምኛ ሲናገሩ ጥርት አድርገው ነው፡፡ በእርግጥ ንጉስ ስለሆኑ በአስተርጓሚ ነው የሚሠሙት፡፡ አንዴ መንገድ ሲሄዱ አንዱ “ጃንሆይ ተበደልኩ” እያለ በኦሮምኛ ይማፀናል፡፡ ጃንሆይም አብሯቸው ያለውን ሰው “ምን አለ?” ብለው ጠየቁት፡፡ እሱ ለካ ኦሮምኛ አይችልም፡፡
“ኧረ እኔ አላውቀውም ጃንሆይ” አላቸው፡፡
“ምን አባክና የአገርህን ቋንቋ አታውቅም” ብለው ገሰፁት፡፡ እሳቸው ገጠሙታ በኦሮምኛ፡፡ አደርኛም አረብኛም ትግርኛም ይሰማሉ፡፡ ንጉስ ስለሆኑ ግን ሁሉንም በአስተርጓሚ ነው፡፡
ከበደ ተሰማን ያውቋቸዋል?
ደጃች ከበደ ተሰማ አብረን ኑረን አይደል፡፡ ጥንት የዘውዲቱ አሽከር ነበሩ፡፡ በምኒልክም ትንሽ ልጅ ናቸው እንጂ መድረስ ደርሰው ነበር፡፡ ጃንሆይ ከነገሡ በኋላ ደጃዝማች ብለው ጠቅላይ ገዢ አደረጉዋቸው፡፡
በፊት አሽከር ነበሩ፡፡ ደጃዝማች ከበደ ተሰማ ለጃንሆይ ቅርብ ነበሩ፡፡ ዕውቀታቸው የሀገር እንጂ የውጪ ትምህርት አልነበራቸውም፡፡ ብልሃተኛ ነበሩ፡፡ እነ ከበደ ተሰማ እየሩሳሌም ተቀምጠው፣ ጃንሆይ እንግሊዝ እያሉ፣ ምስጢር ይነጋገሩ ነበር። ከበደ ተሰማን ጥሩልኝ ብለው ከእየሩሳሌም በፖርት ሰይድ፣ በግብፅ አድርገው እንግሊዝ አገር ገቡ፡፡ የኢትዮጵያ መሬትን ከረገጡማ ጣሊያን ይይዛቸዋል።
በእንግሊዝ ከተገናኙ በኋላ “እንግዲህ አንተን የጠራንህ በኢትዮጵያ ጦርነት ተነስቷል፤ እየቀደምክ ወረቀት እየፃፍክ ለጎንደር፣ ለጎጃም፣ ለሸዋ፣ ለትግሬ፣ ለኦሮሞ… በምስጢር ላክ፤ “ጃንሆይ መጡ ጃንሆይ መጡ” እያልክ አሏቸው፡፡ ከዚያም ጣሊያን እንዳይማርካቸው ከእንግሊዝ ጦር ጋር እየተከተሉ፤ ለጎንደር ህዝብ በአውሮፕላን ወረቀት ተበተነ። እልልታው ፈነዳ፡፡ ያን ግዜ በቤተመንግስት ባንሆንም የቀዳማዊ ኃ/ሥላሴን “መጣሁልህ አይዞህ” የሚል ወረቀት ስናነብ ለቅሶ ሆንን፡፡
ከዚያ እሳቸው ጎጃም ገቡ… የአርበኛውን ጦር ለማየት እዛው ቁጭ አሉ፡፡ አርበኛው ሁሉ ገብቶ ገብቶ ሰልፉን አሳይቷል፡፡ “በላይ ዘለቀ ነገ ይመጣል” ተባለ፡፡ ጃንሆይ ከመጓጓታቸው የተነሳ ጠዋት በ4 ሰዓት የተቀመጡ አልተነሱም፡፡ በኋላ ምሳ ሰዓት ሊደርስ ሲል መጣ፤ በፈጥኖ ደራሽ በወጣት ጦር ታጅቦ፡፡ “የገሊላው” አሉ፤ የጃንሆይ ወንድም ራስ ካሣ ከጃንሆይ ጎን ተቀምጠው። ሲደነግጡ የሚጠቀሙበት ዘይቤያቸው ነው፡፡ በላይ ዘለቀ መጥቶ ከጃንሆይ ፊት ቆመ፡፡
“በላይ ዘለቀ ማለት አንተ ነህ? እንደ ጆሮህ ትልቅ፤ እንደ አይንህ ትንሽ” አሉት፤ ጃንሆይ። (ዝናህን ስንሰማ ትልቅ ዕድሜ ያለህ መስሎን ነበር ማለታቸው ነው) ልጅ ነው፤ ፈጣን፡፡ እሱም ከጐናቸው ተቀመጠ፡፡ የልጅ ነገር ሆነና በገዛ እጁ ሞተ፡፡ የጎጃም ጠቅላይ ገዥ እሆናለሁ ብሎ ነበር፤ ውስጥ ውስጡን፡፡ ሰው ክፉ ነው አጣሏቸው፤ እዚህ መጥቶ ታሰረ፡፡ ከእስር ቤት ሰብሮ አመለጠ፡፡ ሱሉልታ ላይ መቶ አለቃውን በጥይት ገደለ፡፡ በመጨረሻ ተያዘና ለፍርድ ቀረበ። …ጃንሆይ እንዲሞትባቸው አልፈለጉም ነበር፡፡ በፍትሃ ነገስቱ… “በግፍ የገደለ ይገደል” ስለሚል ተሰቀለ፤ ጎጃም አኮረፈ፡፡
በላይ ዘለቀን በደንብ ያውቁት ነበር?
የአክስቴን ቤት ተከራይቶ ነበር የሚኖር። ጠይም የሚምር ቆንጆ፣ ጀግና ነበር፡፡ አክስቴ ከምግቡም ከቅቤውም ከማሩም ለበላይ ሰራተኞች ውሰዱ ይሉናል፤ ወስደን እንሰጣለን፡፡ ቤቱ ስንሄድ እንደ ገጠር ቤት በየቦታው በገል ጢስ ይጢያጣሳል። ይኼን ሳይ “ምንድን ነው” ብዬ አክስቴን ጠየኩዋት። “በሽታ እንዳይነካው ይሆናል” ብላ ሸፋፈነችለት… ነገሩ እንኳን ሌላ ነው፡፡ አንድ ሁለት ወር ያህል እንደተቀመጠ ቤት ተሰጠውና ወጣ፡፡ አፄ ኃይለሥላሴ ደሃቸውን የሚወዱ ነበሩ፡፡
ደመወዝዎ ስንት ነበር?
40 ብር ነበር፡፡ በእኛ ግዜ በጣም ብዙ ነበር፤ የትየለሌ ነው፡፡ ባለቤቴ የቤትዋን ጣጣ ትጨርስበታለች ወሩን ሙሉ፡፡ አንዲት ጠቦት በግ ለመግዛት አስራ አምስት ብር እንኳን አይፈጅም ነበር፡፡
በቤተ መንግስት ውስጥ በኃላፊነት ላይ ከነበሩ ሰዎች በተለየ ከነገስታቱና ሹማምቱ ጋር ቁጭ ብለው ፊልም እንዲያዩ ይፈቀድልዎት ነበር ይባላል?
እኔ ቆሜ ነበር የማየው፡፡ ጃንሆይ ካላዘዙ ማንም የሚቀመጥ የለም፡፡ ምግብ የሚያቀርብላቸውን እሸቱን ጠርተው “ከብላታ አድማሱ ጀርባ ለአያሌው ወንበር አስቀምጡና ፊልም ይመልከቱ” ብለው አዘዙ። ራት በልተን ልንወጣ ስንል ተጠራሁና፤ ፊልም ማየት እንደተፈቀደልኝ ነገሩኝ… እጅ ነሳሁና ተቀመጥኩ፡፡
ቤተመንግሥት ምን ዓይነት ፊልሞች ነበር የሚታዩት?
የጀርመን የሁለተኛ የዓለም ጦርነትን ፊልም ነበር የምናየው፡፡ ጃንሆይ ፊልም ሳያዩ አይተኙም፡፡ ስድስት ኪሎም ሆነ ብሔራዊ ቤተመንግስት ረዣዥም ፊልሞችን ይመለከቱ ነበር፡፡ ለእቴጌ የልዕልት ተናኘ ልጅ ሒሩት ከጎናቸው ቁጭ ብላ ታስተረጉማለች፡፡ እቴጌ እንግሊዝኛ አያውቁም፡፡
አፄ ኃይለስላሴ እንግሊዝኛ በደንብ ይችሉ ነበር?
እንዴታ! በደንብ ነዋ! ፈረንሳይኛማ ከልጅነታቸው ጀምረው እንደውሃ የጠጡት ነው፡፡ እንግሊዝኛ ሲናገሩ የዋዛ መሰሉሽ፡፡ ዶ/ር ቴዎድሮስ የሚባሉ የእርሳቸው ሀኪም ማታ ማታ ከአጠገባቸው አይጠፉም ነበር። በ11 ሰዓት የመጡ ማታ ፊልም ሲያልቅ ከጃንሆይ ጋር ተነስተው ነው የሚሄዱት፡፡ ጃንሆይ በፈረንሳይኛ የሚያወሩት ታዲያ ከሀኪማቸው ጋር ብቻ ነበር፡፡
እስቲ ከዙፋናቸው የወረዱበትን ሁኔታ ይንገሩኝ…
የያዝዋቸው ቤተመንግስት ውስጥ ነው፡፡ መንግስቱ ኃይለማርያም የመጣው ሐረርጌ ኦጋዴን የጦር ኃላፊ ሻምበል ሆኖ ነው፡፡ ወደዚህ እንደመጣ ዋና አደረጉት። “ሻምበል መንግስቱ” … “ሻምበል መንግስቱ” አሉት። ጃንሆይን የያዟቸው ጊዜ፤ “ሰማችሁ ለውጥ ያለ ነገር ነው፤ በእኛ ብቻ አልተጀመረም፤ ግን የአስመራን በር መከራ አይተን ያመጣነው ነውና ተጠንቀቁ፡፡ ኦጋዴኑን ተውት ግዴለም፤ ይሄንን ግን ተጠንቀቁ፤ አደራ አገሪቱ እንዳትሞት” ብለው ነው አጅሬ የተናገሩት፡፡ ሁላችንም አለቀስን፡፡ አፄ ምኒልክ ቤተመንግስት አመጧቸው፡፡ ደበላ ዲንሳ የሚባለው… ሰዎች ይዞ መጥቶ የተፃፈ ነገር በክብር አነበበላቸው፡፡ ከዚያም ግርማዊነትዎ፤ “ወደ ተዘጋጀልዎ ማረፊያ እንዲሄዱ ፍቀዱልን” አሏቸው። እሺ አሉ፡፡ ከጎናቸው እራስ እምሩ አሉ፡፡ “ይሄ ያለ ነገር ነው፤ ብቻ የአገራችሁን ነገር አደራ… አደራ” አሉ፡፡ ለረጅም ሰዓት ሰው ሁሉ ተላቀሰ፡፡ አታንሺብኝ እባክሽ። ለምን መጣሽብኝ?… አመት አቆይዋቸውና አንድ ቀን “ግርማዊ ንጉሰ ነገስት ባደረባቸው ህመም አርፈዋል” ብለው ተናገሩ፡፡ አለቀስን፡፡ ከንቱ ነው ይሄ አለም እባክሽ፡፡
በእስር ቤት እያሉ ያገኙዋቸው ነበር?
የእቴጌ ጣይቱ መኝታ ቤትና የአፄ ምኒልክ መኝታ ቤት ግራና ቀኝ ነበር፡፡ ሁለቱም የሚገናኙት በሰገነት ነበር፡፡
የአፄ ምኒልክ ልጅ ዘውዲቱ ነግሰው አልነበር፤ የጃንሆይ አልጋ ወራሽ ሆነው፡፡ ምድር ቤት እራት የሚበሉበት ስፍራ ነበረች፡፡ እዛ ውስጥ ነው መንግስቱ ለአፄ ኃይለስላሴ ማረፊያ እንዲዘጋጅ ያዘዘው። መንግስቱ ኃይለማርያም… “እርስዎ” እያለ ነበር ትእዛዝ እንኳ የሚያዘን፡፡ ከአፉ “አንተ አንቺ” የሚል አይወጣውም ነበር፡፡ ከሶስት ከአራት ቀን በኋላ… አስጠራኝና “የእስረኞች አዛዥ እርስዎ ነዎት?” አለኝ፡፡
የእነዚያ ሁሉ እስረኞቹ ሃላፊ ነኝ፡፡ በአፄ ምኒልክ አዳራሽ ነበር ያ ሁሉ እስረኛ የታሰረው፡፡ እና ወደ እስረኞች ስገባ መናገር የምፈልገውን ነገርኳቸው። “እኔን ግባ ካላችሁኝ … ስገባ “እንደምን አደራችሁ፤ እግዚአብሔር ያውጣችሁ” እላለሁ፤ ስል “ይሄንንስ ማለት አትችልም” አለኝ አንዱ፡፡
“ይኼን ካላልኩ አልገባም” አልኩ፡፡ ተጠራሁና “ይበሉ” ተብዬ ተፈቀደልኝ፡፡ ሚኒስትሮቹ እነፀሃፊ ትዕዛዝ አክሊሉ፣ መኳንቱ ሁሉ በስሜ ነበር የሚጠሩኝ። እስረኞቹ ከእኔ ጋር አብረው የነበሩ ናቸው፤ ብዙ አገለገልኳቸው፡፡
መንግስቱን ያልሽ እንደሆነ “እንዴት ነበር የምታደርጉት፣ ደሃ አታበሉም ነበር” ሲሉ ይጠይቁኛል።
እኔም የነበረውን ሁሉ አስረዳቸዋለሁ፡፡ የመንግስቱ ጥፋት አንዲት ናት፡፡ ሰውን ካለፍርዱ መግደሉ፤ “ለፍርድ ይቅረብ፣ ፍርድ ያውጣው ቢል” ጥሩ ነበር። እሱ ጥሩ ሰው ነው፤ በዙሪያው ብዙ ቀጣፊዎች ነበሩ የሚያሳስቱት፡፡ ደሃ ሲያይ ይጨነቃል፤ ሀሰት አይወድም። አንድ ቀን ግቢውን ሲጎበኝ ጠራኝ… የብርቱካን ልጣጭ ወድቆ አይቶ… “በሉ የሚመለከተውን ሰው ጥሩና ይሄን አፅዱ አለኝ” አንቱ ብሎ፡፡ ሰውን አክብሮ ነው የሚናገር።
በኢህአዴግ ዘመንስ ቤተመንግሥት ሰርተዋል?
ሁለት ዓመት ሰርቻለሁ፡፡ ብዙም አያዙኝም ነበር። እንደገቡ ፍራሹን ከየክፍሉ አወጡ አሉን፡፡ ለወታደሩ መተኛ አሰናዳን፡፡ መለስ እንደ ኃላፊ ሆኖ መጣ፤ በኋላ ከፍ አደረጉት፡፡ ብዙ ጊዜም ያነጋግረኝ ነበር፡፡ “አጥሩን… በሩን እንደዚህ ያድርጉ፤ የጎደለብዎትን ለእኛ አለቃዎ ይንገሩ” አሉኝ፡፡
አሁን ጡረታ ስንት ያገኛሉ?
400 ብር አገኛለሁ፡፡
በጡረታ ከቤተመንግስት ከተሰናበታችሁ በኋላ ባልደራስ የቤተመንግስት ጡረተኞች በሚል አንድ ትልቅ አዳራሽ ተከራይታችሁ ምግብ ቤት ከፍታችሁ ነበር…
ሁላችንም በጡረታ ተገለልን፡፡ ባልደራስ ጄነራል ፍሬ ሰንበት የተማረ ልጅ ነው ፓይለት፡፡ ጃንሆይ ናቸው ያመጡት፤ እልፍኝ አስከልካያቸው ነበር… ይወደኛል፡፡
እና “ሆቴል ማቋቋም ፈልገናል፤ ከእኔ ጋር ብትሆን” አለኝ፡፡ አቋቋምንና ሰርግ መስራት ጀመርን፤ ጥሩ ሆነ። ጀነራልም ሞተብኝ… እኔም ደከም ስላልኩ ወጣሁኝ፡፡ አሁን በቤቴ ውስጥ ነው ያለሁት ልጄ፡፡
አንዴ እዚህ ባልደራስ ለሠርግ ተጋብዤ መጥቼ ነበር። ከምግብ አቀራረብና መስተንግዶ ስርዓቱ ጀምሮ እስከ ምርቃቱ ድረስ ለየት ያለ ስርዓት ነበረው፤ ከየት የመጣ ሥርዓት ነው?
ባልደራስ ማለት የጃንሆይ የበቅሎው፣ የፈረሱ ሃላፊ ማለት፡፡ በቤተመንግስት ውስጥ ያለውን ስርዓት ነው በሰርጉም ያየሽው፡፡ ሞሰቡ ሁሉ ቀሚስ ለብሶ ለብሶ ይመጣል፤ ወደ ግብር፡፡ ጃንሆይ በዚህ ስርዓት ጊዜ ይቆማሉ፡፡ ሞሰቡ “እንጀራ ይስጣችሁ፤ እንጀራ ይስጣችሁ” እየተባለ ያልፋል፡፡ አዛዡ አደግድጎ አሸብርቆ ነው፡፡ ለመኳንንቱ በመሶብ ነው የሚቀርብ። ያም ሲሆን ደግሞ በየማዕረጋቸው ነው፡፡ የአንቺን መቀመጫ የሚቀመጥበት የለም፡፡ በእኔ መቀመጫ የሚቀመጥ የለም፤ ይሄ ህጉ ነው፡፡ ከ4-6 ሰው በአንድ መሶብ ከብቦ ይበላል፡፡ እየተፈተፈተ አሳላፊው ያስተናግዳል፡፡ ጃንሆይ “የመኳንንቱን ምግብ አምጣው እስኪ” ብለው መሶቡን ያዩታል፡፡ በመሶቡ ላይ የተቀመጠውን እንጀራ ሰቅ ሰቅ ያደርጉታል፡፡ ይህን የሚያደርጉት አሳንሰውት እንዳይሆን በሚል ነው፡፡ “እንዴት ነው ደህና አድርገህ አጥቅሰሃል?” ብለው በእጃቸው ያያሉ፡፡ በአንድ ሞሰብ ከ20-30 እንጀራ ይቀርባል፡፡ የተረፈው የአሽከር መጫወቻ ነው፡፡ ጃንሆይ በክብራቸው በነ ራስ አበበ፣ በነ ቢትወደድ መኮንን እነ ራስ መስፍን… በጠረጴዛ ዙሪያ ይበላሉ፡፡ ሰርግ ላይ ያየሽው ስርዓት ከቤተመንግስት የመጣ ነው፡፡
ምንጭ፦ አዲስ አድማስ
Articles
በኦስሎ ዳይመንድ ሊግ የ5000ሜ ፉክክር ኢትዮጵያውያን አትሌቶች በሁለቱም ፆታዎች በአሸናፊነት አጠናቀዋል

ትላንት ምሽት በኖርዌይ ኦስሎ በተከናወነው የዳይመንድ ሊግ 5000 ሜ. ውድድር ኢትዮጵያውያን አትሌቶች በወንዶችም በሴቶችም ከአንደኛ እስከ ሶስተኛ ያሉትን ደረጃዎች በመቆጣጠር አሸንፈዋል፡፡ በዝናባማ የአየር ሁኔታ ውስጥ በተካሄደው የሴቶች 5000 ሜትር ፉክክር ዳዊት ስዩም በመጨረሻዎቹ መቶ ሜትሮች ውስጥ ፍጥነቷን በመጨመር ጉዳፍ እና ለተሰንበትን ቀድማ አንደኛ ወጥታለች፡፡ የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ለኦሪገን 2022 የአለም ሻምፒዮና ከመረጣቸው ዕጩ አትሌቶች ዝርዝር ውስጥ ያልተካተተችው ዳዊት በኦስሎ ያሸነፈችበት 14፡25.84 የሆነ ሰአት የራሷ ምርጥ ሲሆን እጅጋየሁ ታዬ (14.12.98) እና ለተሰንበት (14፡24.59) ባለፈው ወር በዩጂን ካስመዘገቧቸው በመቀጠልም የዘንድሮ የአለም ሶስተኛው ፈጣን ነው፡፡ በውድድሩ ላይ ከነበሩት ሌሎች ኢትዮጵያውያን መካከል በዘንድሮው የውድድር ዓመት በርቀቱ የመጀመሪያ ተሳትፎዋን ያደረገችው አልማዝ አያና በ14:32.17 ስድስተኛ ሆና አጠናቃለች፡፡ ሀዊ ፈይሳ በ14:33.66፣ ፅጌ ገብረሰላማ በ14:43.90፣ እና አበራሽ ምንሴዎ በ14:47.98 በቅደም ተከተል ሰባተኛ፣ አስረኛ እና አስራ አንደኛ ሆነው ሲያጠናቅቁ ሶስቱም ያስመዘገቡት ሰዓት የራሳቸውን ምርጥ ያሻሻሉበት ሆኗል፡፡ ጥሩነሽ ዲባባ እ.ኤ.አ. በጁን 2008 ዓ.ም. ያስመዘገበችውና 14:11.15 የሆነው የኦስሎ ዳይመንድ ሊግ የሴቶች 5000 ሜትር የውድድር ስፍራ ሪከርድ ይሰበራል ተብሎ ተጠብቆ የነበረ ቢሆንም ሳይሳካ ቀርቷል፡፡

ዳዊት ስዩም ውድድሩን በድል ካጠናቀቀች በኋላ ለውድድሩ አዘጋጆች በሰጠችው አስተያየት ‹‹ዛሬ ለእኔ ደስታን ስላመጣልኝ በውድድሩ ሰዓት የነበረውን ዝናብ ወድጄዋለሁ ማለት እችላለሁ፡፡ ጠንካራ ተፎካካሪዎች የነበሩበት ከባድ ውድድር ነበር እናም ሁሉንም ለማሸነፍ በቅቻለሁ። በርቀቱ የራሴን ምርጥ ሰዓት ማሻሻል መቻሌም አስፈላጊ ነበር፡፡ በስታድየሙ ውስጥ በከፍተኛ ስሜት ድጋፍ ይሰጡን የነበሩ ወገኖቻችን ነበሩ። ለሰጡን ድጋፍ እናመሰግናለን።›› ብላለች፡፡ በኦስሎ የወንዶች 5000 ሜትር የመጨረሻ ፉክክሩ በኢትዮጵያውያኑ ጥላሁን ሀይሌ እና ሳሙኤል ተፈራ መካከል የነበረ ሲሆን ጥላሁን የ1500 ሜትር ስፔሻሊስቱ ሳሙኤልን በአጨራረስ ፍጥነት ቀድሞ በ13:03.51 በአንደኛነት አጠናቋል፡፡ ሳሙኤል ተፈራ የራሱ ምርጥ በሆነ 13:04.35 ሁለተኛ ሲወጣ ጌትነት ዋለ የግሉ የዓመቱ ምርጥ በሆነ 13:04.48 ሶስተኛ ደረጃን ይዞ ጨርሷል። በውድድሩ ላይ የነበሩት ሌሎች ኢትዮጵያውያን ሚልኬሳ መንገሻ በ13:05.94 አምስተኛ እንዲሁም አሊ አብዱልመናን የራሱ ምርጥ በሆነ 13:16.97 አስረኛ ወጥተዋል፡፡

ጥላሁን ሀይሌ ውድድሩን በአሸናፊነት ካጠናቀቀ በኋላ ለውድድሩ አዘጋጆች በሰጠው አስተያየት ‹‹ሶስት ኢትዮጵያውያን የመጀመሪያዎቹን ሶስት ደረጃዎች ይዘን መጨረስ መቻላችን ጥሩ አፈጻጸም ነበር። እየጠነከርኩ እንደሆነ የተሰማኝ ሲሆን በውድድሩ እና ባስመዘገብኩት ሰዓትም ተደስቻለሁ። ለረጅም ጊዜ ጉዳት ላይ ስለነበኩ ወደ አሸናፊነቱ መመለስ መቻሌ በጣም ጥሩ ነው።›› ብሏል፡፡
በኦስሎ የሴቶች 800ሜ. ውድድር ላይ ተፎካካሪ የነበረችው ኢትዮጵያዊቷ ድሪቤ ወልቴጂ በ1፡58.69 አምስተኛ ሆና አጠናቃለች።
Articles
የዘንድሮው የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ብሄራዊ ሻምፒዮና በእኔ እይታ

ከመጋቢት19-24/2014 ዓ.ም በሐዋሳ አለም አቀፍ ስቴድዮም የተደረገው 51ኛዉ የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ሻምፒዮና ከሞላ ጎደል ስኬታማ በሚባል ሁኔታ ተጠናቋል፡፡ ከአምስት አመት በኋላ በድጋሚ በአካል በመገኘት ስለተከታተልኩት የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ሀገር አቀፍ ሻምፒዮና የግል ምልከታዬን እንደሚከተለው አጠናቅሬዋለሁ፡፡ የበለጠ ትኩረትን በሳቡት ውድድሮች ዙሪያ የተመዘገቡ ውጤቶችን በወፍ በረር በመዳሰስ ስጀምር ከፍተኛ ፉክክር በታየበት የመጨረሻ ቀን የወንዶች 5000ሜ. የአለም ከ20 አመት በታች ሻምፒዮና የ3000ሜ የብር ሜዳልያ አሸናፊው አሊ አብዱልመና 13፡45.0 በሆነ ሰዓት ከጥላሁን ሀይሌ፣ ጌትነት ዋለ እና ዮሚፍ ቀጄልቻ ቀድሞ አሸናፊ ሆኗል፡፡ የፉክክሩ አካል የነበረው እና የርቀቱ የወቅቱ የአለም ሻምፒዮን ሙክታር እድሪስ ስድስተኛ ወጥቷል። ከ20 ዓመት በታች የ3000ሜ የአለም ሻምፒዮኑ ታደሰ ወርቁ በ28፡12.0 የወንዶች 10,000ሜ. ሻምፒዮን ሲሆን በ1996 ዓ.ም. በአትሌት ስለሺ ስህን ተመዝግቦ የነበረውን 28፡16.23 የሆነ የሻምፒዮናው ሪኮርድ ለማሻሻልም በቅቷል፡፡ በ10 ሺህ ሜትር የሴቶች ፉክክር ግርማዊት ገብረእግዚአብሔር በቀዳሚነት የጨረሰችበት 31፡21.5 የሆነ ሰዓት አዲስ የሻምፒዮንሺፕ ሪኮርድ ሆኖ ተመዝግቧል፡፡ በርቀቱ የከዚህ ቀደሙ ሪኮርድ ለተሰንበት ግደይ ከሶስት ዓመት በፊት ያስመዘገበችው 32፡10.13 የሆነ ሰዓት ነበር፡፡ ሳሙኤል ፍሬው በዘንድሮ የወንዶች 3000ሜ. መሰናክል አፈፃፀም ከአለም ሁለተኛው ፈጣን በሆነ 8፡22.5 ሰዓት አሸናፊ ሲሆን ጌትነት ዋለ ከአራት ዓመት በፊት አስመዝግቦት የነበረውን 8፡28.98 የነበረ የሻምፒዮናው ሪኮርድም አሻሽሏል፡፡ በሴቶች 3000ሜ. መሰናክል ከ800ሜ ወደ ረጅም ርቀት የተሸጋገረችው ወርቅውሃ ጌታቸው በ9፡41.8 ሰዓት መቅደስ አበበን (9:43.8) በማስከትል በአሸናፊነት አጠናቃለች። አድሃና ካህሳይ (3:51.0) የወንዶች 1500ሜ ፉክክሩን በበላይት ሲያጠናቅቅ በሴቶች 1500 ሜ አያል ዳኛቸው (4:10.0) ተጠባቂዋ ዳዊት ስዩምን (4:11.1) በመቅደም በአንደኛነት አጠናቃለች። በ800ሜ. ወንዶች ቶሌሳ ቦደና (1:47.1) በሴቶች ወርቅነሽ መሰለ (2:02.1) አሸናፊ ሆነዋል። ዮብሰን ብሩ በ400ሜ/400ሜ መሰናክል (45.9/50.5) ድርብ ድል ሲቀዳጅ፣ በወንዶች ጦር ውርወራ ኡታጌ ኡባንግ ብሔራዊ ሪኮርድ በሆነ 73.28ሜ. አሸንፏል፡፡ የኋልዬ በለጠው እና ዮሃንስ አልጋው በእርምጃ ሩጫ የሻምፒዮንነት ክብርን ተቀዳጅተዋል። ጥቂት አስተያየቶች፡- የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ስፖርት አፍቃሪ እንደሆነ እና ለዕድገቱ እንደሚቆረቆር ሰው በብሔራዊ ሻምፒዮናው ላይ ስለተመለከትኳቸው አዎንታዊ እና አሉታዊ ጎኖች ጥቂት አስተያየቶቼን እንደሚከተለው አስቀምጣለሁ፡- አዎንታዊ ጎኖች • ባለው ነባራዊ ሁኔታ ውስጥ ሊገጥሙ የሚችሉትን ተግዳሮቶች በሙሉ በመቋቋም ፌዴሬሽኑ ውድድሩን ከአዲስ አበባ ውጭ አካሂዶ በሰላም ማጠናቀቅ መቻሉ አንደኛው ስኬቱ ነው፡፡ • በሻምፒዮናው ላይ ጥቂት የማይባሉ ታዋቂ አትሌቶች በሀገሪቱ ትልቁ የአትሌቲክስ ፉክክር ላይ ተሳታፊ ሆነው ሲወዳደሩ መመልከት የተቻለ ሲሆን በተለይም በወንዶች 5000 ሜትር ፍፃሜ ላይ የታየው የኮከብ አትሌቶች ፉክክር ልዩ ነበር፡፡ • በውድድሩ ወቅት ለአትሌቲክስ ዳኞች የብቃት ማሻሻያ ስልጠና መሰጠቱም የውድድሩን ጥራት ለማሳደግ የሚረዳ እንደመሆኑ እሰየው የሚባል ነው፡፡ • እንደ ኢትዮ ኤሌክትሪክ ያሉት ክለቦች ለአትሌቲክስ ስፖርት የበለጠ ትኩረት በመስጠትና ተጠናክሮ በመቅረብ ከዚህ ቀደም በጠንካራነታቸው ከሚታወቁት መከላከያ እና ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ጋር የቅርብ ተፎካካሪ ሆነው መታየት፤ የኦሮሚያ ክልል፣ ደቡብ ፖሊስ እና ሲዳማ ቡና ክለብ አትሌቶችም ጠንካራ ተሳትፎ ሳይዘነጋ የሻምፒዮናው ፉክክር ድምቀት ነበሩ፡፡ • የአንዳንዶቹ ተገቢነት አጠያያቂ ቢሆንም ብዛት ያላቸው የሻምፒዮናው ሪኮርዶች የተሻሻሉበት ውድድርም ነበር፡፡ አሉታዊ ጎኖች • የሀገሪቱ ትልቁ የአትሌቲክስ ውድድር ውጤት አሁንም በኤሌክትሮኒክስ የሰዓት መቆጣጠሪያ የማይደገፍ መሆኑ በተለይም በአጭር ርቀት እና በሜዳ ላይ ተግባራት ውድድሮች ላይ የሚሳተፉ አትሌቶች ልፋት ተገቢውን እውቅና እንዳያገኝ እያደረገ ይገኛል፡፡ የሻምፒዮናውን ውጤቶች በዘመናዊ እና ዓለም አቀፉን መለኪያ በሚያሟላ መልኩ አለመያዝ በአህጉራዊ እና አለም አቀፋዊ ውድድሮች ላይ ለተሳትፎ የሚያበቁ ውጤቶችን በማስመዝገቡ ረገድ የሚኖረው አሉታዊ ተፅዕኖ ከፍተኛ መሆኑ ከግምት ውስጥ ገብቶ አሁንም መፍትሄ ያልተበጀለት ጉዳይ ነው፡፡ • የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ወደ ሚዲያ/ለአጠቃላዩ ሕዝብ የሚያስተላልፈው የመጀመሪያዎቹን ሶስት ደረጃዎች ይዘው የሚያጠናቅቁ አትሌቶችን ውጤት ብቻ መሆኑ አወዳዳሪው አካል የሚያደርገውን የራሱን ውድድርም ሆነ አትሌቶቹ የለፉበትን ውጤት ከማስተዋወቅ አኳያ በቂ አይደለም፡፡ • በወንዶች የጦር ውርወራ እና የሴቶች ምርኩዝ ዝላይ ብሔራዊ ሪኮርዶች እንደተመዘገቡ ይታመናል፤ በሴቶች 100ሜ መሰናክል እና የወንዶች 400ሜ መሰናክል የተመዘገቡት ሰዓቶችም የምንግዜውም ፈጣን ሊሆኑ ይችላሉ፡፡ ነገር ግን ውድድሩ በኤሌክትሮኒክስ ታይሚንግ ያልተደገፈ እና የንፋስ ንባብ ያልነበረው መሆኑ ውጤቶቹ በዓለም አቀፍ ደረጃ ተቀባይነት እንዳይኖራቸው የሚያደርግ ነው። • በ20 ኪ.ሜ የእርምጃ ውድድር ላይ በሁለቱም ፆታዎች የተመዘገቡት ሰዓቶች ከሚጠበቀው በላይ እጅግ በጣም ፈጣን እና እውነታዊ አለመምሰላቸው በውድድሩ ላይ የተፈጠረ አንዳች ስህተት መኖሩን የሚያመላክቱ መሆኑ፡፡ እንዲህ አይነት ለማመን የሚከብዱ እና ጥርጣሬን የሚፈጥሩ አይነት ውጤቶች ሲመዘገቡም የተፈጠረ ስህተት መኖር አለመኖሩን ለማጣራት አለመሞከሩ፡፡ • የሴቶች 10 ኪሎ ሜትር ውድድር ላይ ለውድድር የማይፈቀድ የጎዳና ላይ መሮጫ ጫማን በመጠቀም የተመዘገበ ውጤት በሪኮርድነት ጭምር ተይዞ መፅደቁ። ብሔራዊ ፌዴሬሽኑ ከተከለከሉ ጫማዎች ጋር የተያያዙ ዓለም አቀፍ ሕገ ደንቦችን ማወቅና መተግበር ቢገባውም በሴቶች 10 ሺህ ሜትር ውድድር ላይ የተከሰተው ነገር የውድድር ሕገ ደንቦቹ መረጃ በፌዴሬሽኑ ውስጥ በትክክል የተሰራጩ እንዳልሆነ የሚያመላከት ነው፡፡ • በሴቶች 1500 ሜትር የግማሽ ፍፃሜ ውድድር ላይ አትሌት ዳዊት ስዩም የሻምፒዮናውን ሪኮርድ ያሻሻለችበት ውጤት እንደተመዘገበ በውድድሩ ወቅት በተደጋጋሚ ሲነገር ከተደመጠ በኋላ ግልፅ ባልተደረገ ምክንያት ውጤቱ በሐዋሳው ውድድር ላይ ተሻሻሉ ከተባሉት የሻምፒዮናው አዲስ ሪኮርዶች ዝርዝር ውስጥ ሳይካተት መቅረቱም የፌዴሬሽኑን ግልፀኝነት ጥያቄ ምልክት ውስጥ የሚከት ነው፡፡ ከላይ የተዘረዘሩት አዎንታዊ እና አሉታዊ ጎኖች ለረጅም ግዜ የኢትዮጵያን አትሌቲክስ ስፖርት እንቅስቃሴዎች በቅርበት ከመከታተሌ አንፃር በራሴ እይታ ያስቀመጥኳቸው እንደመሆናቸው አንዳንዶቹ ሀሳቦች አከራካሪ ሊሆኑ ይችላሉ፡፡ ሆኖም የውድድር ደንቦችን በአግባቡ ከማስፈፀም አኳያ በታዩት ክፍተቶች ዙሪያ ምንም የሚያከራክር ጉዳይ ስለሌለ በወቅታዊ የውድድር ደንቦች ዙሪያ የግንዛቤ እጥረት ላለባቸው የስፖርቱ ባለድርሻ አካላት በሙሉ አስፈላጊውን ገለፃ እና ትምህርት መስጠት የፌዴሬሽኑ ኃላፊነት ነው፡፡ ከውድድር ጋር የተያያዙ ደንቦችን ከመጣስ አኳያ በሀገር ውስጥ በሚደረጉ ውድድሮች እንደቀላል ነገር የሚታለፉ ጉዳዮች በዓለም አቀፍ ውድድሮች ላይም ተደግመው እንደግል አትሌቶችን እንደቡድን ሀገርን ትልቅ ዋጋ ሊያስከፍሉ ይችላሉና አስፈላጊው ጥንቃቄ ቢደረግ መልካም ነው፡፡ ባለፈው መስከረም ወር በቪየና ሲቲ ማራቶን ውድድሩን በአሸናፊነት ጨርሶ የነበረው ኢትዮጵያዊው ደራራ ሁሪሳ የገጠመውን አንዘንጋው! ሀገራችን ኢትዮጵያን በመልካም ጎኑ ስሟ እንዲነሳ በሚያደርገው እና በትልልቅ ዓለም አቀፍ የውድድር መድረኮች ላይ የኩራታችን ምንጭ በሆነው የአትሌቲክስ ስፖርት እንደጎረቤታችን ኬንያ ዓለም አቀፍ ውድድሮችን የማስተናገድ የብቃት ደረጃ ላይ ደርሰን ማየት የዘወትር ምኞቴ ነው፡፡ የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌደሬሽንም የውድድሮቹን ጥራት ለማሻሻል በትኩረት እንደሚሰራ ተስፋ አደርጋለሁ።
በመጨረሻም በሀዋሳ በተካሄደው 51ኛዉ የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ሻምፒዮና ከመሮጫ ጫማ ጋር የተያያዙ ደንቦችን በማስከበሩ ረገድ የተፈጠረውን ክፍተት እንደማስተማሪያ ብንጠቀምበት በሚል የሚከተለውን ለማለት ወደድኩ፡-
የመሮጫ ጫማ ደንቦች ለትራክ ውድድር
64 ደቂቃ ከ14 ሰከንድ በሆነ ሰዓት የዘንድሮ የራስ አል ካይማህ የግማሽ ማራቶን ውድድር አሸናፊ የሆነችው ግርማዊት ገብረእግዚአብሔር በሐዋሳ በተከናወነው 51ኛው የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ሻምፒዮና ላይ 31 ደቂቃ ከ21.5 ሰከንድ በመግባት የ10,000ሜ. አሸናፊ ሆናለች፡፡ የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽንም ዓለም አቀፉን ደንብ ከግምት ባላስገባ ሁኔታ ውጤቱን በአዲስ የሻምፒዮንሺፕ ሪኮርድነት ጭምር አፅድቆት አልፏል፡፡ ይሁን እንጂ መጋቢት 20/2014 በተደረገው የሴቶች የፍፃሜ ፉክክር ላይ በኢትዮጵያ ምድር የተመዘገበ የምንግዜውም ፈጣን የሴቶች 10 ሺህ ሜትር ሰዓት የሆነው ውጤት በአለም አትሌቲክስ ዘንድ እውቅና ሊሰጠው የማይችል ነው።
● ለምን?
አትሌቷ የሶል ውፍረቱ 40ሚሜ የሆነ ዙምኤክስ ቬፐርፍላይ (ZoomX Vaporfly) ጫማ አድርጋ በመወዳደሯ ምክንያት።
● ደንቡ ምን ይላል?
በትራክ ውድድሮች ላይ የሚፈቀደው ከፍተኛው የሶል ውፍረት ፡-
– 20ሚሜ ከ 800ሜ በታች ለሆኑ ውድድሮች እና ለሁሉም የሜዳ ላይ ተግባራት (ከስሉስ ዝላይ በስተቀር)
– 25ሚሜ ለ800ሜ እና ከዛ በላይ ለሆኑ ውድድሮች እንዲሁም ለስሉስ ዝላይ
– 40ሚሜ ለትራክ ላይ የእርምጃ ውድድሮች
እነዚህ ደንቦች እ.ኤ.አ. እስከ ኦክቶበር 31, 2024 ድረስ በሥራ ላይ ይውላሉ። ከኖቬምበር 1 ቀን 2024 ጀምሮ ለ800ሜ እና ከዚያ በላይ ለሆኑ ውድድሮች እንዲሁም ለስሉስ ዝላይ የሚፈቀደው ከፍተኛ የሶል ውፍረትም ወደ 20 ሚሜ ዝቅ የሚል ይሆናል።
● የትራክ ላይ መወዳደሪያ ስፓይክ ጫማ ከሌለኝስ?
ደንቡ የጎዳና ላይ የመሮጫ ጫማዎች በትራክ ላይ እንዳይደረጉ አይከለክልም ነገር ግን በ25 ሚሊ ሜትሩ ገደብ ምክንያት 30 ሚሜ ወይም 40 ሚሜ የሆኑ የጎዳና ላይ መሮጫ ጫማዎች በትራክ ውድድሮች ላይ እንዲደረጉ አይፈቅድም፡፡
● ለበለጠ መረጃ :-
https://www.worldathletics.org/news/press-releases/new-athletic-shoe-regulations-approved-2022
Opinions
On the TPLF’s Love Affair With ‘Genocide’

Today, the joint investigation report by the Ethiopian Human Rights Council and the UNHR
on human rights violations committed in Tigray concluded that there is no evidence that genocide has taken place so far. While this is a bit of a setback for the TPLF, which has wanted the world to believe—since the 1990s, even as the TPLF was dominating power in Addis—that a genocide has been perpetrated against the people of Tigray, unfortunately the group still appears to be determined to make genocide a reality. This is confusing for people who don’t understand why the TPLF is obsessed with genocide, why its internet cadres began using #TigrayGenocide in April 2020, months before the war began. So many weapons have been deployed in this war, and among them: confusion and obfuscation.
In the past several months and more so in the past few weeks, we have been getting
testimony after testimony from allied Amhara forces fighting the TPLF that Tigrayan residents of cities in Wollo have been collaborating with the TPLF by a) attacking ENDF and allied forces from behind; b) forcing ENDF and allied forces to withdraw from towns and cities afraid of committing large scale massacres by firing back at the civilians (Tigrayans) firing at them; c) helping the TPLF locate and execute young Amharas believed to be a threat; and d) in at least one horrifying account by an IDP who managed to escape occupied territories, handing TPLF soldiers a list of women to rape. Another shocking development in the past several months has been the widespread use of child soldiers by the TPLF, which, according to experts who have studied the practice, is an “alarm bell” calling attention to possible plans to commit mass atrocities. The use of child soldiers by the TPLF and its attendant implications, along with the widespread deployment of civilian sleeper agents in Amhara cities the TPLF has taken over, serves to create an overall perception of every Tigrayan as a potential enemy, sowing fear and mistrust.
Many Ethiopians are looking at this and wondering: why are Tigrayan elites on the internet
either celebrating the TPLF’s advance via these toxic methods or silent about all this? How can they not see how dangerous this is for everyone, especially for Tigrayans who live outside Tigray? How can they not see that there is no “winning” after stoking all this lasting animosity? Do Tigrayan elites not understand that there can be no justice for Tigray—whether Tigray secedes or not—unless there is justice for her neighbors, for Tigray does not exist in a vacuum? The questions are being asked but nobody is answering them. Our academic class has largely failed to offer viable analyses of the ideas driving this war, as they failed over the past fifty years in regards to coming up with a fitting paradigm for understanding Ethiopia’s unique situation.
Here is my humble attempt to explain what I think is happening with the TPLF’s obsession
with—and with its active attempt to inspire—genocide:
The most successful psychopaths in any field understand that, in order to win anything, one
must risk everything, including the very thing one is supposedly fighting for. In the case of the
TPLF (and associated Tigrayan political elites), whose motto appears to be “give me supremacy or give me death,” that “everything” they are risking is the lives of ordinary Tigrayans in whose names they are fighting. We have seen over the past several months the extent to which the TPLF is willing to go to sacrifice ordinary Tigrayans in order to get what it wants: wave after wave after wave of young poorly armed and inexperienced Tigrayans were unleashed upon ENDF and Amhara and Afar forces in order to force the latter to waste ammunition and energy before the more experienced soldiers are sent.
So, for a political group who sends tens of thousands, if not hundreds of thousands, of
young Tigrayans towards open fire, violence against hundreds of thousands of Tigrayans is nothing if it means the TPLF will in the end win the “prize” it has been obsessed with for decades: genocide. You see, merely attaining power in Addis Ababa is not enough for the TPLF, whose core driving ideology is Tigrayan supremacy. Power is temporary; anybody can take it away from you, and the 2018 uprisings demonstrated that. Genocide is forever. Nobody can take away from you the story of genocide committed against your people.
The TPLF looked at countries like Israel and Rwanda and realized what a potent instrument
genocide is for establishing perpetual minority rule. We have some indications suggesting that the TPLF views Israel as a model. When the war between Ethiopia and the TPLF began in November 2020, Sekoutoure Getachew, a TPLF official, went on TV to tell us that the TPLF’s decision to launch a preemptive attack on the Northern Command was inspired by how the young state of Israel, feeling threatened by her neighbors, launched preemptive attacks against them in the “six-day war” of 1967. Another indication is the manner in which the TPLF, during its 27 years in power, invested heavily in creating a wealthy and strongly networked Tigrayan diaspora which has been used to lobby and influence western governments and organizations much in the same way as the Jewish diaspora aids the state of Israel. The TPLF has figured out that truth does not matter in politics, especially in international politics. If you have the wealth and the personnel to peddle your preferred narrative, if you have the military power to subdue the people you want to subdue, if you are willing to make concessions to external forces (US, Egypt, etc), you can do unspeakable things to others (much like the state of Israel does to Palestinians) and still manage to portray yourself as the victim.
This calculation is so far working for the TPLF, but nothing would seal the deal like the actual
commission of genocide—or something that looks like it—against Tigrayans. As we have seen over the past twelve months, western governments and organizations have shown their willingness to adopt TPLF’s narratives without scrutiny and can easily reward the TPLF with its much pursued prize, genocide, even if actual genocide doesn’t take place.
But why does the TPLF need genocide to establish minority rule? Because, as we saw in their
first tenure in power, you can only rule with an iron fist for a limited period of time. Leaders of the TPLF are adherents of Tigrayan supremacy: the idea that Tigrayans, as the “only” heirs of the Axumite empire, are the natural rulers of the Ethiopian state, and cannot be ruled by “barbarians” south of them. The only acceptable power arrangement for the TPLF is one in which Tigrayans are either directly dominating political power or are the perpetual kingmakers pulling all the major strings. Anything outside that, any system that forces Tigrayans to live on equal footing with everyone else, is unacceptable. And this kind of domination by a minority cannot coexist with a democratic system that the majority of Ethiopians clearly prefer. So, the TPLF needs something more potent than pure political/economic/military power to justify bypassing democracy to establish itself as the permanent ruler/kingmaker of Ethiopia. It needs a new and powerful raison d’être to justify its domination not just to Tigrayans and the rest of Ethiopians but, and most importantly, to the rest of the world. If a genocide were to be committed against Tigrayans (or if the U.S. decides to reward the TPLF with the genocide label even in the absence of it), then the TPLF can license itself to impose all manner of drastic measures aimed at “protecting Tigray and
Tigrayans.” This could be anything from redrawing internal borders (and taking debilitating
measures against the peoples whose lands are being robbed—most likely Amharas and Afaris—so that they will never be in a position to assert themselves) to ethnic cleansing and genocide against populations considered to be a threat. And when you oppose it, the TPLF will say “you committed a genocide against Tigrayans” over and over and over, and its western backers will repeat the same chorus. If they have been this loud over a non-existent genocide over the past twelve months, just imagine what it would be like if the U.S. or UN rewards them with that label.
And this is where the Ethiopian government’s major dilemma comes from: if ENDF and
Amhara forces fight to regain their cities and towns, they risk committing large scale massacres. The TPLF networks reported to be operating within these cities wear civilian clothing and fire at the armies from inside civilian establishments, in an apparent attempt to set up pro-Ethiopia forces. Pro-Ethiopia forces are essentially being dared to commit large scale massacres in order to win back their own cities. So far, they are choosing to withdraw from these towns and cities. But that is another problem: not only is the TPLF committing unspeakable violence against civilians and destroying infrastructure in those cities, the takeovers are emboldening it to continue pressing, giving young people back in Tigray false hope that they are winning and—this is very important—the false idea that they are being “welcomed” by locals in those cities. Then more and more and more young Tigrayans are sent to their deaths.
So the Ethiopian government is stuck between a rock and a hard place. One option is
allowing its forces to do whatever it takes to take back territory, thereby offering protection to its citizens in Wollo and elsewhere, but also risking the “genocide” label by western governments who have been eagerly waiting for such an opportunity so that they can blackmail the government into submitting itself to their wishes on GERD and other issues. Option two is avoiding large scale violence and allowing the TPLF to take power in Addis Ababa and do to Ethiopia what it wishes. One of the things it might do to Ethiopia, according to its leaked strategy document, is force a confederation that will no doubt privilege some states, i.e. Tigray, more than others, and that will no doubt be designed to subdue some populations—mainly Amharas and Afaris—who are considered obstacles to Tigray’s aspirations of domination and expansion (in the TPLF’s original manifesto, Afar is claimed as Tigray land).
And there is absolutely no doubt that the TPLF will make big concessions on the GERD in
order to compensate its western and Egyptian backers, if not redraw borders to make Benishangul Gumuz Tigrayan territory. If you think this is wild, read about the history of the state of Israel, the TPLF’s model state. The redrawing of borders that the TPLF undertook in 1991 was also wild at the time; people don’t think of it as outrageous anymore because the fact that they held onto the territory for 30 years has normalized the event in our minds. And that’s all the TPLF needs: another thirty years to normalize all the outrageous things they will do next.
One may argue that this is a false dichotomy, that there is a third or even maybe fourth option: winning these cities back without mass violence much in the same way the ENDF managed to do during its first campaign in Tigray. We all should pray for such a miracle, of course. However, one can also say that in the early days of the war, the TPLF was mostly withdrawing from Tigrayan cities to avoid urban warfare. And even when they engaged in urban warfare, it was not at the same scale and intensity as has been the case over the past four and half months or so. Starting in mid June, the TPLF’s use of civilians as human shields and fighters stopped being just another weapon in its arsenal and became a center of its operations. The near collapse of the ENDF inside Tigray right before its withdrawal was precipitated by the TPLF’s intensified use of “civilians” to trap the ENDF. Many ENDF soldiers chose to surrender rather than fire at those “civilians.” It is still possible to avoid large scale violence in the attempt to retake towns in Wollo, but the risk for it is very high, and is possibly behind the federal government’s reluctance to take decisive actions.
The point is: barring miracles, the Ethiopian government is positioned to lose something
one way or another. All that is left is choosing its preferred poison. Perhaps one thing to consider for the federal government is: the rights of Amharas and Afaris to defend themselves against the existential threats posed against them by the TPLF is much bigger than the national government’s concerns about its place and relationships with the rest of the world. If the federal government decides to risk the disintegration of Ethiopia, like it has done so far either due to incompetence or severe fear of committing large scale violence, that is fine for the federal government. But when you allow that disintegration to happen, please don’t leave the people of Amhara and Afar in a vulnerable position, unable to defend themselves and their lands. If we must return to the State of Nature, at least give these two peoples, who have so far shed more blood than anyone else in defense of their country, a chance to preserve their lives and their lands. Give them the resources they need to defend themselves before it is too late for them even if you feel it is too late for Ethiopia. Anything less is just a continuation of the gross criminal negligence that the federal government has been guilty of so far.
-
EBS Mogachoch9 years ago
[New] EBS Drama Series – Mogachoch : ሞጋቾች | Episode 7
-
Articles9 years ago
Ethiopia’s renewable energy revolution shouldn’t fail to empower its poor
-
News2 years ago
መንግሥት ከሕወሓት ይልቅ ለአገሪቱ ሥጋት የሆኑ ሌሎች ችግሮች አሉብኝ አለ
-
Opinions2 years ago
On the TPLF’s Love Affair With ‘Genocide’
-
Music4 years ago
2019 ESFNA Atlanta: Ethiopian Day – Ethiopia Hagerachin : ኢትዮጵያ ሀገራችን
-
Music4 years ago
2019 #ESFNA Atlanta: Ethiopian Day | Neway Debebe – Hageren Alresam : ሀገሬን አልረሳም
-
Articles8 years ago
ሰበር ዜና፦ ተዋናይት ሰብለ ተፈራ (ትርፌ) በመኪና አደጋ ህይወቷ አለፈ
-
Bahilawi Zefenoch10 years ago
Bahilawi Zefenoch – ባህላዊ ዘፈኖች
Anonymous
April 20, 2014 at 8:21 am
Man kedemo mute menn wey hile selasy sle lejochachew
Anonymous
April 20, 2014 at 8:16 am
Wow I love it but more vedio begun yemrtal kechalachu endgena vedio please ena hile selasy tekbrewal wey weys aletkeberum yet new yetkeberut arfwal betbal sat please please
seifu
April 10, 2014 at 4:03 am
Good
Anonymous
April 9, 2014 at 10:57 am
vedio ቢሆን የበለጠ ጥሩ ነው
Emebet Gebeyehu
April 9, 2014 at 9:29 am
መተታደለል ነወ፡፡
yimegnushal Ayele
April 9, 2014 at 6:19 am
tiru new yemanakachewun eyasawekachihun new enamesegnalen!!!!!!!!!
Anonymous
April 9, 2014 at 1:14 am
Wow I love it thank u
Anonymous
April 9, 2014 at 1:13 am
Wwow I love it thank u
samson
April 8, 2014 at 9:21 pm
Pls this man is a library so if it is recorded it is best.
alemu
April 8, 2014 at 4:19 pm
wow…… i love it
Anonymous
April 8, 2014 at 1:41 pm
WoW ………..!
ሙሀመድ እድሪስ
April 8, 2014 at 12:13 pm
ይህን ቃለመጠየቅ ያዘጋጀዉን ጋዜጠኛ እና ጋዜጣዉን አመሰገናልሁ፤፤
በአካል ታሪኩ ሲፈጸም የነበሩ እማኝ ሰዉ እንዲህ መዘገበብ ለታሪከ በጣም ጠቃሚ ነዉ፤፤ እና በመጨረሻ ሁሉም ያልፋል፤፤