Connect with us

Articles

ሕዝባዊ ትብብር ለተቃዉሞች ስኬት ብቸኛ አዋጭ መንገድ ነው!

Published

on

14218387_1187616214592655_965790004_n

በአብዱረዛቅ ሁሴን

ህዝባዊ ተቃውሞዎች በጊዜ ሂደት እየሰፉና እየተጠናከሩ እየሄዱ ነው፤ የሚያስከፍሉት መስዋትነትም እንዲሁ፡፡ የተቃውሞቹ መስፋትና መጠናከር የኢህአዴግ ራስ ምታት መሆን መጀመረቸው ከሚወስዳቸው ኢሰብአዊ እርምጃዎችና ከሚያወጣቸው የተዘበራረቁ መግለጫዎች መረዳት ቀላል ነው፡፡ ከኦሮሚያ ክልል በዘለል በአማራ ክልል እየተካሄዱ ያሉት ተቃውሞዎች የህዝብን ጥያቄ በሰላም መፍታት ለሚሳነው ኢህአዴግ ሰላሙን ነስተውታል፡፡ እስካሁን የሄደበት መንገድና የአገዛዙ ባህሪ ለሚነሱት ጥያቄዎች ተገቢ መልስ ሊሰጥ ይችላል ብሎ መጠበቅ ከባድ ነው፡፡ ተቃዉሞው እየተካረረ በሄደ ቁጥርና የሚከፈለው መስዋትነትም እየጨመረ ሲሄድ ኢህአዴግ መልስ ልስጥ እንኳን ቢል የሚሰማው መኖሩን የሚያጠራጥርበት ደረጃም እየተደረሰ ነው፡፡ ያው እስካሁን ካልተደረሰ ማለቴ ነው፡፡ ስለዚህም ቀጣይ ጊዜያት መንግስት ተቃዉሞቹን ለመጨፍለቅ ያገኘውን ድንጋይ የሚፈነቅልበት እና ተቃውሞውም እየከረረና ጉልበተኛ እየሆነ የሚሄድበት ይመስላል፡፡

መንግስት ከሚፈነቅላቸው ደንጋዮች ውስጥ በቅርቡ የኮሚኒኬሽን ሚንስትር /ቤት እንዳስፈራራውም የህብረተሰብ ትስስርን ማፈራረስን አላማ ሊያደርግ እንደሚችል ነው፡፡ የሶሪያ እልቂትን እንደመማሪያ ማንሳት ትቶ እንደ ማስፈራሪያ መጠቀሙ የስርአቱን ንቅዘት ያሳያል፡፡ በከፍተኛ ጥንቃቄ እና በጠንካራ ዲሞክራሲ መታገዝ ያለበት የብሄር ተኮሩ ፌደራሊዝም ኢህአዴግን በመሰሉ አምባገን መንግስታት እጅ ሲወድቅ የሶሪያና የሩዋንዳ መሰሉ እልቂትን ለስልጣን መክረሚያ አድርገው እንደ መጨረሻ ካርድ አይጠቀሙም ብሎ ማሰብ ሞኝነት ነው፡፡ የኢትዮጵያ ፖለቲካን በቅርብ ከሚያውቁና በውስጡም ካለፉ እንደ ዶክተር ነጋሶ ጊዳዳና ፕሮፌሰር መራራ ጉዲና ካሉ አንጋፋ ፖለቲከኞችና ምሁራን አፍም ተመሳሳይ ስጋት ሲንጸባረቅ መስማቱም የጉዳዩን አሳሳቢነት ያጎላዋል፡፡

አጠቃላይ ሂደቱ መስመር እንዳይለቅና መጨረሻውም የተሻለች ዲሞክራሲያዊት ኢትዮጵያን መፍጠር እንዲሆን ሁሉም ክፍል ሃላፊነት አለበት፡፡ እንዲህ አይነት አገራዊ ሃላፊነትን ከኢህአዴግ መጠበቅ ቢከብድም በአገዛዙ በደል እና በዲሞክራሲ እጥረት የተነሳው ህዝብ እና በተለይም እንቅስቃሴውን የሚመሩ አካለት ሃላፊነት ከሁላችንም የከበደ ነው፡፡ ይህን ፈታኝ ጊዜ በብቃት ለመወጣትና የሁላችን የሆነች ዲሞክራሲያዊት ኢትዮጵያን ለመፍጠር እስካሁን በታሪካችን ተከስቶ የማያውቅ ባህሪ ያለዉን የኢህአዴግ አገዛዝ በቅጡ መገንዘብና በጥንቃቄ ማቀድን ይጠይቃል፡፡

3+1

አራት መሰረታዊ የሃይል ምንጮች አሉ፡ፖለቲካ፣ ወታደር፣ ኢኮኖሚ (3) + ህዝብ (1)፡፡ የአንድ መንግሰት ጥንካሬ እነዚህ የሃይል ምንጮች ላይ ባለው የቁጥጥር መጠን ይለካል፡፡ ዲሞክራሲያዊ በሆኑ ሃገራት ህዝብ የበላይ ወሳኝ ስለሆነ የህዝብ ምርጫ በፖለቲካው ወንበር ማን መቀመጥ እንዳለበት በመወሰን የአገሪቱን ወታደራዊና ኢኮኖሚያዊ ተክለ ሰውነት የመወሰን አቅም አለው፡፡ የህዝብን ምርጫ መሰረት በማያደርጉ መንግስታትና ሃገራት ውስጥ ግን የሶስቱንን የሃይል ምንጮች የተቆጣጠሩ ሃይላት የአገሩቱን እጣ ፈንታ መወሰኑ ላይ ትልቅ ሚናን ይጫወታሉ፡፡ በኢትዮጵያ የቅርብ ጊዜ ዘመናዊ ታሪክ የነዚህ የአራት ሃይል ምንጮች ሚና የአንድ መንግስትን እድሜ እየለኩ ሲቆርጡ ተስተውሏል፡፡

ፊውዳላዊ መሰረት የነበረው የቀዳማዊ አፄ ሃይለስላሴ መንግስት ዘመናዊነትን ወደ ወታደሩ ከማስገባቱ በፊት በንጉሱ አካባቢ ያሉ መኳንንት የአገሪቱን ፖለቲካዊ ስልጣን፣ ወታደራዊ ሃይልና ኢኮኖሚውን በስፋት ይቆጣጠሩት ነበር፡፡ ዘመናዊ ትምህርትና ዘመናዊነት እየተስፋፋ በመጣ ቁጥር ግን ወደ ፖለቲካዊ ስልጣን የሚመጣው ለአገዛዙ ቅርብ የነበረ ቢሆንም ከበፊት መኳንንቶችና ባላባቶች በእጅጉ ባነሰ መልኩ ለስርአቱ ስሜታዊና  እና ኢኮኖሚያዊ ትስስሩ የቀነሰ መሆን ጀመረ፡፡ የወታደሩ ሙሉ ለሙሉ ከፊውዳላዊ ወታደራዊ አደረጃጀት ነፃ መሆኑ የንጉሱን ስርአት ከህዝብ ተቃዉሞ ጠለላ ሊሆኗቸው ከሚችሉት ሁለት ዋነኞቹን የሃይል ምንጮች እንዲያጡ አደረጋቸው፡፡ በኢኮኖሚው (በብዛት የመሬት ባለቤትንትን ይመለከታል) ዘንድ ምንም እንኳን ለስርአቱ ቅርብ በሆኑ ሰዎች ዘንድ ቢሆንም ሊከሰት የሚችልን ተቃውሞ ለማስቆም በሚረዱት ፖለቲካዊና ወታደራዊ ተቋማት ውስጥ ግን ሁነኛ ቦታ አልነበረቸውም፡፡ ስለዚህም ንጉሱ የህዝብን ጥያቄ ከመመለስ ውጪ ለመጨፍለቅ የሚያስችል በቂ የሃይል ምንጭ ቁጥጥር ሳይኖራቸው ቀረ፡፡ ጥያቄዎችንም መመለስ ሲሳናቸውና አራተኛ ሃይል የሆነው ህዝቡ ተቃውሞውን እያፋፋመ ሲሄድ ከሶስቱ የሃይል ምንጮች አንዱ የሆነው ወታደር ከህዝቡ ጎን በመቆም የሃይል ሚዛኑን በማዛባት አገዛዙ እንዲያበቃ አደረገው፡፡

በደርግ ዘመንም እነዚህ አራት የሃይል ምንጮች ትስስር አገዛዙን እድሜ መወሰኑ ላይ ከፍተኛ ሚና ነበራቸው፡፡ ደርግ ፖለቲካዊ ስልጣንን እና ወታደራዊ ሃይልን ሙሉ ለሙሉ በቁጥጥሩ ውስጥ አድርጎ ነበር፡፡ ፖለቲካዊ ስልጣኑን በመጠቀም የፈለገውን ሲሾም የፈለገውን ሲሽር የፈለገውን ሲከስ የፈለገውን ሲያስር ነበር፡፡ ወታደራዊ ሃይሉ ደግሞ ያለ ማንኛውንም ተቃውሞዎች ላይ ያለርህራሄ እርምጃ ይወስድ ነበር፡፡ በሁለቱም መዋቅሮች ውስጥ የደርግን ርእዮተ አለም የሚያስፈፅሙ አመራር ካድሬዎችን በርካታ ነበሩ፡፡ ደርግ በኢኮኖሚው ላይ ያለው ቁጥጥር መጠንና አይነት ግን ለስርአቱ መውደቅ ሰበብ ሆኖታል፡፡ ኢኮኖሚያዊ የሃይል ምንጭን መቆጣጠር ስንል በሁለት መልኩ ሊገለጽ ይችላል፡፡ የመጀመሪያው የኢኮኖሚውን ወሳኝ ክፍሎች ፖለቲካዊ ስልጣን ባላቸው ግለሰቦች ቁጥጥር ስር መሆንን ሲሆን ሁለተኛው ደግሞ የስልጣን ባለቤቶች ስልጣናቸውን ተገን በማድረግ ሰፊ ሃብትን ለግልም ሆነ በአካባቢያቸው ማካበት መቻልን ይመለከታል፡፡ ደርግ የሚያራምደው ርእዮተ አለም ከኢኮኖሚው የወል ተጠቃሚነትን እንጂ የግለሰብ ተጠቃሚነትን የሚፈቅድ አልነበረም፡፡ አንድ በፖለቲካዊ ሹመት ወደ ስልጣን የመጣ ግለሰብ ስልጣኑን በመጠቀም በቀላሉ ሃብት ማካበትና አካባቢው ያሉትን ሰዎችንም የምዝበራው ተጠቃሚ ማድረግ በእጅጉ ከባድ ነበር፡፡ ስለዚህም እንደዚህ አይነት ባለስልጣናትና ወታደራዊ አመራሮች ለደርግ ሊኖራቸው ከሚችለው ርእዮተ አለማዊ ቅንነት ባለፈ ስርአቱ እንዲከርም ተጨማሪ መስዋትነት ሊያስከፍል የሚችል የግልም ሆነ የቤተሰባዊ የጎላ ህልውናዊ ትስስርና ተጠቃሚነት አልነበራቸውም፡፡ አገዛዙ አረመኔነቱ እየጨመረ ሲሄድና የትጥቅ ትግሉም ሲጠናከር ስርአቱና በውስጡ ያሉ ግለሰቦች በቀላሉ መፍረክረክ ጀመሩ፡፡ በስተመጨረሻም የኢኮኖሚያዊ ሃይልን አለመቆጣጠር ከህዝብ ሃይል ጋር ሲደመር በፖለቲካና በወታደራዊ ሃይል የተንጠለጠለውን የደርግ አገዛዝን አወረደው፡፡

እነዚህ የቅርብ ጊዜ ታሪኮቻችን ሁለት ወሳኝ ነገሮች ያስተምሩናል፡፡ የህዝብ የበላይነት በማይረጋገጥባቸው አምባገነን መንግስታት ውስጥ የህዝብ ተቃውሞ ለብቻው የስርአት ለውጥን የማምጣት ሃይሉ ዝቅጠኛ መሆኑን፤ በሌላ በኩል በስልጣን ላይ ያለ አምባገነናዊ መንግስት ፖለቲካዊ፣ ወታደራዊና ኢኮኖሚያዊ የሃይል ምንጮችን በአግባቡ ካልተቆጣጠረ ከሶስት አንዳቸው ከህዝብ ጋር በማበር መጨረሻውን በቀላሉ ሊያቀርቡት እንደሚችሉ፡፡ የኢህአዴግ መንግስት በተለይም ግንባሩን በግንባር ቀደምትነት እየመሩት ያሉት የህወሃት ልሂቃን ፖለቲካዊ እና ወታደራዊ የሃይል ምንጮችን መቆጣጠር መቻላቸውና በሶስተኝነትም ግለሰባዊም ሆነ ቡድናዊ ኢኮኖሚያዊ ጥቅምንም እያካበቱበት በመሆኑ ከአገዛዙ ጋር ያለውን ትግል ከባድ፣ ጥንቃቄና ቆራጥነት የሚያስፈልገው እንደሆነ ያሳየናል፡፡

የህዝብ ሃይልን ማፈርጠም

የሃገርን እጣ ፈንታ መወሰን ከሚችሉ የሃይል ምንጮች ውስጥ ህዝብ ሲቀር ፖለቲካዊ፣ ወታደራዊ እና ኢኮኖሚያዊ የሃይል ምንጮች በኢህአዴግ በተለይም ህወሃት ሹማንቶችና አካባቢያቸው ባሉ ግለሰቦች ቁጥጥር ስር ይገኛሉ፡፡ ለነዚህ ባለስልጣናት ከስልጣን መወገድ ማለት እንደ ንጉሱና ባላባቶቻቸው ኢኮኖሚያዊ ኪሳራ ብቻ፤ እንደ ደርግ ባለስልጣናት ፖለቲካዊና ወታደራዊ ስልጣንን ማጣት ብቻ ሳይሆን እስከዛሬ ያከማቹትን ፖለቲካዊ፣ ወታደራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ቁጥጥርና ጥቅም ማጣትም ጭምር ነው፡፡ የሶሪያ የእልቂት ምሳሌንም ማንሳት ያስፈለጋቸውም ለዚሁ ነው፡፡ ሶሪያን ለረጅም ጊዜ እየመራ ያለው በወታደራ መፈንቅለ መንግስት የመጣው የባዝ ፓርቲ በአብዛኛው በሶሪያ ውስጥ አስር ፐርሰንት ከማይሞሉት አለዋይቶች የተወጣጣ ሲሆን ለረጅም ጊዜም የሃገሪቱን ፖለቲካዊ፣ ወታደራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ሃይሎችን ተቆጣጥሮ ቆይቷል፡፡ ግጭቱ ከመንግስት ህዝብ አልፎ ሴክቴሪያን ቅርፅ መያዝ ሲጀምር በሽር አሳድም ሆነ ባዝ ፓርቲ ትግሉን ስልጣን ልቀቅ አትልቀቅ ብቻ ሳይሆን ስልጣንን፣ ወታደራዊን እና ኢኮኖሚያዊ ጥቅማቸውን ከማሳጣት አልፎ የአለዋይቶችን እልቂት የሚያስከትል እንደሆነ ስለተገነዘቡ በቁጥጥራቸው ስር ያለውን ማንኛውንም ፖለቲካዊ፣ ወታደራዊና ኢኮኖሚዊ ሃይል በመጠቀም እስከመጨረሻው የደም ጠብታ እንዲታገሉ አስገደዳቸው፡፡ የህዝብ አመፅ ለብቻው የመንግስትን ለውጥ ማምጣትም ተሳነው፤ ህዝብን ሳይዙ ፖለቲካዊ፣ ወታደራዊና ኢኮኖሚያዊ ሃይሎችንም መቆጣጠር ሃገርን ለማስተዳደር በቂ ሳይሆንም ቀረ፡፡ በስተመጨረሻም ታሪካዊቷ ሶርያ የህዝብ እልቂት ፣ ጭፍጨፋ እና የአገር ውድመት ምሳሌ አደረጓት፡፡

በአገራችን እየሰፋ ያለውንም ተቃውሞ በአግባቡ መምራት እስካልተቻለ ድረስ ወደ ተመሳሳይ የእልቂት ቦይ መፍሰሳችን እንደማይቀር መተማመኛ ማንም ሊሰጠን አይችልም፡፡  ህዝባዊ ተቃውሞው ለግዜው በቁጥጥሩ ውስጥ ያለው የህዝብ ሃይል ብቻ መሆኑን በመገንዘብ የቀሪ ሶስት የሃይል ምንጮችን ከተቆጣጠጠውን ህወሃት/ኢህአዴግን በጥንቃቄ መታገል አለበት፡፡ ትግሉ የህወሃት ልሂቃንን የያዙተን የሃይል ምንጮች በሚያቀጭጭና የህዝብ ሃይልን በሚያፈረጥም መልኩ ስትራቴጂዎች ሊኖሩት ይገባል፡፡ የሚከተሉት አካሄዶች በዚህ ረገድ ሊረዱን ይችላሉ፡፡

ኢህአዴግና ህዝብን መለየት

ኢህአዴግ ከሚያራምደው አስተሳሰብና ከሚከተለው ፖሊሲ ተጠቃሚ የሆነ የህብረተሰብ ክፍል ይኖራል፡፡ ምናልባትም ይህ ተጠቃሚነት ለአንዳንድ የህብረተሰብ ክፍሎች ከሃያ አምስት አመቱ ቆይታው በተወሰኑት ውስጥ ሊሆን ይችላል፤ ለሌሎች ደግሞ እስካሁንም ሊቀጥል የሚችል፡፡ በቋንቋው መማር መቻሉን፣ የራሱን የህብረተሰብ ክፍል የማስተዳደር እድል መሰጠጥን እና የመሳሰሉ ማንነት ነክ ጉዳዮች ላይ ኢህአዴግ በሚከተለው ርእዮተ አለም ተጠቃሚ የሆኑ ህዝቦች ለአገዛዙ ቅርብ ሊሆኑ እንደሚችሉ መገመት አያዳግትም፡፡ ከስርአቱ ጋር የቅርብ ትስስር በመመስረትም ኢኮኖሚያዊ ጥቅምን የጋበሱም በስፋት ይኖራሉ፡፡ እነዚህ የህብረተሰብ ክፍሎች ጥቅማቸውን ለማስጠበቅ ከኢህአዴግ ጎን የመሰለፍ እድላቸው ከፍተኛ ነው፡፡ ሕዝብ ብቸኛ የሃይል ምንጩ የሆነው የተቃውሞ እንቅስቃሴ እነዚህን ከስርአቱ ጋር የጥቅም ትስስር እንጂ መሰረታዊ ቁርኝት የሌላቸውን የህብረተሰብ ክፍሎች አስፈላጊውን የቃልም ይሁን የተግባር መተማመኛ በመስጠት ለኢህአዴግ ሊሰጡ የሚችሉትን ድጋፍ መቀነስ ይገባዋል፡፡ የስርአቱ መወገድ ከነሱ ህልውና መክሰም ጋር እንደማይያዝና ዲሞክራሲያዊት በሆነች ኢትዮጵያ የሁሉም መብት ተከብሮና ታፍሮ መኖር እንደሚቻልም ተስፋን መስጠት ኢህአዴግ ላለመውደቅ ከሚደገፍባቸው ምርኩዞች ዋነኛውን እንማስወገድ ይቆጠራል፡፡

ህወሃትን ከኢህአዴግ መለየት

ህወሃት የግንባሩ ፈላጭ ቆራጭ እንደሆነ ማስረጃ ማቅረብ አያስፈልግም፡፡ በግንባሩ ስር ያሉ ሶስት ድርጅቶችን ከአመሰራረታቸው ዘመን ጀምሮ አሁንም ድረስ በፈለገው ቅርፅና መጠን እየከረከማቸው ኖሯል፡፡ ከፍተኛ አመራራቸውን ጨምሮ የፈለገውን የመሾም፣ የጠላውን የመሻር እና ያስከፋውን የማሰር አቅሙም አለው፡፡ ከጠቅላይ ሚንስቴሩ ጀምሮ የሁሉም ፓሪቲ መሪዎችን ከበስተኋላ የሚያዝና የሚያናዝዝ ህወሃት እንደሆነ ግልፅ ነው፡፡ እነዚህ እጣፈንታቸው በህወሃት ሹማንቶች እጅ ላይ የሆኑ አመራርና ፓርቲዎች የተቃውሞው እንቅስቃሴ በብልሃት ሊጠቀምባቸው ይገባል፡፡ ህዝባዊው ተቃዉሞው እነዚህ ፓርቲዎችና አመራሮቻቸውን በሚሰነዝራቸው ትችትም ይሁን ዛቻ ወደ ጥግ በመግፋት ከህወሃት ጋር ያላቸውን የጥቅምና የስልጣን ግንኙነት ወደ ህልውናዊ ግንኙት እንዳይቀየር መጠንቀቅ የግድ ነው፡፡ ከህዝብና ከስልጣናቹ አንዱን ምረጡ በሚል ወቅቱን ያልጠበቀ ጀብደኝት አጣብቂኝ ውስጥ እንዲገቡ ማድረግ የህዝብን ጥያቄ በጉልበት ለመጨፍለቅ እየሞከረ ላለው አገዛዝ ተጨማሪ የህልውና ትስስር ያላቸው ሃይላትን እንደመደጎም ስለሚቆጠር ተቃውሞዉን የሚመሩ አካላትና ህዝቡ በኢህአዴግ ውስጥም ህወሃትንና ሌሎቹን በለየ መልኩ የትግል እቅዶችን መንደፍ ያስፈልገዋል፡፡

ህወሃትን ከትግራይ ህዝብ መለየት

ህዝብ ለዘላለም ነዋሪ ሲሆን ስልጣን እና ባለስልጣናት ግን አላፊዎች ናቸው፡፡ የዲሞክራሲ ትግልን ከህዝብመንግስት ትንቅንቅ አውጥተን ወደ ህዝብህዝብ ካወረድነው ለእልቂት በር ከፋቾች እንሆናለን፡፡ ለጭቆናው መንስኤ የሆኑትን የጥቂት ልሂቃን ሃጢያት ለአንድ ሙሉ ህዝብ ማሸከም አግባብ ከፍትሃዊነት የራቀ ነው፡፡ ይህ አይነት አካሄድ ከስርአቱ ጋር ምንም አይነት ንኪኪ ከሌላቸው የትግራይ ተወላጆች አንስቶ አገዛዙን ከማናችም በላይ አምርረው የሚጠሉትን ጭምር ኢፍትሃዊ የሆነ ጫና በማሳደር ከህወሃት ጋር ህልውናዊ ትስስር እንዲመሰርቱ ሊያስገድዳቸው ይችላል፡፡ ይህ ለትግሉ ጠላትን ከማብዛቱም በላይ ለእልቂትና ለሃገር መፈራረስ ሰበብም የመሆን እድሉ ከፍተኛ ነው፡፡ የትግራይ ህዝብን ከህወሃት ልሂቃን አለመለየት የዲሞክራሲ እጦት ያስነሳው ተቃውሞ እና አመራሩን ሁለት የመርህ ግጭቶች ውስጥ ይከተዋል፡፡ በአንድ በኩል ህወሃት ዘርን መሰረት ያደረገ ማግለልና ጭቆና እያደረሰ ነው እያልን እኛም ተመሳሳይ አካሄድ የምንከተል ሲያስመስለን በሌላ በኩል ደግሞ ህዝብን እንደ ህዝብ የማያከብር አስተሳሰብ ህወሃት የነፈገንን ህዝብን መሰረት ያደረገች ዲሞክራሲያዊት ኢትዮጵያ እንመሰርታለን ማለት ለትዝብት ይዳርገናል ፡፡ ስለዚህም የትግራይን ህዝብ እንደ ህዝብ የሚወነጅል አካሄድን፣ በትግራይ ተወላጆች ላይ የሚደርስ ስነልቦናዊ ጫናንና የሃይል እርምጃዎችን ግልጽ በሆነ ቃል ማውገዝና ለመከላከል የተቻለውን ያህል ርቀት መጓዝ አንድነቷን ለጠበቀች ዲሞክራሲያዊት ኢትዮጵያ ለተደዋደቁ ሰማእታት ክብር መስጠት ነው፡፡

ማጠቃለያ

በስፋትና በሚያስከፍሉት ዋጋ እየጨመሩ የሄዱት ህዝባዊ ተቃውሞዎች ዲሞክራሲት ኢትዮጵያን ለመመስረት ወደሚያስችለን ግብ እንዲያደርሱን በጥንቃቄ መመራት ይገባቸዋል፡፡ ህወሃት ፖለቲካዊና ወታደራዊ ስልጣኑን ከመቆጣጠሩም ባለፈ ኢኮኖሚያዊ ጉልበትን ማካበቻ በማድረጉ በአገራችን ዘመናዊ ታሪክ ሶስቱን መሰረታዊ የሃይል ምንጮችን የተቆጣጠረ ብቸኛ አገዛዝ ያደርገዋል፡፡ ንጉሱ አራተኛ የሃይል ምንጭ የሆነው ህዝብ ሲያምፅባቸው ዘመናዊነት ወታደራዊ እና በከፊል ፖለቲካዊ የሃይል ምንጮች ነፍጓቸው ስለነበር በቀላሉ ከስልጣን ሊወገዱ ቻሉ፡፡ ደርግ በበኩሉ ፖለቲካዊ እና ወታደዊ ሃይልን ተቆጣጥሮ የነበረ ቢሆንም ሹማምንቱን ከርእዮተ አለም ቅንንት ባለፈ ከስርአቱ ጋር ህልውናዊ ትስስር እንዲኖራቸው ሊያደር የሚችለው ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነትን አስገኝቶላቸው ስላልነበር የህዝብ ሃይል ጫናው ሲበረታ ስርአቱ በቀላሉ መፍረክረክ ቻለ፡፡

ፖለቲካዊ፣ ወታደራዊም ሆነ ኢኮኖሚያው የሃይል ምንጮች ላይ ቁጥጥር የሌለውና የህዝብን ሃይል ብቻ መሰረት ያደረገው የአሁኑ ህዝባዊ ተቃውሞ ግብ እንዲመታ ጠላትን በመቀነስ እና የህዝብን ጉልበት በማፈርጠም ላይ መሰረት ያደረገ ስትራቴጂዎችን መከተል ይገባዋል፡፡ ይህንም በሶስት እርከን በመክፈል ከኢህአዴግ ከስርአቱ ተጠቅሚያለው ከሚልው ህዝብ በመለየት፣ ህወሃትን ከኢህአዴግ በመለየትና የትግራይን ህዝብ ከህወሃት በመለየት ላይ በማተኮር ሰፊ ስራዎችን መስራት የህወሃትን በሌሎች ድጋፍ የፈረጠመውን ጡንቻ ከማመንመኑም በላይ አገሪቱን ከደገሱላት የእልቂት ድግስ በማሰናከል አንድነቷን የጠበቀች ዲሞክራሲያዊት ኢትዮጵያን ለመመስረት የሚደረገውን ትግል ስኬት ያፋጥነዋል፡፡

Articles

በኦስሎ ዳይመንድ ሊግ የ5000ሜ ፉክክር ኢትዮጵያውያን አትሌቶች በሁለቱም ፆታዎች በአሸናፊነት አጠናቀዋል

Published

on

Dawit-Seyaum-1
ትላንት ምሽት በኖርዌይ ኦስሎ በተከናወነው የዳይመንድ ሊግ 5000 ሜ. ውድድር ኢትዮጵያውያን አትሌቶች በወንዶችም በሴቶችም ከአንደኛ እስከ ሶስተኛ ያሉትን ደረጃዎች በመቆጣጠር አሸንፈዋል፡፡ 

በዝናባማ የአየር ሁኔታ ውስጥ በተካሄደው የሴቶች 5000 ሜትር ፉክክር ዳዊት ስዩም በመጨረሻዎቹ መቶ ሜትሮች ውስጥ ፍጥነቷን በመጨመር ጉዳፍ እና ለተሰንበትን ቀድማ አንደኛ ወጥታለች፡፡ የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ለኦሪገን 2022 የአለም ሻምፒዮና ከመረጣቸው ዕጩ አትሌቶች ዝርዝር ውስጥ ያልተካተተችው ዳዊት በኦስሎ ያሸነፈችበት 14፡25.84 የሆነ ሰአት የራሷ ምርጥ ሲሆን እጅጋየሁ ታዬ (14.12.98) እና ለተሰንበት (14፡24.59) ባለፈው ወር በዩጂን ካስመዘገቧቸው በመቀጠልም የዘንድሮ የአለም ሶስተኛው ፈጣን ነው፡፡ በውድድሩ ላይ ከነበሩት ሌሎች ኢትዮጵያውያን መካከል በዘንድሮው የውድድር ዓመት በርቀቱ የመጀመሪያ ተሳትፎዋን ያደረገችው አልማዝ አያና በ14:32.17 ስድስተኛ ሆና አጠናቃለች፡፡ ሀዊ ፈይሳ በ14:33.66፣ ፅጌ ገብረሰላማ በ14:43.90፣ እና አበራሽ ምንሴዎ በ14:47.98 በቅደም ተከተል ሰባተኛ፣ አስረኛ እና አስራ አንደኛ ሆነው ሲያጠናቅቁ ሶስቱም ያስመዘገቡት ሰዓት የራሳቸውን ምርጥ ያሻሻሉበት ሆኗል፡፡ ጥሩነሽ ዲባባ እ.ኤ.አ. በጁን 2008 ዓ.ም. ያስመዘገበችውና 14:11.15 የሆነው የኦስሎ ዳይመንድ ሊግ የሴቶች 5000 ሜትር የውድድር ስፍራ ሪከርድ ይሰበራል ተብሎ ተጠብቆ የነበረ ቢሆንም ሳይሳካ ቀርቷል፡፡  
ዳዊት ስዩም ውድድሩን በድል ካጠናቀቀች በኋላ ለውድድሩ አዘጋጆች በሰጠችው አስተያየት ‹‹ዛሬ ለእኔ ደስታን ስላመጣልኝ በውድድሩ ሰዓት የነበረውን ዝናብ ወድጄዋለሁ ማለት እችላለሁ፡፡ ጠንካራ ተፎካካሪዎች የነበሩበት ከባድ ውድድር ነበር እናም ሁሉንም ለማሸነፍ በቅቻለሁ። በርቀቱ የራሴን ምርጥ ሰዓት ማሻሻል መቻሌም አስፈላጊ ነበር፡፡ በስታድየሙ ውስጥ በከፍተኛ ስሜት ድጋፍ ይሰጡን የነበሩ ወገኖቻችን ነበሩ። ለሰጡን ድጋፍ እናመሰግናለን።›› ብላለች፡፡
 
በኦስሎ የወንዶች 5000 ሜትር የመጨረሻ ፉክክሩ በኢትዮጵያውያኑ ጥላሁን ሀይሌ እና ሳሙኤል ተፈራ መካከል የነበረ ሲሆን ጥላሁን የ1500 ሜትር ስፔሻሊስቱ ሳሙኤልን በአጨራረስ ፍጥነት ቀድሞ በ13:03.51 በአንደኛነት አጠናቋል፡፡ ሳሙኤል ተፈራ የራሱ ምርጥ በሆነ 13:04.35 ሁለተኛ ሲወጣ ጌትነት ዋለ የግሉ የዓመቱ ምርጥ በሆነ 13:04.48 ሶስተኛ ደረጃን ይዞ ጨርሷል። በውድድሩ ላይ የነበሩት ሌሎች ኢትዮጵያውያን ሚልኬሳ መንገሻ በ13:05.94 አምስተኛ እንዲሁም አሊ አብዱልመናን የራሱ ምርጥ በሆነ 13:16.97 አስረኛ ወጥተዋል፡፡
ጥላሁን ሀይሌ ውድድሩን በአሸናፊነት ካጠናቀቀ በኋላ ለውድድሩ አዘጋጆች በሰጠው አስተያየት ‹‹ሶስት ኢትዮጵያውያን የመጀመሪያዎቹን ሶስት ደረጃዎች ይዘን መጨረስ መቻላችን ጥሩ አፈጻጸም ነበር። እየጠነከርኩ እንደሆነ የተሰማኝ ሲሆን በውድድሩ እና ባስመዘገብኩት ሰዓትም ተደስቻለሁ። ለረጅም ጊዜ ጉዳት ላይ ስለነበኩ ወደ አሸናፊነቱ መመለስ መቻሌ በጣም ጥሩ ነው።›› ብሏል፡፡

በኦስሎ የሴቶች 800ሜ. ውድድር ላይ ተፎካካሪ የነበረችው ኢትዮጵያዊቷ ድሪቤ ወልቴጂ በ1፡58.69 አምስተኛ ሆና አጠናቃለች።
Continue Reading

Articles

የዘንድሮው የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ብሄራዊ ሻምፒዮና በእኔ እይታ

Published

on

IMG_0110
ከመጋቢት19-24/2014 ዓ.ም በሐዋሳ አለም አቀፍ ስቴድዮም የተደረገው 51ኛዉ የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ሻምፒዮና ከሞላ ጎደል ስኬታማ በሚባል ሁኔታ ተጠናቋል፡፡ ከአምስት አመት በኋላ በድጋሚ በአካል በመገኘት ስለተከታተልኩት የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ሀገር አቀፍ ሻምፒዮና የግል ምልከታዬን እንደሚከተለው አጠናቅሬዋለሁ፡፡

የበለጠ ትኩረትን በሳቡት ውድድሮች ዙሪያ የተመዘገቡ ውጤቶችን በወፍ በረር በመዳሰስ ስጀምር ከፍተኛ ፉክክር በታየበት የመጨረሻ ቀን የወንዶች 5000ሜ. የአለም ከ20 አመት በታች ሻምፒዮና የ3000ሜ የብር ሜዳልያ አሸናፊው አሊ አብዱልመና 13፡45.0 በሆነ ሰዓት ከጥላሁን ሀይሌ፣ ጌትነት ዋለ እና ዮሚፍ ቀጄልቻ ቀድሞ አሸናፊ ሆኗል፡፡ የፉክክሩ አካል የነበረው እና የርቀቱ የወቅቱ የአለም ሻምፒዮን ሙክታር እድሪስ ስድስተኛ ወጥቷል። 

ከ20 ዓመት በታች የ3000ሜ የአለም ሻምፒዮኑ ታደሰ ወርቁ በ28፡12.0 የወንዶች 10,000ሜ. ሻምፒዮን ሲሆን በ1996 ዓ.ም. በአትሌት ስለሺ ስህን ተመዝግቦ የነበረውን 28፡16.23 የሆነ የሻምፒዮናው ሪኮርድ ለማሻሻልም በቅቷል፡፡ በ10 ሺህ ሜትር የሴቶች ፉክክር ግርማዊት ገብረእግዚአብሔር በቀዳሚነት የጨረሰችበት 31፡21.5 የሆነ ሰዓት አዲስ የሻምፒዮንሺፕ ሪኮርድ ሆኖ ተመዝግቧል፡፡ በርቀቱ የከዚህ ቀደሙ ሪኮርድ  ለተሰንበት ግደይ ከሶስት ዓመት በፊት ያስመዘገበችው 32፡10.13 የሆነ ሰዓት ነበር፡፡

ሳሙኤል ፍሬው በዘንድሮ የወንዶች 3000ሜ. መሰናክል አፈፃፀም ከአለም ሁለተኛው ፈጣን በሆነ 8፡22.5 ሰዓት አሸናፊ ሲሆን ጌትነት ዋለ ከአራት ዓመት በፊት አስመዝግቦት የነበረውን 8፡28.98 የነበረ የሻምፒዮናው ሪኮርድም አሻሽሏል፡፡ በሴቶች 3000ሜ. መሰናክል ከ800ሜ ወደ ረጅም ርቀት የተሸጋገረችው ወርቅውሃ ጌታቸው በ9፡41.8 ሰዓት መቅደስ አበበን (9:43.8) በማስከትል በአሸናፊነት አጠናቃለች። 

አድሃና ካህሳይ (3:51.0) የወንዶች 1500ሜ ፉክክሩን በበላይት ሲያጠናቅቅ በሴቶች 1500 ሜ አያል ዳኛቸው (4:10.0) ተጠባቂዋ ዳዊት ስዩምን (4:11.1) በመቅደም በአንደኛነት አጠናቃለች። በ800ሜ. ወንዶች ቶሌሳ ቦደና (1:47.1) በሴቶች ወርቅነሽ መሰለ (2:02.1) አሸናፊ ሆነዋል።
ዮብሰን ብሩ በ400ሜ/400ሜ መሰናክል (45.9/50.5) ድርብ ድል ሲቀዳጅ፣ በወንዶች ጦር ውርወራ ኡታጌ ኡባንግ ብሔራዊ ሪኮርድ በሆነ 73.28ሜ. አሸንፏል፡፡ የኋልዬ በለጠው እና ዮሃንስ አልጋው በእርምጃ ሩጫ የሻምፒዮንነት ክብርን ተቀዳጅተዋል።

ጥቂት አስተያየቶች፡-
የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ስፖርት አፍቃሪ እንደሆነ እና ለዕድገቱ እንደሚቆረቆር ሰው በብሔራዊ ሻምፒዮናው ላይ ስለተመለከትኳቸው አዎንታዊ እና አሉታዊ ጎኖች ጥቂት አስተያየቶቼን እንደሚከተለው አስቀምጣለሁ፡-

አዎንታዊ ጎኖች
• ባለው ነባራዊ ሁኔታ ውስጥ ሊገጥሙ የሚችሉትን ተግዳሮቶች በሙሉ በመቋቋም ፌዴሬሽኑ ውድድሩን ከአዲስ አበባ ውጭ አካሂዶ በሰላም ማጠናቀቅ መቻሉ አንደኛው ስኬቱ ነው፡፡

• በሻምፒዮናው ላይ ጥቂት የማይባሉ ታዋቂ አትሌቶች በሀገሪቱ ትልቁ የአትሌቲክስ ፉክክር ላይ ተሳታፊ ሆነው ሲወዳደሩ መመልከት የተቻለ ሲሆን በተለይም በወንዶች 5000 ሜትር ፍፃሜ ላይ የታየው የኮከብ አትሌቶች ፉክክር ልዩ ነበር፡፡

• በውድድሩ ወቅት ለአትሌቲክስ ዳኞች የብቃት ማሻሻያ ስልጠና መሰጠቱም የውድድሩን ጥራት ለማሳደግ የሚረዳ እንደመሆኑ እሰየው የሚባል ነው፡፡
 
• እንደ ኢትዮ ኤሌክትሪክ ያሉት ክለቦች ለአትሌቲክስ ስፖርት የበለጠ ትኩረት በመስጠትና ተጠናክሮ በመቅረብ ከዚህ ቀደም በጠንካራነታቸው ከሚታወቁት መከላከያ እና ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ጋር የቅርብ ተፎካካሪ ሆነው መታየት፤ የኦሮሚያ ክልል፣ ደቡብ ፖሊስ እና ሲዳማ ቡና ክለብ አትሌቶችም ጠንካራ ተሳትፎ ሳይዘነጋ የሻምፒዮናው ፉክክር ድምቀት ነበሩ፡፡  
• የአንዳንዶቹ ተገቢነት አጠያያቂ ቢሆንም ብዛት ያላቸው የሻምፒዮናው ሪኮርዶች የተሻሻሉበት ውድድርም ነበር፡፡ 

አሉታዊ ጎኖች
• የሀገሪቱ ትልቁ የአትሌቲክስ ውድድር ውጤት አሁንም በኤሌክትሮኒክስ የሰዓት መቆጣጠሪያ የማይደገፍ መሆኑ በተለይም በአጭር ርቀት እና በሜዳ ላይ ተግባራት ውድድሮች ላይ የሚሳተፉ አትሌቶች ልፋት ተገቢውን እውቅና እንዳያገኝ እያደረገ ይገኛል፡፡ የሻምፒዮናውን ውጤቶች በዘመናዊ እና ዓለም አቀፉን መለኪያ በሚያሟላ መልኩ አለመያዝ በአህጉራዊ እና አለም አቀፋዊ ውድድሮች ላይ ለተሳትፎ የሚያበቁ ውጤቶችን በማስመዝገቡ ረገድ የሚኖረው አሉታዊ ተፅዕኖ ከፍተኛ መሆኑ ከግምት ውስጥ ገብቶ አሁንም መፍትሄ ያልተበጀለት ጉዳይ ነው፡፡ 
 
• የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ወደ ሚዲያ/ለአጠቃላዩ ሕዝብ የሚያስተላልፈው የመጀመሪያዎቹን ሶስት ደረጃዎች ይዘው የሚያጠናቅቁ አትሌቶችን ውጤት ብቻ መሆኑ አወዳዳሪው አካል የሚያደርገውን የራሱን ውድድርም ሆነ አትሌቶቹ የለፉበትን ውጤት ከማስተዋወቅ አኳያ በቂ አይደለም፡፡
  
• በወንዶች የጦር ውርወራ እና የሴቶች ምርኩዝ ዝላይ ብሔራዊ ሪኮርዶች እንደተመዘገቡ ይታመናል፤ በሴቶች 100ሜ መሰናክል እና የወንዶች 400ሜ መሰናክል የተመዘገቡት ሰዓቶችም የምንግዜውም ፈጣን ሊሆኑ ይችላሉ፡፡ ነገር ግን ውድድሩ በኤሌክትሮኒክስ ታይሚንግ ያልተደገፈ እና የንፋስ ንባብ ያልነበረው መሆኑ ውጤቶቹ በዓለም አቀፍ ደረጃ ተቀባይነት እንዳይኖራቸው የሚያደርግ ነው።

• በ20 ኪ.ሜ የእርምጃ ውድድር ላይ በሁለቱም ፆታዎች የተመዘገቡት ሰዓቶች ከሚጠበቀው በላይ እጅግ በጣም ፈጣን እና እውነታዊ አለመምሰላቸው በውድድሩ ላይ የተፈጠረ አንዳች ስህተት መኖሩን የሚያመላክቱ መሆኑ፡፡ እንዲህ አይነት ለማመን የሚከብዱ እና ጥርጣሬን የሚፈጥሩ አይነት ውጤቶች ሲመዘገቡም የተፈጠረ ስህተት መኖር አለመኖሩን ለማጣራት አለመሞከሩ፡፡
     
• የሴቶች 10 ኪሎ ሜትር ውድድር ላይ ለውድድር የማይፈቀድ የጎዳና ላይ መሮጫ ጫማን በመጠቀም የተመዘገበ ውጤት በሪኮርድነት ጭምር ተይዞ መፅደቁ። ብሔራዊ ፌዴሬሽኑ ከተከለከሉ ጫማዎች ጋር የተያያዙ ዓለም አቀፍ ሕገ ደንቦችን ማወቅና መተግበር ቢገባውም በሴቶች 10 ሺህ ሜትር ውድድር ላይ የተከሰተው ነገር የውድድር ሕገ ደንቦቹ መረጃ በፌዴሬሽኑ ውስጥ በትክክል የተሰራጩ እንዳልሆነ የሚያመላከት ነው፡፡  

• በሴቶች 1500 ሜትር የግማሽ ፍፃሜ ውድድር ላይ አትሌት ዳዊት ስዩም የሻምፒዮናውን ሪኮርድ ያሻሻለችበት ውጤት እንደተመዘገበ በውድድሩ ወቅት በተደጋጋሚ ሲነገር ከተደመጠ በኋላ ግልፅ ባልተደረገ ምክንያት ውጤቱ በሐዋሳው ውድድር ላይ ተሻሻሉ ከተባሉት የሻምፒዮናው አዲስ ሪኮርዶች ዝርዝር ውስጥ ሳይካተት መቅረቱም የፌዴሬሽኑን ግልፀኝነት ጥያቄ ምልክት ውስጥ የሚከት ነው፡፡

ከላይ የተዘረዘሩት አዎንታዊ እና አሉታዊ ጎኖች ለረጅም ግዜ የኢትዮጵያን አትሌቲክስ ስፖርት እንቅስቃሴዎች በቅርበት ከመከታተሌ አንፃር በራሴ እይታ ያስቀመጥኳቸው እንደመሆናቸው አንዳንዶቹ ሀሳቦች አከራካሪ ሊሆኑ ይችላሉ፡፡ ሆኖም የውድድር ደንቦችን በአግባቡ ከማስፈፀም አኳያ በታዩት ክፍተቶች ዙሪያ ምንም የሚያከራክር ጉዳይ ስለሌለ በወቅታዊ የውድድር ደንቦች ዙሪያ የግንዛቤ እጥረት ላለባቸው የስፖርቱ ባለድርሻ አካላት በሙሉ አስፈላጊውን ገለፃ እና ትምህርት መስጠት የፌዴሬሽኑ ኃላፊነት ነው፡፡ ከውድድር ጋር የተያያዙ ደንቦችን ከመጣስ አኳያ በሀገር ውስጥ በሚደረጉ ውድድሮች እንደቀላል ነገር የሚታለፉ ጉዳዮች በዓለም አቀፍ ውድድሮች ላይም ተደግመው እንደግል አትሌቶችን እንደቡድን ሀገርን ትልቅ ዋጋ ሊያስከፍሉ ይችላሉና አስፈላጊው ጥንቃቄ ቢደረግ መልካም ነው፡፡ ባለፈው መስከረም ወር በቪየና ሲቲ ማራቶን ውድድሩን በአሸናፊነት ጨርሶ የነበረው ኢትዮጵያዊው ደራራ ሁሪሳ የገጠመውን አንዘንጋው! 

ሀገራችን ኢትዮጵያን በመልካም ጎኑ ስሟ እንዲነሳ በሚያደርገው እና በትልልቅ ዓለም አቀፍ የውድድር መድረኮች ላይ የኩራታችን ምንጭ በሆነው የአትሌቲክስ ስፖርት እንደጎረቤታችን ኬንያ ዓለም አቀፍ ውድድሮችን የማስተናገድ የብቃት ደረጃ ላይ ደርሰን ማየት የዘወትር ምኞቴ ነው፡፡ የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌደሬሽንም የውድድሮቹን ጥራት ለማሻሻል በትኩረት እንደሚሰራ ተስፋ አደርጋለሁ።      
      
የ10,000ሜ. አሸናፊ የሆነችው ግርማዊት ገብረእግዚአብሔር (Photo by EAF)

በመጨረሻም በሀዋሳ በተካሄደው 51ኛዉ የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ሻምፒዮና ከመሮጫ ጫማ ጋር የተያያዙ ደንቦችን በማስከበሩ ረገድ የተፈጠረውን ክፍተት እንደማስተማሪያ ብንጠቀምበት በሚል የሚከተለውን ለማለት ወደድኩ፡-

የመሮጫ ጫማ ደንቦች ለትራክ ውድድር

64 ደቂቃ ከ14 ሰከንድ በሆነ ሰዓት የዘንድሮ የራስ አል ካይማህ የግማሽ ማራቶን ውድድር አሸናፊ የሆነችው ግርማዊት ገብረእግዚአብሔር በሐዋሳ በተከናወነው 51ኛው የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ሻምፒዮና ላይ 31 ደቂቃ ከ21.5 ሰከንድ  በመግባት የ10,000ሜ. አሸናፊ ሆናለች፡፡ የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽንም ዓለም አቀፉን ደንብ ከግምት ባላስገባ ሁኔታ ውጤቱን በአዲስ የሻምፒዮንሺፕ ሪኮርድነት ጭምር አፅድቆት አልፏል፡፡ ይሁን እንጂ መጋቢት 20/2014 በተደረገው የሴቶች የፍፃሜ ፉክክር ላይ በኢትዮጵያ ምድር የተመዘገበ የምንግዜውም ፈጣን የሴቶች 10 ሺህ ሜትር ሰዓት የሆነው ውጤት በአለም አትሌቲክስ ዘንድ እውቅና ሊሰጠው የማይችል ነው።

ለምን?

አትሌቷ የሶል ውፍረቱ 40ሚሜ የሆነ ዙምኤክስ ቬፐርፍላይ (ZoomX Vaporfly) ጫማ አድርጋ በመወዳደሯ ምክንያት።

ደንቡ ምን ይላል?

በትራክ ውድድሮች ላይ የሚፈቀደው ከፍተኛው የሶል ውፍረት ፡-
– 20ሚሜ ከ 800ሜ በታች ለሆኑ ውድድሮች እና ለሁሉም የሜዳ ላይ ተግባራት (ከስሉስ ዝላይ በስተቀር)

– 25ሚሜ ለ800ሜ እና ከዛ በላይ ለሆኑ ውድድሮች እንዲሁም ለስሉስ ዝላይ

– 40ሚሜ ለትራክ ላይ የእርምጃ ውድድሮች

እነዚህ ደንቦች እ.ኤ.አ. እስከ ኦክቶበር 31, 2024 ድረስ በሥራ ላይ ይውላሉ። ከኖቬምበር 1 ቀን 2024 ጀምሮ ለ800ሜ እና ከዚያ በላይ ለሆኑ ውድድሮች እንዲሁም ለስሉስ ዝላይ የሚፈቀደው ከፍተኛ የሶል ውፍረትም ወደ 20 ሚሜ ዝቅ የሚል ይሆናል።

የትራክ ላይ መወዳደሪያ ስፓይክ ጫማ ከሌለኝስ?  

ደንቡ የጎዳና ላይ የመሮጫ ጫማዎች በትራክ ላይ እንዳይደረጉ አይከለክልም ነገር ግን በ25 ሚሊ ሜትሩ ገደብ ምክንያት 30 ሚሜ ወይም 40 ሚሜ የሆኑ የጎዳና ላይ መሮጫ ጫማዎች በትራክ ውድድሮች ላይ እንዲደረጉ አይፈቅድም፡፡

ለበለጠ መረጃ :-
https://www.worldathletics.org/news/press-releases/new-athletic-shoe-regulations-approved-2022

Continue Reading

Opinions

On the TPLF’s Love Affair With ‘Genocide’

Published

on

WhatsApp-Image-2021-11-04-at-12.41.51-AM
Ethiopia's Lalibela, a UN World Heritage Site, now under Tigrayan forces control

Today, the joint investigation report by the Ethiopian Human Rights Council and the UNHR
on human rights violations committed in Tigray concluded that there is no evidence that genocide has taken place so far. While this is a bit of a setback for the TPLF, which has wanted the world to believe—since the 1990s, even as the TPLF was dominating power in Addis—that a genocide has been perpetrated against the people of Tigray, unfortunately the group still appears to be determined to make genocide a reality. This is confusing for people who don’t understand why the TPLF is obsessed with genocide, why its internet cadres began using #TigrayGenocide in April 2020, months before the war began. So many weapons have been deployed in this war, and among them: confusion and obfuscation.


In the past several months and more so in the past few weeks, we have been getting
testimony after testimony from allied Amhara forces fighting the TPLF that Tigrayan residents of cities in Wollo have been collaborating with the TPLF by a) attacking ENDF and allied forces from behind; b) forcing ENDF and allied forces to withdraw from towns and cities afraid of committing large scale massacres by firing back at the civilians (Tigrayans) firing at them; c) helping the TPLF locate and execute young Amharas believed to be a threat; and d) in at least one horrifying account by an IDP who managed to escape occupied territories, handing TPLF soldiers a list of women to rape. Another shocking development in the past several months has been the widespread use of child soldiers by the TPLF, which, according to experts who have studied the practice, is an “alarm bell” calling attention to possible plans to commit mass atrocities. The use of child soldiers by the TPLF and its attendant implications, along with the widespread deployment of civilian sleeper agents in Amhara cities the TPLF has taken over, serves to create an overall perception of every Tigrayan as a potential enemy, sowing fear and mistrust.

Many Ethiopians are looking at this and wondering: why are Tigrayan elites on the internet
either celebrating the TPLF’s advance via these toxic methods or silent about all this? How can they not see how dangerous this is for everyone, especially for Tigrayans who live outside Tigray? How can they not see that there is no “winning” after stoking all this lasting animosity? Do Tigrayan elites not understand that there can be no justice for Tigray—whether Tigray secedes or not—unless there is justice for her neighbors, for Tigray does not exist in a vacuum? The questions are being asked but nobody is answering them. Our academic class has largely failed to offer viable analyses of the ideas driving this war, as they failed over the past fifty years in regards to coming up with a fitting paradigm for understanding Ethiopia’s unique situation.


Here is my humble attempt to explain what I think is happening with the TPLF’s obsession
with—and with its active attempt to inspire—genocide:


The most successful psychopaths in any field understand that, in order to win anything, one
must risk everything, including the very thing one is supposedly fighting for. In the case of the
TPLF (and associated Tigrayan political elites), whose motto appears to be “give me supremacy or give me death,” that “everything” they are risking is the lives of ordinary Tigrayans in whose names they are fighting. We have seen over the past several months the extent to which the TPLF is willing to go to sacrifice ordinary Tigrayans in order to get what it wants: wave after wave after wave of young poorly armed and inexperienced Tigrayans were unleashed upon ENDF and Amhara and Afar forces in order to force the latter to waste ammunition and energy before the more experienced soldiers are sent.


So, for a political group who sends tens of thousands, if not hundreds of thousands, of
young Tigrayans towards open fire, violence against hundreds of thousands of Tigrayans is nothing if it means the TPLF will in the end win the “prize” it has been obsessed with for decades: genocide. You see, merely attaining power in Addis Ababa is not enough for the TPLF, whose core driving ideology is Tigrayan supremacy. Power is temporary; anybody can take it away from you, and the 2018 uprisings demonstrated that. Genocide is forever. Nobody can take away from you the story of genocide committed against your people.


The TPLF looked at countries like Israel and Rwanda and realized what a potent instrument
genocide is for establishing perpetual minority rule. We have some indications suggesting that the TPLF views Israel as a model. When the war between Ethiopia and the TPLF began in November 2020, Sekoutoure Getachew, a TPLF official, went on TV to tell us that the TPLF’s decision to launch a preemptive attack on the Northern Command was inspired by how the young state of Israel, feeling threatened by her neighbors, launched preemptive attacks against them in the “six-day war” of 1967. Another indication is the manner in which the TPLF, during its 27 years in power, invested heavily in creating a wealthy and strongly networked Tigrayan diaspora which has been used to lobby and influence western governments and organizations much in the same way as the Jewish diaspora aids the state of Israel. The TPLF has figured out that truth does not matter in politics, especially in international politics. If you have the wealth and the personnel to peddle your preferred narrative, if you have the military power to subdue the people you want to subdue, if you are willing to make concessions to external forces (US, Egypt, etc), you can do unspeakable things to others (much like the state of Israel does to Palestinians) and still manage to portray yourself as the victim.
This calculation is so far working for the TPLF, but nothing would seal the deal like the actual
commission of genocide—or something that looks like it—against Tigrayans. As we have seen over the past twelve months, western governments and organizations have shown their willingness to adopt TPLF’s narratives without scrutiny and can easily reward the TPLF with its much pursued prize, genocide, even if actual genocide doesn’t take place.


But why does the TPLF need genocide to establish minority rule? Because, as we saw in their
first tenure in power, you can only rule with an iron fist for a limited period of time. Leaders of the TPLF are adherents of Tigrayan supremacy: the idea that Tigrayans, as the “only” heirs of the Axumite empire, are the natural rulers of the Ethiopian state, and cannot be ruled by “barbarians” south of them. The only acceptable power arrangement for the TPLF is one in which Tigrayans are either directly dominating political power or are the perpetual kingmakers pulling all the major strings. Anything outside that, any system that forces Tigrayans to live on equal footing with everyone else, is unacceptable. And this kind of domination by a minority cannot coexist with a democratic system that the majority of Ethiopians clearly prefer. So, the TPLF needs something more potent than pure political/economic/military power to justify bypassing democracy to establish itself as the permanent ruler/kingmaker of Ethiopia. It needs a new and powerful raison d’être to justify its domination not just to Tigrayans and the rest of Ethiopians but, and most importantly, to the rest of the world. If a genocide were to be committed against Tigrayans (or if the U.S. decides to reward the TPLF with the genocide label even in the absence of it), then the TPLF can license itself to impose all manner of drastic measures aimed at “protecting Tigray and
Tigrayans.” This could be anything from redrawing internal borders (and taking debilitating
measures against the peoples whose lands are being robbed—most likely Amharas and Afaris—so that they will never be in a position to assert themselves) to ethnic cleansing and genocide against populations considered to be a threat. And when you oppose it, the TPLF will say “you committed a genocide against Tigrayans” over and over and over, and its western backers will repeat the same chorus. If they have been this loud over a non-existent genocide over the past twelve months, just imagine what it would be like if the U.S. or UN rewards them with that label.


And this is where the Ethiopian government’s major dilemma comes from: if ENDF and
Amhara forces fight to regain their cities and towns, they risk committing large scale massacres. The TPLF networks reported to be operating within these cities wear civilian clothing and fire at the armies from inside civilian establishments, in an apparent attempt to set up pro-Ethiopia forces. Pro-Ethiopia forces are essentially being dared to commit large scale massacres in order to win back their own cities. So far, they are choosing to withdraw from these towns and cities. But that is another problem: not only is the TPLF committing unspeakable violence against civilians and destroying infrastructure in those cities, the takeovers are emboldening it to continue pressing, giving young people back in Tigray false hope that they are winning and—this is very important—the false idea that they are being “welcomed” by locals in those cities. Then more and more and more young Tigrayans are sent to their deaths.


So the Ethiopian government is stuck between a rock and a hard place. One option is
allowing its forces to do whatever it takes to take back territory, thereby offering protection to its citizens in Wollo and elsewhere, but also risking the “genocide” label by western governments who have been eagerly waiting for such an opportunity so that they can blackmail the government into submitting itself to their wishes on GERD and other issues. Option two is avoiding large scale violence and allowing the TPLF to take power in Addis Ababa and do to Ethiopia what it wishes. One of the things it might do to Ethiopia, according to its leaked strategy document, is force a confederation that will no doubt privilege some states, i.e. Tigray, more than others, and that will no doubt be designed to subdue some populations—mainly Amharas and Afaris—who are considered obstacles to Tigray’s aspirations of domination and expansion (in the TPLF’s original manifesto, Afar is claimed as Tigray land).


And there is absolutely no doubt that the TPLF will make big concessions on the GERD in
order to compensate its western and Egyptian backers, if not redraw borders to make Benishangul Gumuz Tigrayan territory. If you think this is wild, read about the history of the state of Israel, the TPLF’s model state. The redrawing of borders that the TPLF undertook in 1991 was also wild at the time; people don’t think of it as outrageous anymore because the fact that they held onto the territory for 30 years has normalized the event in our minds. And that’s all the TPLF needs: another thirty years to normalize all the outrageous things they will do next.

One may argue that this is a false dichotomy, that there is a third or even maybe fourth option: winning these cities back without mass violence much in the same way the ENDF managed to do during its first campaign in Tigray. We all should pray for such a miracle, of course. However, one can also say that in the early days of the war, the TPLF was mostly withdrawing from Tigrayan cities to avoid urban warfare. And even when they engaged in urban warfare, it was not at the same scale and intensity as has been the case over the past four and half months or so. Starting in mid June, the TPLF’s use of civilians as human shields and fighters stopped being just another weapon in its arsenal and became a center of its operations. The near collapse of the ENDF inside Tigray right before its withdrawal was precipitated by the TPLF’s intensified use of “civilians” to trap the ENDF. Many ENDF soldiers chose to surrender rather than fire at those “civilians.” It is still possible to avoid large scale violence in the attempt to retake towns in Wollo, but the risk for it is very high, and is possibly behind the federal government’s reluctance to take decisive actions.


The point is: barring miracles, the Ethiopian government is positioned to lose something
one way or another. All that is left is choosing its preferred poison. Perhaps one thing to consider for the federal government is: the rights of Amharas and Afaris to defend themselves against the existential threats posed against them by the TPLF is much bigger than the national government’s concerns about its place and relationships with the rest of the world. If the federal government decides to risk the disintegration of Ethiopia, like it has done so far either due to incompetence or severe fear of committing large scale violence, that is fine for the federal government. But when you allow that disintegration to happen, please don’t leave the people of Amhara and Afar in a vulnerable position, unable to defend themselves and their lands. If we must return to the State of Nature, at least give these two peoples, who have so far shed more blood than anyone else in defense of their country, a chance to preserve their lives and their lands. Give them the resources they need to defend themselves before it is too late for them even if you feel it is too late for Ethiopia. Anything less is just a continuation of the gross criminal negligence that the federal government has been guilty of so far.

Continue Reading

Trending